“እግዚአብሔር ብርሃኔ ነው” ቅዱስ ዑራኤል
ጥር ፳፪፤፳፻፲፰ ዓመተ ምሕረት
በቅዱስ ፈቃዱ ዓለምን የፈጠረው ሁሉን ቻይ አምላካችን እግዚአብሔር መላእክትን ከእሳትና ከነፋስ በቀዳሚት እሑድ ሲፈጥራቸው በነገድና ከተሞች ከፋፍሎ እንደነበርና ለእያንዳንዱም ሊቃነ መላእክት እንደሾመላቸው የመጽሐፍተ ፍጥረታት ይጠቅሳሉ፡፡
በብርሃንና በመባርቅት ላይ የተሾመው የስሙ ትርጓሜ “እግዚአብሔር ብርሃኔ ነው” የሆነው ሊቃነ መላአክት ቅዱስ ዑራኤል የከበረች በዓሉ በጥር ፳፪ ቀን ነው፡፡ ለሰው ልጆች ሁሉ ምሕረትን የሚለምነው ይህ መላእክ የአምላክን ፈቃድ፣ የፍርድና የአምልኮቱን ነገር፣ ምሥጢር የሚተርጎምና የሚያስረዳ እንደሆነ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ያስረዳሉ፡፡
የሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ጸሎቱ፣ አማላጅነቱና ተራዳኢነቱ አይለየን፤ ከበዓሉ በረከት ረድኤት ያሳተፈን፤ አሜን!
