የ፲፪ኛው ሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በፎቶ
መጋቢት ፳፬ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን ለ፲፪ኛ ጊዜ ያዘጋጀው የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በቾ ወረዳ ቤተ ክህነት ከአዲስ አበባ ከተማ በሰባ ሁለት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ቱሉ ጉጂ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዛሬው ዕለት ተካሒዷል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይም ከዐሥራ ሦስት ሺሕ ሁለት መቶ አምሳ በላይ ምእመናን መሳተፋቸው ታውቋል፡፡ መርሐ ግብሩ ከሰዓታት በፊት በጸሎት የተፈጸመ ሲኾን፣ የጉባኤውን አጠቃላይ ኹኔታም በሚከተሉት ፎቶዎች ትመለከቱ ዘንድ ጋበዝናችሁ፤

መርሐ ግብሩ በጸሎተ ወንጌል ሲከፈት

የጉባኤው ተሳታፊዎች ቆመው ጸሎተ ወንጌል ሲያስደርሱ

የጉባኤው ተሳታፊዎች በከፊል

ምክረ አበው አቅራቢ መምህራን

የማኅበረ ቅዱሳን ዘማርያን የበገና ዝማሬ ሲያቀርቡ

የመርካቶ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ሰ/ት/ቤት የጎልማሶች መዘምራን መዝሙር ሲያቀርቡ

መጋቤ ስብሐት ዓለሙ አጋ የበገና ዝማሬ ሲያቀርቡ

የጉባኤው ተሳታፊዎች በከፊል

በጉባኤው የተገኙ የቱሉ ጉጂና የአካባቢው ምእመናን በከፊል

ጉዞ ወደ ቱሉ ጉጂ

የቱሉ ጉጂ አካባቢ ወጣቶች መንገድ ሲያስተካክሉ

የመኪኖች መቆሚያ እና የጉባኤው ቦታ በከፊል ከርቀት ሲታይ

ምእመናን ከመኪና ወርደው ወደ ጉባኤው ሲያመሩ

የጉባኤው ሥፍራ በከፊል