‹‹ታጠቡ ንጹሐንም ሁኑ›› /ት.ኢሳ. ፩፡፲፮/

ቤተ ክርስቲያን የግል ንጽሕናንና የአካባቢ ንጽሕናንም መጠበቅ እንደሚገባ የጤና ሥርዓት ሳይዘረጋ በቀድሚነት አስተምራለች፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ ‹‹ታጠቡ ንጹሐንም ሁኑ፤ የሰውነታችሁን ክፋት ከዐይኖቼ ፊት አስወግዱ፤ ክፉ ማድረግንም ተው፤ መልካም መሥራትንም ተማሩ›› /ት.ኢሳ. ፩፡፲፮/ እንዲል የሥጋንም የነፍስንም ንጽሕና መጠበቅ ክርስቲያናዊ መመሪያ ነው፡፡

“ኦሪትና ነቢያት በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ጸኑ” (ማቴ.፳፪፥፵)

መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በተናገረው በዚህ ኀይለ ቃል ፍቅር የሁሉም ነገር ማሰሪያና መደምደሚያ መሆኑን እንማራለን፡፡ ሰው የሕግ ሁሉ ማሰሪያ የሆነውን እርሱም ፍቅርን ገንዘብ ሊያደርግ እንደሚገባ ያስረዳበት አማናዊ ትምህርት በመሆኑም ሁሉም ሊያውቀውና ሊረዳው እንዲሁም በተግባር ሊፈጽመው የሚገባ ነው፡፡

“በመካከላችንም ሆኖ በመስቀሉ አስታረቀን፤ በልዩ ትንሣኤውም ሰውን ዳግመኛም ወደ ገነት መለሰው” (ቅዱስ ኤፍሬም)

አፈ በረከት ቅዱስ ኤፍሬም እመቤታችንን ለማመስገን አጅግ አብዝቶ ይለምን የነበረ፤ በእመቤታችን ጥሪም “አመስግነኝ” የተባለ ታላቅ ሰው ነበር፡፡ በድርሰቱ ምሥጢረ ሥላሴን፣ ምሥጢረ ሥጋዌን፣ ምሥጢረ ጥምቀትን፣ ምሥጢረ ቊርባንን፣ ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታንን፣ በአጠቃላይ ሃይማኖትን ከምግባር፣ ነገረ ድኅነትን ከነገረ ቅዱሳን ጋር አስማምቶ የደረሰና ያስተማረ ታላቅ አባት ነው፡፡ በአባቶች የተመሰለውን ምሳሌና በነቢያት የተነገረውን ትንቢት አመሥጥሮና አራቅቆ የተረጎመ ሊቅም ነው፡፡ በመሆኑ ነገረ ድኅነትን በተናገረበት ምስጋናው “በመካከላችን ሆኖ በመስቀሉ አስታረቀን፤በልዩ ትንሣኤውም ሰውን ዳግመኛ ወደ ገነት መለሰው” የሚለውን ኃይለ ቃል እናገኛለን፡፡

ከዕለተ ትንሣኤ እስከ ዳግም ትንሣኤ

ከዕለተ ትንሣኤ እስከ ዳግም ትንሣኤ ባሉት ዕለታት በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የሚፈጸመው መንፈሳዊና ሐዋርያዊ አገልግሎት ልክ እንደ መጀመሪያው የትንሣኤ ሥርዓት ኾኖ ይከናወናል፡፡ ከትንሣኤ እሑድ ጀምሮ እስከ ሳምንቱ እሑድ ድረስ የሚገኙት ዕለታትም ‹ሰሙነ ፋሲካ› ወይም ‹ትንሣኤ› እየተባሉ ይጠራሉ፤ የየራሳቸው ምሥጢራዊ ስያሜም አላቸው፡፡

ዓርብ ስቅለት (የድኅነት ቀን)

ዓርብ ስቅለት የዕዳ ደብዳቤያችን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ለመጨረሻ ጊዜ የተደመሰሰበት፤ ከአጋንንት አገዛዝ ነጻ የወጣንበት ዕለት ስለኾነ ‹የድኅነት ቀን› ይባላል፡፡

ጸሎተ ሐሙስ

ጸሎተ ሐሙስ በብሉይ ኪዳን ለፋሲካ ዝግጅት ተደርጎበታል (ማቴ. ፳፮፥፯-፲፫)፡፡ ‹ፋሲካ› ማለት ማለፍ ማለት ነው፡፡ ይኸውም እስራኤላውያን በግብጽ ምድር ሳሉ መልአኩን ልኮ እያንዳንዱ እስራኤላዊ የበግ ጠቦት እንዲያርድና ደሙን በበሩ ወይም በመቃኑ እንዲቀባ ለሙሴ ነገረው፡፡ ሙሴም የታዘዘውን ለሕዝቡ ነገረ፤ ሁሉም እንደ ታዘዙት ፈጸሙ፡፡ በኋላ ከእግዚአብሔር ዘንድ መቅሠፍት ታዞ መልአኩ የደም ምልክት የሌለበትን የግብጻውያንን ቤት በሞተ በኵር ሲመታ፤ የበጉ ደም ምልክት ያለበትን የእስራኤላውያንን ቤት ምልክቱን እያየ አልፏል፡፡ ፋሲካ መባሉም ይህን ምሥጢር ለማስታወስ ነው (ዘፀ. ፲፪፥፩-፳)፡፡

ሆሳዕና

ሆሼዕናህ ከሚል ከዕብራይስጥ ቃል የተገኘው ሆሳዕና ትርጓሜው እባክህ አሁን አድን ማለት ነው፡፡ ይህ ቃል በዘመነ ብሉይ በቀደምት ነቢያት ዘንድ የተለመደ ቃል ነው፡፡ አቤቱ እባክህ አሁን አድን፣ አቤቱ እባክህ አሁን አቅና፣ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ ቡሩክ ነው፡፡ (መዝ.፻፲፯፥፳፭-፳፮) የሆሳዕና በዓል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ የሚቀድሙትና የሚከተሉት ሕዝብ በተለይም አእሩግና ሕፃናት ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ፣ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፣ ሆሳዕና በአርያም በማለት ጌታችንን በክብር መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል ነው፡፡ በዓሉም ሆሳዕና የሚለውን ስያሜ ያገኘው በዕለቱ ከተዘመረው መዝሙር ነው፡፡

ኒቆዲሞስ

በመዘነ ሥጋዌ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ምደር መምጣትና መሲሕ መባል ያልተቀበሉት በርካታ እስራኤላዊያን እርሱን እስከመስቀል እንደደረሱ ወንጌል አስተምሮናል፡፡ ሆኖም በፍጹም እምነት እስከ መጨረሻው ከተከተሉት ፈሪሳውያን አንዱ ኒቆዲሞስ ለታላቅ ክብር የበቃ ሰው ነው፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይህን ታላቅ ሰው ለመዘከር የዐቢይን ጾም ሰባተኛ እሑድ በስሙ ሰይማ ታከብረዋለች፤ ተከታዮቿ ምእመናንም የእርሱን አሠረ ፍኖት እንዲከተሉ ትመክራለች፤ ታስተምራለችም፡፡

“እናንተ ኃጢአተኞች እጃችሁን አንጹ፤ እናንተ በሁለት ሀሳብ የምትዋልሉ ልባችሁን አጥሩ” (ያዕቆብ ፬፥፰)

አሁንም ይህ መቅሰፍት የእግዚአብሔር ቁጣ መሆኑን ማመን የማይፈልጉ እና የማያምኑ ሰዎች በርካታ ናቸው፤‹‹ስለዚህ ቍጣዬን አፈሰስሁባቸው፥ በመዓቴም እሳት አጠፋኋቸው፤ መንገዳቸውንም በራሳቸው ላይ መለስሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር›› እንዲል። (ሕዝ. ፳፪፥ ፴፩) እነርሱ ፈውሰ ሥጋም ሆነ ነፍስ እግዚአብሔር መሆኑን ዘንግተውታል፤ ድኀነተ ሥጋም ሆነ ድኅነተ ነፍስ የሚገኘው ግን ከፈጣሪ ዘንድ ነው፡፡

“ከእነዚህ ሥራዎችም ሰውነታችሁን ብትጠብቁ በሰላም ትኖራላችሁ” (ሐዋ.፲፭፥፳፰)

ሐዋርያት በወቅቱ ደቀ መዛሙርቱን የላኳቸው መልእክት እንዲህ የሚል ነበር። “ሥርዓት እንዳናከብድ፤ ሌላም ሸክም እንዳንጨምር መንፈስ ቅዱስ ከእኛ ጋራ ነውና ነገር ግን ይህን በግድ ትተው ዘንድ እናዝዛችኋለን። ለአማልክት የተሠዋውን፣ ሞቶ የተገኘውን፣ ደምንም አትብሉ፤ ከዝሙትም ራቁ፤ በራሳችሁ የምትጠሉትንም በወንድሞቻችሁ ላይ አታድርጉ፤ ከእነዚህ ሥራዎችም ሰውነታችሁን ብትጠብቁ በሰላም ትኖራላችሁ”፡፡(ሐዋ.፲፭፥፳፰-፳፱)፤ሐዋርያት ለሕዝቡ ከመጨነቃቸው የተነሣ “ሥርዓት እንዳናከብድ ሌላም ሸክም እንዳንጨምር መንፈስ ቅዱስ ከእኛ ጋር ነውና” በሚል መልእክቱን ልከዋል፡፡ ዛሬም ቅዱስ ሲኖዶስ የሚያስተላልፈውን መመሪያ መስማት ከምእመናን ይጠበቃል። በምእመናን ላይ ሥርዓት እንዳይከብድ፣ ምእመናኑ በመጣው መዓት እንዳይደናገጡ፣ ባልጸና እምነታቸው የመጣውን መዓት መቋቋም ተስኗቸው ከቤቱ እንዳይወጡ በማዘን ነውና ቃላቸውን ሊሰማ ይገባል።