“ፈረስ ለጦርነት ቀን ይዘጋጃል፤ ድል ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው” (ምሳሌ ፳፩÷፴፩)
በማናቸውም ውጊያ እግዚአብሔርን ኃይል ያደረጉና ለእውነት የቆሙ ሁሉ የሚያሸንፋቸው ማንም አይኖርም፡፡ የእግዚአብሔር ወገን የተባሉ እስራኤል ዘሥጋ በልዩ ልዩ ምክንያቶች ከቤተ አሕዛብ ጋር እንደ ተዋጉና የእግዚአብሔርን ሕጉ ጠብቀው፣ ፈቃዱን በመፈጸምና እርሱን በመማጸን ሀገራቸውን፣ ርስታቸውንና እምነታቸውን ለመከላከል ለሰልፍ በሚወጡበት ጊዜ ድል ያደርጉ እንደ ነበር መጽሐፍ ይነግረናል፡፡