የ33ኛው ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ባለ 21 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ

 ጥቅምት 8 ቀን 2007 ዓ.ም.

መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

33 9 2007 01 የ33ኛው ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ማጠቃለያ መርሐ ግብር የተጀመረው ከረፋዱ 2፡46 ነበር፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ ፖትርያርክ አቡነ ማትያስ ጉባኤውን በጸሎት ከከፈቱ በኋላ ብፁዕ ዶ/ር አቡነ ገብርኤል “ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን” በሚል ርዕስ ከምንጊዜውም በላይ የቤተ ክርስቲያንን አንድነት፣ መጠበቅ እንደሚገባ ሰፋ ያለ ትምህርት ሰጥተዋል፡፡

33.02.2007.02በመቀጠልም ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ለሦስት ቀናት በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ውይይት እንዲደረግ ጋብዘዋል፡፡ ሆኖም ግን ቅዱስ ፓትርያርኩ በጉባኤው መክፈቻ ዕለት ማኅበረ ቅዱሳንን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ላይ ብቻ ሰፊና ጠንካራ ውይይቶች ተደርጓል፡፡

የጉባኤው ማጠቃለያ በመጋቤ ብሉይ አእመረ አሸብር ቃለ ጉባኤ ተነቦ ባለ 21 ነጥብ የአቋም መግለጫ ተነቧል፡፡ ከቃለ ጉባኤው ንባብ ለመረዳትም እንደተቻለው ማኅበረ ቅዱሳን በበጀት ዓመቱ በበርካታ ሀገረ ስብከቶች በከፍተኛ ደረጃ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት መደገፉ ተወስቷል፡፡

33.2007.03በመጨረሻም በበጀት ዓመቱ በልማት፣ ዓመታዊ ገቢ በስብከተ ወንጌል፣ በመልካም አስተዳደር የተሻለ አፈጻጸም የነበራቸውን ሀገረ ስብከቶች ደረጃ በማውጣት  ሽልማት ተበርክቶለቸዋል፡፡ሽልማቶቹም የሕዳሴው ግድብ ቦንድ ግዢ፣ መጻሕፍት፣ የቃለ ዓዋዲ መጽሐፍ ተሸልመዋል፡፡

ቅዱስ ፓትርያርኩ ለ33ኛው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ተሳታፊዎች ቃለ ምእዳንና መመሪያ በመስጠት ጉባኤው ተጠናቋል፡፡