‹‹ወልድ ተውህበ ለነ›› (ኢሳ.፱፥፮)
ውድ ክርስቲያኖች! ይህ የሰው ልጅ ታሪክ የተቀየረበትን ዕለት በደስታ፣ በፍቅር፣ የተጣላን ታርቀን፣ የበደልን ክሰን፣ በኃጢአት ያደፈ ሕይወታችን በንስሐ አንጽተን፣ በቅዱስ ሥጋውና በክቡር ደሙ ሕይወታችንን አስቀድሰን እናክብረው!
መልካም በዓል!
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 998 entries already.
ውድ ክርስቲያኖች! ይህ የሰው ልጅ ታሪክ የተቀየረበትን ዕለት በደስታ፣ በፍቅር፣ የተጣላን ታርቀን፣ የበደልን ክሰን፣ በኃጢአት ያደፈ ሕይወታችን በንስሐ አንጽተን፣ በቅዱስ ሥጋውና በክቡር ደሙ ሕይወታችንን አስቀድሰን እናክብረው!
መልካም በዓል!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ! ነቢያት በብሉይ ኪዳን “አቤቱ ከሰማያት ወርደህ፣ ተወልደህ አድነን” ብለው የተነበዩት ትንቢት ተፈጽሞ አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ወልድ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደበትን ቀን በድምቀት እናከብር ዘንድ ይገባል፡፡
ልጆች! ለዛሬ “የቱን ታስታውሳላችሁ?” በሚለው ላቀረብንላችሁ ጥያቄዎች ምላሾቹን ይዘን ቀርበናል፡፡ አንብባችሁ ምላሽ የሰጣችሁ በርቱ! ያልመለሳችሁ ደግሞ በቀጣይ በምናዘጋጀው ጥያቄና መልስ ተሳተፉ!
“እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ወደ በጎች በረት በበሩ የማይገባ በሌላ መንገድ ግን የሚወጣ እርሱ ሌባ ወንበዴም ነው፤ በበሩ የሚገባ ግን የበጎች እረኛ ነው። ለእርሱ በረኛው ይከፍትለታል፤ በጎቹም ድምፁን ይሰሙታል፥ የራሱንም በጎች በየስማቸው ጠርቶ ይወስዳቸዋል። የራሱንም ሁሉ ካወጣቸው በኋላ በፊታቸው ይሄዳል፥ በጎቹም ድምፁን ያውቃሉና ይከተሉታል፤ ከሌላው ግን ይሸሻሉ እንጂ አይከተሉትም፥ የሌሎችን ድምፅ አያውቁምና።”
ተወዳጆች ሆይ! ስሙ እንደ መዓር በሚጣፍጥ፣ መድኃኒትም በሚሆን፣ በቅዱስነቱ ዘለዓለም ያለ ረዓድ በአስጨናቂዎቻችን ፊት ክብር እና ሞገስ አግኝተን፣ ሕያውም ሆነን በምንኖርበት በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንዴት ሰነበታችሁ? ፍቁራን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ፈቃድ፣ በባሕርይ አባቱ በአብ፣ በባሕርይ ሕይወቱ በሚሆን በመንፈስ ቅዱስም ፈቃድ ሳምንቱን አልፈን በቀጣይ ክፍል እነሆ ተገናኘን!
በባለፈው ሳምንት ስለ ማኅበራዊ ሕይወታችን፣ በእኛ ዘመን ምን እየሆነ፣ ምን እየሠራን እያለፍን እንደሆነ፣ ካለፈው ዘመን ጋር እያመሳሰልን ከራሳችን ጋር እየመዘንን በስሱም ቢሆን ገረፍ አድርገን ለማየት ሞክረናል። ዛሬም ያንኑ ርእሰ አንቀጽ ይዘን ማኅበራዊ ሕይወት በክርስትና አስተምህሮ እና በዘለዓለማዊ የሕይወት ሽግግራችን ያለውን ምልከታ፣ የማኅበራዊ ሕይወት መሳሳት መንሥኤዎችን እና መዳኛ የሚሆነንን ጠቅሰን እናልፋለን።
ሕዝቡን እያሳተ ከገደል ቢመራ
ትእዛዙ ሲፈጸም ለሥጋው የፈራ
የእምነት አርበኖች ሠለስቱ ሕፃናት
ከፊቱ በመቆም መሰከሩ ለእምነት
በእሳት ሲያስፈራ በሚከስመው ነዶ
ጣኦትን ሊያስመልክ ፈጣሪን አስክዶ
ከላይ ከሰማያት መልአክን አውርዶ
እሳቱ ሲበርድ ሰይጣን በዚህ ሲያፍር
ጽናት ተጋድሏቸው ገሀድ ሲመሰክር
የሰው ዘርና መሠረት የሆኑት አዳምና ሔዋን ስያሜያቸው በጾታ ተለይቶ በማይታይበት ሁኔታ (በጋራ ስያሜአቸው) ‹‹ሰው›› የሚሰኙ ሲሆን ‹‹አዳም›› በመባል የሚታወቀው ቀዳሚ ፍጥረትም ከወንድ ጾታ በተጨማሪ የሰው ዘር ሁሉ ምንጭና መጠረያ ሆኖም አገልግሏል፡፡
በአጠቃላይ ‹‹ተባዕታይ/ዊ/››- “ወንዳዊ፣ ወንድ፣ ወንዳማ፣ ወንዳ ወንድ፣ ብርቱም” ማለት ሲሆን ‹‹አንስታይ/ዊ/››- “ሴታም፣ ሴትማ፣ ሴት፣ ባለ ሴትም” የሚለውን ያመለክታል፡፡ አንስትና ብእሲት ለሰው ብቻ ይነገራል፡፡ (ዘፍ.፩፥፳፯)
ጾታቸውና ግብራቸው በአንድነት ሲገለጽ ደግሞ የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ስያሜዎች የሚከተሉትን ትርጉሞች ይይዛሉ፡-
አዳም ማለት “የሚያምር፣ ደስ የሚያሰኝ ሰው፣ ደግ፣ መልከ መልካም፣ የመጀመሪያ ሰው፣ የሰው ሁሉ አባት” የሚል ትርጒም ተሰጥቶታል፡፡
ሔዋን ማለት “ሕይወት” ማለት ነው፡፡ “ሔዋን” ብሎ የሰየማትም አዳም ሲሆን ስያሜው ‹‹የሕያዋን ሁሉ እናት /እመ ሕያዋን/›› መሆኗን ያመለክታል፡፡ (ዘፍ.፪፥፬-፳፬) ከዚህም ሌላ ረዳት ትባላለች፡፡
የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ለትውልድ ማእከል ግንባታ የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ በታኅሣሥ ወር ፳፻፲፯ ዓ.ም. ባካሄደው ልዩ መርሐ ግብር ላይ በመሪጌታ ባሕረ ጥበብ ሙጬ “የሉላዊነት ተጽዕኖ በኦርቶዶክስ ላይ” በሚል ርእስ የቀረበው ጥናታዊ ጽሑፍ ለቤተ ክርስቲያን የሚበጅ ብቁ ዜጋ ለማፍራት በልዩ ትኩረትና በንቃት መሥራት እንደሚገባ የሚያመለክት እንደሆነ ተገልጿል፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ትምህርት እንዴት ነው? እየበረታችሁ ነውን? የምትማሩትን ትምህርት እያጠናችሁ እንደሆነ ተስፋችን ነው፤ በርቱ! ልጆች ለዛሬ ይዘንላችሁ የቀረንበው ባለፉት በተከታታይ ሳምንታት ስንማማረው ከነበረው የአማላጅነት ትምህርት ካነበበችሁት (ከተማራችሁት) መካከል “የቱን ታስታውሳላችሁ” በሚል ርእስ ጥያቄዎችን ነው፡፡ በጥንቃቄ አንብባችሁ መልሶቻችሁን በድረ ገጽ አድራሻችን “website.amharic@eotcmk.org” እና “https://t.me/Hiwot122716” ትልኩልናላችሁ!
የሰው ልጅ ተፈጥሮአዊ ባሕርይ በስሙ ተገልጧል፡፡ የተለየ የሚያደርገውም በአምሳለ እግዚአብሔር የተፈጠረ መሆኑ ነው፤ ነገር ግን አሁን ባለው ዓለም ውስጥ ክብሩን ለማዋረድ የሚሞክር ነገረ ህልውናም ፍጹም በተሳሳተ እይታ የሚተነትን የሐሰት “ሳይንስ” ይስተዋላል፡፡ መላእክት ዕውቀት አላቸው፤ ነገር ግን በኃይለ ዘር አይራቡም:: ከዚህ በተቃራኒው ደግሞ እንስሳት ዕውቀት የላቸውም፤ በኃይለ ዘር ግን ይራባሉ፤ ሰው ግን እንደ መላእክት ዕውቀት እንደ እንስሳት ደግሞ በኃይለ ዘር ስለሚራባ ከሁለቱም የተለየ ያደርገዋል፤ ዳግመኛም መላእክት ሕያዋን ናቸው፤ እንስሳት ደግሞ መዋትያን ናቸው፤ የሰው ልጅ ግን ሕያውም መዋቲም በመሆኑ የተለየ ነው፤ እግዚአብሔር እንዲህ ውብና ቅዱስ አድርጎ የፈጠረው ስላለው ክብር ባለ መረዳትና ባለ ማወቁ ወደ ኃጢአት ሲወድቅ ይስተዋላል፡፡
ሕይወታችንን ስናስብ የሌሎችን በሕይወት መቆየት እንጠባበቃለን። በጋራ ዓለም ላይ አብሮ የጋራ ዓለምን ማቅናት ላይ እንድንመረኮዝ እንገደዳለን። በሕገ ተፈጥሮ ውስጥ ለራሱ የተፈጠረ ፍጥረት የለም። ከእሑድ እስከ ዓርብ ያሉ ፍጥረታት እርስ በራሳቸው ተመጋጋቢ ቢሆኑም ሁሉም ግን ስለ አዳም ተፈጥረዋል። አንዳንዶቹ ለምግበ ሥጋ ምግበ ነፍስ፣ አንዳንዶቹ ለአንክሮ ለተዘክሮ፣ አንዳንዶቹ ለመድኃኒትነት፣ አንዳንዶቹ ለምስጋና፣ አንዳንዶቹ አዳም መሥዋዕት አድርጎ ሊያቀርባቸው፣ ሌሎቹ ደግሞ ለሌላ ለተለያየ ነገር ተፈጥረዋል። እነዚህ ሁሉ ለራሳቸው ሲባል አልተፈጠሩም።