ሲመቱ ለሊቀ ዲያቆናት ወቀዳሜ ሰማዕታት ቅዱስ እስጢፋኖስ

የስሙ ትርጓሜ ‹አክሊል› የሆነው በሕገ ወንጌል የመጀመሪያ ሊቀ ዲያቆናትና ቀዳማዊ ሰማዕት የተባለ ቅዱስ እስጢፋኖስ ‹‹ሊቀ ዲያቆናት›› ከመባሉ በፊትም በመጀመሪያ ሐዋርያና ካህን ነበር፤ ከዚያም ዲያቆን ሆኖ ተሾሟል፤ ይህም ጥቅምት ፲፯ ቀን ነው፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ፵ኛ ዓመት ጠቅላላ ዓለም አቀፍ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባዔ ስብሰባ የአቋም መግለጫ

ዕረፍቱ ለሊቀ ጳጳስ አባ ድሜጥሮስ

ቅዱስ ድሜጥሮስ የእስክንድርያ ዐሥራ ሁለተኛ ጳጳስ ከመሆኑ በፊት የቤተ ክርስቲያን ዕውቀት ያልነበረው በግብርና ሥራ የሚተዳደር ሰው ነበር፡፡አባቱ ደማስቆ ወይም እንድራኒቆስ አጎቱ ደግሞ አርማስቆስ ወይም አስተራኒቆስ ይባላሉ፡፡ ሁለቱም በዘመነ ሰማዕታት ከኢየሩሳሌም ርቀው በባዕድ ሀገር በፋርስ ባቢሎን በስደት ለረጅም ዘመናት ይኖሩ ነበር፡፡ በዚህ የስደት ዘመናቸው ከሁለቱ (ደማስቆና አርማስቆስ) በስተቀር በሀገሩ የሚኖሩት አሕዛብ ነበሩ፡፡…

አኀዝ

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የግእዝ ቋንቋን ለመማር ይረዳችሁ ዘንድ በየሁለት ሳምንቱ እያዘጋጀን የምናቀርብላችሁ ‹‹የግእዝ ይማሩ›› ዐምድ የዝግጅት ክፍሉ ባጋጠመው ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ለተወሰኑ ጊዜያት ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም በአዲስ መልክ ለአንባብያን በሚያመች መንገድ አዘጋጅተን አቅርበንላችኋልና በጥሞና ተከታተሉን፡፡

ልጆች ዘወትር ጸልዩ!

እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች? እግዚአብሔር ይመስገን አላችሁ? መልካም፤ እግዚአብሔር አምላካችን የተመሰገነ ይሁን፡፡

ልጆች የዛሬ ትምህርታችን ስለጸሎት ነው፤ በመጀመሪያም የቃሉን ትርጉም እንመልከት፡፡…

ክብረ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ

በምድረ በዳ እንደመላእክት የኖሩትና በዝቋላ ተራራ ባለው ባሕር ውስጥ ፻ (መቶ) ዓመት ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ ሰዎች ምሕረትን የለመኑት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ዕረፍታቸው እንዲሁም ቃል ኪዳን የተቀበሉበት ዕለት በሀገራችን ኢትዮጵያ በድምቀት ይከበራል፡፡

‹‹አንደበትህን ከክፉ ከልክል›› (መዝ.፴፫፥፲፫)

ሰዎች አንደበታችንን እግዚአብሔርን ለማመስገንና በጎ ነገርን ለመናገር ልንጠቀመው ይገባል። በእያንዳንዱ ንግግራችን የምናወጣቸው ቃላትም ሆነ የምንመሠርታቸው ዓረፍተ ነገሮች ከክፋት የጸዱ መሆን አለባቸው። ለዚህም ነው ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹አንደበትህን ከክፉ ከልክል፥ ከንፈሮችህም ሽንገላን እንዳይናገሩ›› በማለት የተናገረው። ሊቁ ቅዱስ ያሬድም በጾመ ድጓው ሲናገር ‹‹ይጹም ዐይን ይጹም ልሳን እዝንኒ ይጹም እምሰሚዐ ሕሡም፥ ዐይን ይጹም፣ አንደበትም ይጹም፣ ዦሮም ክፉን ከመስማት ይጹም›› ብሎ እንደተናገረ አንደበት በቃለ እግዚአብሔር እና በበጎ መንፈሳዊ ምግባራት ካልተገታችና ካልታረመች የሰውን ልጅ ወደ ጥልቅ የበደልና የጥፋት መንገድ ሊጥሉት ከሚችሉ ሕዋሳት አንዲቱ ናት። (መዝ.፴፫ (፴፬)፥፲፫)

‹‹ለነገ አትጨነቁ፤ ነገ ለራስዋ ታስባለችና›› (ማቴ.፮፥፴፬)

ጭንቀት እንደ የማኅበረሰቡ አኗኗርና የኑሮ ፍልስፍና የሚሰጠው ትርጉም ከቦታ ቦታና ከሰው ሰው ይለያያል። የሕዝቦቻቸው መሠረታዊ ፍላጎቶች ባልተሟሉባቸው አንዳንድ ሀገራት ምጣኔ-ሀብታዊ አለመረጋጋት በብዛት የሚስተዋል የጭንቀት መንሥኤ ነው። በአንጻሩ ብዙዎቹ ዜጎቻቸው የቅንጦት ሕይወት በሚመሩባቸው ‹ሥልጡን› ሀገራት ደግሞ፥ ደስታ ይገኝባቸዋል ተብለው የሚጀምሩ የዝሙት፣ የሱስ፣ የዘፈን… የመሳሰሉት እኩይ ተግባራት ከጊዜያት በኋላ እግዚአብሔርን ፍለጋ በሚቃትተውና እውነተኛ ደስታ ምን ማለት እንደሆነ አንጠርጥሮ በሚያውቀው ውሳጣዊ ኅሊናቸው ዕረፍት የለሽ ሙግት የተነሣ ደስታ ሰጪነታቸው አብቅቶ መዳረሻቸው ጭንቀት ይሆናል። በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ለዚህ ኅሊናዊ ምሪት የሚሰጡት መልስ በአብዛኛው አሁንም ተቃራኒውን መሆኑ ነው። ‹‹ለምንድነው የምኖረው?›› ለሚለው ጥያቄያቸው መልሳቸው ‹‹ለምንም!›› የሚል ይሆንና የሕይወታቸውን ፍጻሜ ያበላሸዋል።…

ወርኃ ጽጌ

በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ መሠረት ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፮ ያለው ወቅት ወርኃ ጽጌ (የጽጌ/የአበባ ወር) ይባላል፡፡ በወርኃ ጽጌ አበባዎች ያብባሉ፤ ፍሬም ያፈራሉ፤   በዚህም ወቅት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ እንዲጠብቃት ከታዘዘው አረጋዊው ዮሴፍ ጋር ስትኖር መልኳ አንዳንድ ጊዜ እንደ ጽጌረዳ አበባ ቀይ ሁና፣ በሌላ ጊዜ ደግሞ እንደ ሮማን አበባ ነጭ ሁና ስትታየው፣  ቀይ የነበረው መልኳ ተለውጦ እንደ ሮማን አበባ ጸዓዳ ነጭ፣ ነጭ የነበረው እንደ ጽጌረዳ ቀይ ሲለወጥ በመደንገጥ እርሷ መሆኗን ለማረጋገጥ ‹‹ማርያም›› ብሎ እየጠራ ያረጋግጥ ነበር፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለዚህ ምሥጢር ሲያስረዳ ‹‹መልኳ እንደ ጽጌረዳና እንደ ሮማን አበባ ይለዋወጥበት ስለነበር በአንድ ዓይነት መልክ አላወቃትም›› ብሏል፡፡ በዚህም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እመቤታችንን በአበባ፣ ጌታችንን ደግሞ በፍሬ እየመሰሉ ለማመስገንና ለማወደስ በሚያስችል ምሥጢር የስደቱ ጊዜ በወርኃ ጽጌ እንዲዘከር አድርገዋል፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለዘለዓለሙ የማይደርቀውን የሕይወት ፍሬ ኢየሱስ ክርስቶስን ያስገኘችልን ንጽሕት የማትጠወልግ አበባ ናትና፡፡