ማእከላት ለኦዲትና ኢንስፔክሽን ሥራዎች ትኩረት እንዲሰጡ ተጠየቀ

ሚያዚያ 22 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደጀኔ

የማኅበረ ቅዱሳን ኦዲትና ኢንስፔክሽን አገልግሎት ክፍል ማእከላት ለኦዲትና ኢንስፔክሽን ሥራዎች ትኩረት እንዲሰጡ የክፍሉ ሓላፊ አቶ የሸዋስ ማሞ አስታወቁ፡፡

በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ለሀገር ውስጥ ማእከላት ስለ ኦዲትና ኢንስፔክሽን አገልግሎትና አሠራር ዙሪያ ሚያዝያ 12 እና 13 ቀን 2005 ዓ.ም. በተሰጠበት ወቅት ነበር ማእከላት አገልግሎቱን አጠናክረው መቀጠል የሚገባቸው መሆኑን የተገለጸው፡፡

ማእከላት የሒሳብ ክፍል አሠራራቸውንና የኦዲትና ኢንስፔክሽን ክፍሎቻቸውን ይበልጥ  አጠናክረውና በሰው ኃይል አደራጅተው አገልግሎታቸውን መቀጠል እንዳለባቸው በሥልጠናው ላይ ተገልጿል፡፡

ለማእከላት በርካታ ሥልጠናዎችና የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን የማእከላቱ የግንዛቤ መጠን መጠነኛ ለውጦችን ማምጣት መቻሉን አቶ የሸዋስ ገልጸው ማእከላቱ ለኦዲትና ኢንስፔክሽን ሥራዎች ትኩረት እንዲሰጡና ክፍሉንም በባለሙያ እንዲያጠናክሩ ጥሪያቸውን ያቀረቡት፡፡ የአገልግሎት ክፍሉ እና የሒሳብ ክፍሉ መጠናከር የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚኖረውና ለማእከላት ወጥ የሆነ የሒሳብ አያያዝ ሥርዓትም አዎንታዊ ተጽዕኖ ሊኖረው እንደሚችል አስገንዝበዋል፡፡

የአገልግሎት ክፍሉ የማኅበሩን ስልታዊ ዕቅድ ከማስፈጸም አኳያ የተለያዩ ድጋፎችን ለማእከላት የሚያደርግ መሆኑና በዕቅዱም ዘመን የራሱን የአገልግሎት ስልት ዘርግቶ እንደሚሠራ ነው ከሓላፊው ገለጻ የተረዳነው፡፡ ሚያዝያ 12 እና 13 ቀን 2005 ዓ.ም. በተሰጠው ሥልጠና በሀገር ውስጥ ከሚገኙ ማእከላት ተወካዮች በሥልጠናው መሳተፋቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚማሩ አባላት መንፈሳዋ ጉዞ አካሄዱ

ሚያዚያ 21 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዳዊት ደስ

የማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል “መራሔ ፍኖት” በሚል መሪ ቃል በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እየተማሩ ላሉ የቤተ ክርስቲያን ልጆች መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ሱሉልታ ደብረ ምሕረት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሚያዚያ 20 ቀን 2005 ዓ.ም. አካሄደ፡፡

የጉዞውን ዓላማ አስመልክቶ አስተባባሪ የሆነው ሸዋለም ተክሉ ከዚህ ቀደም በግቢ ሲማሩ የነበሩ ተሞክሮአቸውን የሚያካፍሉበት፣ ተማሪዎች መንፈሳዊም ሆነ በሚማሩት ትምህርታቸው ያለባቸውን ጥያቄ የሚመለስበትና የክርስትና ሃይማኖት ተከታይ ሆነው ወደ ግቢ የማይመጡትን ተማሪዎችን በግቢ እየመጡ እንዲማሩ ለማድረግ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

አያይዘውም ይህ የግቢ ጉባኤ አንድነት መርሐ ግብር ለአራተኛ ጊዜ የተካሄደ ሲሆን ከጉዞው የሚጠበቀው ውጤት በመንፈሳዊ ሕይወታቸው የዛሉ የመንፈስ ብርታት የሚያገኙበት፣ የግቢያት የአባላት ቁጥር ወደተሻለ እድገት እንዲመጣ ለማድረግ ነው ሲሉ አስተባባሪው ተናገረዋል፡፡

በዕለቱ በግቢ ጉባኤ ተማሪዎችና በዘማርያም መዝሙር ቀርቢል፣ ትምህርተ ወንጌል የተሰጠ ሲሆን ግቢያቱ በተለያየ ርዕሰ ጉዳይ የተጠየቁ ጥያቄች ምላሽ ተሰጥተውባቸዋል፡፡ በመርሐ ግብሩ ሲሳተፉ ያገኘናቸው ወጣት ዮዲት ተገኔ የሮያል ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተማሪ ስትሆን በዚህ ጉዞ ለመጀመሪያ ጊዜዬ ነው የተጓዝኩት፡፡ ጉዞው ትልቅ ነገር አስተምሮኛል፡፡ የሌሎችን ግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ጋር አስተዋውቆኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ እየተሠራ ያለውን ተግባር እንዳይ አድርጎኛል በማለት ገልጻለች፡፡

ሌላው የ5 ኪሎ ግቢ ጉባኤ ተማሪ የሆነው ናትናኤል ስዮም በጉዞው በመሳተፌ በውስጤ ይመላለስ የነበሩብኝ ጥያቄዎች ተመልሰውልኛል፡፡ እንደዚህ አይነት መርሐ ግብሮች ወጣቱን የሚያንፁ ስለሆነ ማኅበሩ አጠናክሮ ሊሠራበት የሚገባ ተግባር ነው፡፡ ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡ በጉዞው ላይ ከ60 በላይ ከሚሆኑ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የመጡ ከሁለት ሺህ በላይ ተጓዦች ተሳትፈዋል፡፡

አትማረኝ ዋሻ

ሚያዚያ 18 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

 

/ጸበል ጸዲቅ ክፍል አምስት/

“አትማረኝ” እያሉ ስለ ጸለዩ አባት የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት በትምህርታቸው እያነሱ በምሳሌነት ከሚጠቅሷቸው ትምህርቶች አንዱ ነው፡፡ ከጣና ሐይቅ ጉዞ ከቃረምኳቸው መረጃዎቼ መካከል ለዛሬ  በጸበል ጸዲቅ ጽሑፌ አትማረኝ ዋሻንና ታሪኩን በጥቂቱ ላስተዋውቃችሁ፡፡

አትማረኝ ዋሻ በጣና ሐይቅ ደሴቶች መካከል ከሚገኙ ገዳማት መካከል ከማን እንደ አቡነ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም በስተ ምእራብ አቅጣጫ የጣና ሐይቅን ጉዞ ከገታው አንደ ተራራ ሥር የሚገኝ ዋሻ ነው፡፡

ከብርጊዳ ማርያም ገዳም ወደ ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም ገዳም በጀልባ እየተጓዝን አብረውን ከነበሩት ደብረ ሲና ማርያም ገዳም መነኮሳት መካከል አንዱ አባት ጣታቸውን ወደ ምእራብ አቅጣጫ ወደ አንድ ዋሻ እያመለከቱ፡፡ “ያ ተራራ ይታያችኋል? ከተራራው ሥር የሚገኘው ዋሻስ?!” አሉን፡፡

ሁላችንም አባታችን በጣታቸው ወደሚጠቁሙት አቅጣጫ ተመለከትን፡፡ በርቀትም ቢሆን ዋሻውን ተመለከትን፡፡ የጋዜጠኝነት ጆሮዎቻችን ተቀሰሩ፡፡ለመስማት ጓጓን፡፡

“በዚህ በምትመለከቱት ዋሻ ውስጥ ለብዙ ዘመናት አንድ አባት የጸሎት በዐት አድርገውት “አትማረኝ” እያሉ የጸለዩበት ቦታ ነው” አሉን፡፡

ይህንን ታሪክ ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም ገዳም እንደደረስን ለማጣራት ጥረት ያደረግን ሲሆን የገዳሙ አባቶች የአቡነ ያሳይ ገድልን መሠረት አድርገው የታሪኩ ትክክለኛነት አረጋግጠውልናል፡፡ ታሪኩንም አሳጥሬ ላቅርብላችሁ፡፡

አቡነ ያሳይ ከሰባቱ የአቡነ መድኀኒነ እግዚእ ደቀመዛሙርት መካከል አንዱ ናቸው፡፡ ወደ ጣና ደሴት ከአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ እና አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ጋር በመሆን በጸሎት ይተጉ እንደነበር ገድላቸው ይናገራል፡፡ ከእግዚአብሔር በተሰጣቸውም ጸጋ በጣና ሐይቅ ላይ እንደ ጀልባ የሚጓዙበት አንድ ጠፍጣፋ ድንጋይ /ዛሬም ድረስ በገዳማቸው ውስጥ ይገኛል፡፡/ በጣና ደሴት ላይ ለአገልግሎት በመፋጠን ላይ እያሉ ዛሬ አትማረኝ ዋሻ ተብሎ ወደሚጠራው አካባቢ ሲደርሱ አንድ አባት ዋሻው ውስጥ “አትማረኝ – አትማረኝ- አትማረኝ” እያሉ ሲጸልዩ ያገኟቸዋል፡፡

አቡነ ያሳይ በሰውዬው ጸሎት በመገረም ቀርበዋቸው “አባቴ ምን ዓይነት ጸሎት ነው የሚጸልዩት?” አሏቸው፡፡

“አባቴ እንደ እርስዎ ያሉ አባት መጥተው “አትማረኝ” እያልክ ጸልይ ብሎኝ ነው በማለት መለሱላቸው፡፡

“እንዲህ ዓይነት ምክር የሚመክር ጠላት ዲያብሎስ ነው፡፡ ከዛሬ ጀምረው “ማረኝ” እያሉ ይጸልዩ በማለት አቡነ ዘበሰማያትን አሰተምረዋቸው ይሄዳሉ፡፡

አትማረኝ እያሉ ይጸልዩ የነበሩት አባትም “ማረኝ” እያሉ መጸለያቸውን ቢቀጥሉም ብዙ መግፋት ሳይችሉ ጸሎቱ ይጠፋባቸዋል፡፡ ጸሎቱን ያስጠኗቸው አባት አቡነ ያሳይ ርቀው ሳይሄዱባቸውም በውኃ ላይ እየተራመዱ በመከተል ይደርሱባቸዋል፡፡

“አባታችን ያስጠኑኝ ጸሎት ጠፋብኝ፡፡ እባክዎ ያስተምሩኝ” ይሏቸዋል፡፡

አቡነ ያሳይ የእኚህ አባት መብቃት ተመልከተው “አባቴ እግዚአብሔር የልብ ነውና የሚመለከተው እንዳስለመዱት ይጸልዩ የእርስዎ ይበልጣል” ብለዋቸው ይሔዳሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ቦታው አትማረኝ ዋሻ ተብሎ ተጠርቷል፡፡

ይቆየን
 

ቅዱስ ፓትርያርኩ ከማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጋር ልዩ ቃለ መጠይቅ አደረጉ

ሚያዚያ 17 ቀን 2005 ዓ.ም.


 abune matyas 17

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ከማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጋር በዓለ ትንሣኤን ምክንያት በማድረግ ልዩ ቃለ መጠይቅ አደረጉ፡፡ በዚህ አንድ ሰዓት የፈጀ ቃለ መጠይቅ ላይ ቅዱስነታቸው ስለ ልጅነት ጊዜያቸው ፣ በትምህርት ቤት ሳሉ ስለነበሯቸው ገጠመኞች ፣ ስለ ምንኩስና ሕይወት፣ በቤተ ክርስቲያኒቱ ስላሉ ልዩ ልዩ አስተዳደራዊና ችግሮች እና በተሠጣቸው ሓላፊነት ምን ሊሠሩ እንዳሰቡ ፣ ስለ ቅድስት ሀገር የርስት ጉዳይ ከግብፅ ቤተ ክርስቲያን ጋር ለመሥራት ስለታሰበው መፍትሔ እና ስለ ዕርቀ ሰላሙ ጉዳይ ሰፋ ያለ ማብራሪያ የሠጡ ሲሆን ሙሉ ቃለ መጠይቁ በማኅበሩ የቴሌቪዥን መርሐ ግብር ከበዓለ ትንሣኤ ጀምሮ እንደሚቀርብ የማኅበሩ ሬድዮና ቴሌቪዥን ክፍል አስተባባሪ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ገልጸዋል፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን በኢቢኤስ ቴሌቪዥን መርሐ ግብር ከተጀመረበት የካቲት ፲፮ ፳፻፭ ጀምሮ እስከ በዓለ ትንሣኤ ድረስ ዐሥር ልዩ ልዩ መርሐ ግብራትን ያስተላለፈ ሲሆን የተጀመረበትን ሰዓት በማስተካከልም መርሐ ግብሩ ዘወትር እሑድ ከ5፡30 – 6፡00 ሰዓት ድረስ ሆኗል፡፡ የተላለፉ ዝግጅቶችም በኢንተርኔት http:// eotc.tv ላይ በማንኛውም ሰዓት መከታተል ይቻላል፡፡ ዝግጅቶቹን በመመልከት በስልክና በኢንተርኔት አድራሻዎቻችን ገንቢ አስተያየቶቻችሁን የሠጣችሁን ምዕመናንን እያመሰገንን ለበለጠ ሥራ ረድኤተ እግዚአብሔር እንዳይለየን ጸልዩልን ሲሉ የክፍሉ አስተባባሪ ገልጸዋል፡፡  

hosaena

ሆሣዕና(ለሕፃናት)

ሚያዚያ 17 ቀን 2005 ዓ.ም.

በቤካ ፋንታ

hosaenaበኢየሩሳሌም ሀገር ውስጥ በምትገኝ በአንድ ትንሽ መንደር ውስጥ ነው የምኖረው፡፡ ከተወለድኩ ዛሬ 5 ዓመት ሞልቶኛል፡፡ ቀኑ ሰንበት ነው እቤት ውስጥ እየተጫወትኩ እናቴም በጓዳ ሥራ እየሠራች ድንገት የብዙ ሰዎች የእልልታ ድምጽ ሰፈሩ ውስጥ ተሰማ፡፡ እናቴም በፍጥነት ከጓዳ ሮጣ ወጥታ “ልጄ ልጄ ነይ እንሂድ ብላ በጀርባዋ ላይ አዝላኝ ሮጣ ከቤት ወጣች፡፡ እኔም በሁኔታው ተገርሜያለሁ፡፡

በሰፈር ውስጥ ያሉ ጓደኞቼ ሁሉ በእናታቸው ጀርባና በአባታቸው ትከሻ ላይ ሆነው ደስ ብሏቸው እንደ ወላጆቻቸው እልል ይላሉ፡፡ ወላጆቻችን ሁሉ ተሰብስበው ከሰፈራችን መውጫ ጋር ወዳለ ትልቅ የዘንባባ ዛፍ ተያይዘው አመሩ፡፡ ከዚያም የዘንባባ ዝንጣፊውን እየቆረጡ ሁሉም ያዙ ለእኛም ሰጡን፡፡ ከዚያ እልል እያልን በደስታ ወደ ቤተ መቅደስ እሮጥን፡፡
በመንገድ ላይ በጣም ብዙ ሕዝብ አየሁኝ ሁሉም ደስ ብሏቸው እነርሱም እንደኛ ወደ ቤተ መቅደስ ይሮጣሉ፡፡ የሕፃናቶቹን ብዛት ሳይ ውስጤ በጣም ደስ አለው፡፡ የገረመኝ ደግሞ የሚያለቅስ ልጅ አንድ እንኳን የለም፡፡ “ዛሬ የኛ የደስታና የዝማሬ ቀን ነው” ማለት ነው ብሎ ልቤ በደስታ ፈነደቀ፡፡

ወደ ቤተ መቅደስ ለመድረስ ጥቂት መንገድ ሲቀረን በርቀት ወደ ቤተ መቅደሱ የሚጓዙ በጣም በጣም ብዙ ሕዝብ ተመለከትኩኝ፡፡ እንደኛ እነርሱም ዘንባባ ይዘዋል፡፡ በመካከላቸው አንድ ትልቅ አህያ አየሁኝ፣ ከአህያይቱም ጋር ልጇ ውርንጫዋ አለች፡፡ የሚያማምር ልብስ በአህያዎቹ ጀርባ ላይ ተነጥፏል፡፡ በውርንጫዋም ላይ የሁላችን ፈጣሪ፣ ንጉሣችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተቀምጦ ስመለከት በደስታ ዘለልኩኝ፡፡ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር መሆን በጣም ያስደስታል፡፡

ምክንያቱም እኛ ሕፃናትን ሲያይ ደስ ይለዋል፡፡ እቅፍ አድርጎ ስሞን በጉልበቱ ላይ ቁጭ አድርጎን ያስተምረናል፣ ይመክረናል፡፡ በዙሪያውም ላሉት ሰዎች እንደነዚህ ሕፃናት ንጹሃን ሁኑ፣ ኀጢአት አትሥሩ፣ እነርሱ አይዋሹም፣ እያለ ይመክራቸዋል፡፡

ከዚያ ምን ሆነ መሰላችሁ፤ እልል እያለ የሚያመሰግነው ሕዝብና በእናትና በአባቶቻችን እቅፍ ውስጥ ያለነው ሕፃናት በአንድነት ሆነን ጮክ ብለን የዘንባባውን ቅጠል ወደ ቀኝ ወደ ግራ፣ ወደ ቀኝ ወደ ግራ እያውለበለብን መዝሙር መዘመር ጀመርን፡፡ መዝሙሩም እንዲህ የሚል ነው፡፡ “ሆሣዕና በአርያም ለዳዊት ልጅ፤ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም፣ ሆሣዕና በአርያም፣ ሆሣዕና በአርያም” የመዝሙሩ ድምጽ በኢየሩሳሌም ከተማ ከጫፍ እስከ ጫፍ ተሰማ፡፡ በጣም ደስ ያለኝ ደግሞ የእኛ የሕፃናቱ ድምጽ ከትልልቆቹ በልጦ መስማቱ ነው፡፡ ጌታችንን በአህያዋ ላይ ተቀምጦ ባየሁት ጊዜ ትዝ ያለኝ አባዬ መጽሐፍ ቅዱስ እያነበበ ያስተማረኝን ታሪክ ልንገራችሁ “አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ እጅግ ደስ ይበልሽ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ እልል በይ እነሆ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው ትሑትም ሆኖ በአህያም፣ በአህያይቱ ግልገል በውርንጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል” ት.ዘካ.9፥9፡፡

የዝማሬውን ድምጽ ሲሰሙ አባታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወዱት እና የሚያሳድዱት በከተማው ውስጥ ያሉ ጨካኝ ሰዎች እኛ ተሰብስበን እየዘመርን ወደአለንበት መጡ፡፡ ሲመለከቱ ሕዝቡ ሁሉ ደስ ብሏቸው እየዘመሩ እልል እያሉ የዘንባባውን ቅጠል እያውለበለቡ ኢየሱስ ክርስቶስን በአህያዋ ውርንጫ ላይ አስቀምጠው እያመሰገኑት ወደ ቤተ መቅደስ ሲሄዱ ተመልክተው ጨካኞቹ ሰዎች በጣም ተናደው ሕዝቡን “ዝም በሉ” ብለው ተቆጧቸው፡፡ ትልልቆቹ ሁሉ ፈርትው ዝም አሉ፡፡

እኔና ጓደኞቼ ግን በእናታችን ጀርባ ላይ ካሉት ሕፃናት ጋር አብረን ሆነን ጮክ ብለን “ሆሣዕና በአርያም” የሚለውን መዝሙር መዘመር አላቆምንም ነበር፡፡ የገረመኝ ደግሞ ከእኔ የሚያንሱት ገና የተወለዱትም ሕፃናት መዝሙሩን ጮክ ብለው ሲዘምሩት በመስማቴ ነው፡፡ “እግዚአብሔር ሆይ መናገር የማንችለውን እኛን እንድንዘምርልህ ስለፈቀድክልን ተመስገን፡፡” ብዬ አመስግኜ መዝሙሩን መዘመር ቀጠልኩኝ “ሆሣዕና፣ ሆሣዕና፣ ሆሣዕና በአርያም….”

እነዚህ ጨካኞቹ ሰዎች ግን እናትና አባቶቻችንን ዝም አስብሏቸው ብለው ሲያስፈራሩዋቸው ወላጆቻችን ፈርተው የሁላችንንም አፋችንን ይዘው ዝም አስባሉን፡፡ አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያዋ ውርንጫ (በትንሿ አህያ) ላይ ቁጭ ብሎ ለጨካኞቹ ሰዎች እንዲህ አላቸው “ከሕፃናት ከሚጠቡት አፍ ምስጋናን ለራሴ አዘጋጅቻለሁ፡፡ የእነርሱንም አፍ ይዛችሁ ዝም ብታስብሏቸው በዙሪያዬ ያሉት ድንጋዮች ያመሰግኑኛል፡፡ የፈጠርኳችሁ ድንጋዮች ሆይ ሕፃናት እንደዘመሩ እናንተም በመዝሙር አመስግኑኝ፡፡” በማለት በታላቅ ድምጽ ሲናገር፤ ትልልቁም ድንጋይ፣ ትንንሹም ድንጋይ ከመሬት ወደ ላይ እየተነሡ “ሆሣዕና በአርያም ለዳዊት ልጅ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቀርባለን ምስጋና…” እያሉ በጣም ደስ በሚል ድምጽ መዘመር ጀመሩ፡፡ በዚህን ጊዜ ጨካኞቹ ሰዎች አፍረውና ፈርትው ሄዱ፡፡

እኛም ወላጆቻችንም በዙሪያችንም ያሉትም ድንጋዮች አምላካችንን ከበን በእልልታ እየዘመርን ለአህያዎቹ መርገጫ ልብሳችንንና የዘንባባውን ዝንጣፊ እያነጠፍን ወደ ቤተ መቅደስ ገባን፡፡ በዚያም ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደስ የሚል ትምህርት አስተማረን፡፡

በመጨረሻም ሆሣዕና ብለን ምስጋና ላቀረብነውና በቤተ መቅደስ ተገኝተን ቃሉን ለምንሰማው ሕፃናት እንዲህ ብሎ መከረን “ልጆቼ በመዝሙራችሁ ተደስቻለሁ፣ ሁል ጊዜ ወደ ቤቴ ወደ ቤተ ክርስቲያን ኑና ዘምሩልኝ፡፡ አፋችሁ በመዝሙር ይዘምር እንጂ ዘፈን እንዳይዘፍን አደራችሁን፡፡ ዘፈን መዝፈን ኀጢአት ነው፡፡”

ትምህርቱን ጨርሰን ከእናቴ ጋር ደስ እያለን ወደ ቤት ተመለስን፡፡ ታዲያ ሁል ጊዜ ይህችን የሆሣዕናን በዓል በውስጤ አስባታለሁ፣ መዝሙሩን መዘመር በጣም ያስደስተኛል፡፡ አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስ በመጨረሻ የመከረኝንም ምክር ጠብቄ ዘፈን የሚባል በአፌ ሳልዘፍን መዝሙር እየዘመርኩኝ እግዚአብሔርን እያመሰገንኩኝ አደኩኝ፡፡

ልጆችዬ ዛሬ የምታነቡት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የሚሆነው ማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 21 እስከ ቁጥር 16 እና ማርቆስ ወንጌል ምዕራፍ 11 ከቁጥር 1 እስከ 17 ያለውን ይሆናል፡፡ ሆሣዕና በአርያም ብለን እንድናመሰግነው ኀይሉን የሰጠን እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን አሜን፡፡፡

tana desate

ቤተ ክርስቲያን ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ

ሚያዚያ 15 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

ጸበል ጸዲቅ /ክፍል አራት/

tana desateከጎንደር ከተማ በጎርጎራ ወደብ አድርገን ልንቃኛቸው በመረጥናቸው አምስት የጣና ሐይቅ ገዳማትን ለመዘገብ የተነሳነው ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ነው፡፡ የጀልባ ላይ ጉዞ አድርጌ አላውቅም፡፡ ነገር ግን ቅዱሳን አበውን ያፈሩ፤ በጾም በጸሎት፤ በተጋድሎ የጸኑባቸው ገዳማትን በረከት ለማግኘት፤ ታሪካቸውን ለመቃኘት ቸኩያለሁ፡፡ የጋዜጠኞቹ ቡድን በአንድነት ሆነን የ64 ኪሎ ሜትሩን መንገድ ተያያዝነው፡፡

አመሻሽ ላይ ጎርጎራ ወደብ ደረስን፡፡ የጠዋት ጉዟችንን ለማመቻቸት እንዲረዳን ወደቡ ላይ ከሚገኘው የደብረ ሲና ቅድስት ማርያም ገዳም የአባቶችን ፈቃድ በመጠየቅ የምንፈልገውን መረጃ ማሰባሰባችንን ቀጠልን፡፡ በምፈልገው አቅጣጫ ጥያቄዎችን እየጠየቅን፤ ምላሽ ከአባቶች እየተሰጠን አመሸን፡፡ አዳራችንንም እዚያው አደረግን፡፡

በጠዋት ተነስተን አንጋራ ተክለ ሃማኖት ገዳምና ብርጊዳ ቅድስት ማርያም ገዳምን ቃኝተን  ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም ስንደርስ በመምሸቱ አስፈላጊ ናቸው ያልናቸውን መረጃዎች ስናሰባስብ አደርን፡፡ በማግስቱም ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ ገዳም ዘልቀን እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ላይ ከተምን፡፡

የዛሬው የጸበል ጸዲቅ ጽሑፌ እንደ ሰሞኑ ታሪክ ላይ ያተኮረ አይደለም፡፡ በጉዟችን የቃኘናቸው የአባቶቻችን አሻራ ያረፈባቸው፤ እግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ የስልጣኔ ጫፍ የደረሰ አእምሯቸው ውጤቶች በነበሩ ነገር ግን የተፈቱና ለመፈታት በቋፍ ላይ የሚገኙት ጥንታዊ የጣና ደሴት በረከቶችን እንቃኝ ዘንድ ወደድኩ፡፡ ክፍል አራት ጸበል ጸዲቅን ተቃመሱ፡፡

አንጋራ አቡነ ተክለ ሃማኖት ገዳም፡-
angawa tekelehaymanoteአንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ለመድረስ ከደብረ ሲና ማርያም ገዳም የ20 ደቂቃ በጀልባ  የጣና ሐይቅን ማቋረጥ ይጠይቃል፡፡ በደብረ ሲና ማርያም ገዳም አገልጋይ የሆኑት ሁለት መነኮሳት አባቶች ወደ ማን እንደ አባ አቡነ ያሳይ መድኀኔዓለም ገዳም ስለሚሔዱ እንድናደርሳቸው ስለጠየቁን አብረን ለመጓዝ ተስማምተን ጸሎት አድርገውልን የጣና ሐይቅ የጀልባ ላይ ጉዞ ተጀመረ፡፡ 

አንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ስንደርስ ያልጠበቅነው ነገር ገጠመን፡፡ በድንጋያማው ደሴት ላይ ያረፈው ቤተ መቅደስ በዝምታ ተውጧል፡፡ አፍ አውጥቶ “የሰው ያለህ” በማለት የሚጣራ ይመስላል፡፡ በአካባቢው ሰው ዘር ያለ አይመስልም፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ስንጠጋ አንዲት ደሳሳ ጎጆ ቤት ደጃፍ ላይ አንድ አባት እድሜ ተጭኗቸው ኩርምት ብለው ተቀምጠዋል፡፡ ዓይነ ሥውር ናቸው፡፡ ዘጠና ዓመታቸው ሲሆን ወደ አንጋራ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ከመጡ 25 ዓመታታን አስቆጥረዋል፡፡

“አባታችን ስለዚህ ገዳም ታሪክና አሁን ያለበት ሁኔታ የሚነግረን ሰው እናገኝ ይሆን?” የሁላችንም ጥያቄ ነበር፡፡

“የምን ሰው?! ማን አለ ብላችሁ ነው?! ገዳሙ ሊፈታ ምንም አልቀረውም፡፡ እስቲ ወደ ታች ወረድ ብላችሁ ገበዙን ፈልጉት” አሉን፡፡

ውስጤ መረበሽ ጀመረ፡፡ ማንን እንጠይቅ? የኢየሩሳሌምን ጥፋት አታሳየኝ ያለውና እንደ ቃሉም የተፈጸመለት አቤሜሌክን አስታወስኩ፤፤ ከጓደኞቼ ገንጠል ብዬ የሚተናነቀኝን የቁጭት እንባ አፈሰስኩ፡፡ ቤተ መቅደሱ ላይ ዓይኖቼ እንደተተከሉ አባቶችን አሰብኩ፡፡ አባቶቻችን ይህንን ገዳም ሲገድሙት ምን ይመስል ነበር? በገዳማውያን አባቶች ተሞልቶ፤ መላእክትን መስለው እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑበት፤ በጸሎት አጋንንት ድል ሲነሱበት የነበረ፤ ቃል ኪዳን የተቀበሉበት ሥፍራ ምነው ዛሬ ነጠፈ?! ራሴንና ይህንን ትውልድ ተጠያቂ ከማድረግ ሌላ ምን ማለት እችላለሁ? አባቶቻችንን መስለን ያልተገኘን፤ የአባቶቻችን አደራ መሸከምም ሆነ መወጣት ያቃተን ትውልዶች እንደሆንን ተሰማኝ፡፡ ብቻዬን መሆን አማረኝ፡፡ ነገር ግን አልቻልኩም እንደተከፋሁ ከጓደኞቼ ጋር ተቀላቀልኩ፡፡ እንደ እኔው በዝምታ ቆዝመዋል፡፡ 

የቤተ ክርስቲያኑን ገበዝ ከእኛ ጋር ከደብረ ሲና ቅድስት ማርያም ገዳም የመጡት መነኮሳት አባቶች ፈልገው ይዘዋቸው መጡ፡፡ በእርግና እድሜ ላይ ነው የሚገኙት፡፡ ደብዳቤያችንን አሳይተን መረጃ እንዲሰጡን ጠየቅናቸው፡፡ ታሪኩን በተደራጀ መልኩ መናገር ተሳናቸው፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን ቅድስት ቤተ ክርስተቲያንን ለትውልድ ይተላለፍ ዘንድ የከፈሉት መስዋእትነት እንደዋዛ ፈዛዛ ማለፉ ነው፡፡ ገዳሙ የእምነታችን መገለጫ የሆኑትን የአባቶቻችንን ታሪክና ቅርሶችን ታቅፎ ዝምታን መምረጡ ለምን ይሆን? ለመሆኑ ተጠያቂው ማነው? ውስጤን ሰላም ነሳኝ፡፡ 

አገልጋዮቹ ከሦስት አይበልጡም፡፡ ቅዳሴ አይታሰብም፡፡ ከቀናቸው ኪዳን ያደርሳሉ፡፡ ካልሆነም በግል ጸሎት ይተጋሉ፡፡ የሚተካቸው የለም፡፡ ይህ ትውልድ ርቋቸዋል፡፡ አባቶቻችንን መምሰል፤ በቃልኪዳናቸው መጠቀምን ዘንግተን ይሆን? የወደፊት የእኛም ሆነ የተፈቱ ገዳማት እጣ ፈንታ ምን ይሆን? የቃረምነውን መረጃ ቋጥረን፤ በሐዘን አንገታችንን እንደደፋን ወደ ጀልባችን አመራን፡፡ ጉዞ ወደ ብርጊዳ ቅድስት ማርያም ገዳም፡፡

ብርጊዳ ማርያም ገዳም፡-
ወደ ብረጊዳ ማርያም ገዳም እያመራን ደሴት ስንመለከት ይህ ምንድነው ማለታችን አልቀረም፡፡ አብረውን ያሉት አባቶች ከእኛ የተሻለ መረጃ ስላላቸው የሰቀላ ሚካኤልን፤ የቅዱስbergeda mariyame ጊዮርጊስንና የእመቤታችን ማርያም የጥንት ገዳማትን በጣታቸው እያሳዩን አለፍን፡፡ ሦስቱም ገዳማት ተፈትተው ዛሬ ሰው አልባ ሆነዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያኖቹም ፈርሰዋል፡፡ በምሰማው ነገር ታመምኩ፡፡ 

ብርጊዳ ማርያም ገዳምን  ከአንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ብዙም የተሻለ ነገር አለው ለማለት አያስደፍርም፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ክብ ሲሆን ዙሪያው ከመሠረቱ ጀምሮ አንድ ሜትር ያህል ከፍታ በድንጋይ ተገንብቷል፡፡ ቀሪው ክፍል በቀጫጭን ሸንበቆ የተሰራ በመሆኑ ለመፍረስ እየቃጣው ነው፡፡ ሕመሜ አገረሸ፡፡ እስኪበቃኝ አለቀስኩ፡፡ ለቅሶዬ ግን መፍትሔ ሰጪ አልነበረም፡፡ የቀድሞው ቤተ ክርስቲያን በመብረቅ ተመትቶ በመቃጠሉ ፍርስራሹ ብቻ ለታሪክ ነጋሪነት ተቀምጧል፡፡ አገልጋዮቹ ከአምስት አይበልጡም፡፡ አነስተኛ የእርሻ መሬት ከደሴቱ ወዲያ ማዶ ስላላቸው እያረሱ ይተዳደራሉ፡፡ ተተኪ ግን የላቸውም፡፡ ያገኘነውን አነስተኛ መረጃ ቋታችን ውስጥ አስገብተን ጉዟችንን ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም ቀጠልን፡፡ አዳራችንንም እዚያው ለማድረግ ተስማማን፡፡ የማን እንደ አባ ገዳምን ሁኔታ ስመለከት ደግሞ ሕመሜ በመጽናናት አስታገስኩት፡፡

ዛሬ ስለ ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም የምነግራችሁ አይኖረኝም፡፡ አንድ ነገር ብቻ ጠቁሜያችሁ ልለፍ፡፡ ገዳሙ ለሌሎች ገዳማት ምሳሌ ሊሆን የሚችልና ትክክለኛ የገዳም ገጽታና ሥርዓት የተላበሰ ስለመሆኑ ካየሁትና ከሰማሁት ነገር ተነስቼ መመስከር እችላለሁ፡፡ እግዚአብሔር ቢፈቅድ በሌላ ጊዜ እንመለስበታለን፡፡

በማግስቱ በጠዋት ወደ ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ አንድነት ገዳም የአንድ ሰዓት የሐይቅ ላይ ጉዞ ተጀመረ፡፡

ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ አንድነት ገዳም እስካሁን ካየናቸው ገዳማት በተራራማነቱ ለየት ይላል፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እየወጣን ተግባር ቤት አካባቢ ሁለት ሰዎችን አገኘን፡፡ የመጣንበትን አስረድተን መረጃ እንዲሰጡን ጠየቅናቸው፡፡ አገልጋዮቹ ሁሉም ወደ ሞፈር ቤት መሄዳቸውን ነገሩን፡፡ እነሱም የቤተ ክርስቲያኑን አባቶች የሚራዱ የአካባቢው ገበሬዎች እንደሆኑ ገለጹልን፡፡

ከመካከላቸውም አንዱ አባት ስለቤተ ክርስቲያኑ የሚያውቁትን ታሪክ ያጫወቱን ዘንድ ፈቃዳቸው ሆነ፡፡ ገዳሙ ደርቡሽ ጎንደርን በወረረበት ወቅት ገዳማትን ሲያፈርስ የየገዳማቱ ቅርሶች መሸሸጊያ ሆኗል፡፡ ደርቡሽ ሊደርስባቸው ካልቻላቸው ገዳማት አንዱ ነው፡፡ በገዳሙ በጾምና ጸሎት በመትጋት የዘጉ አባቶች መኖራቸውንና ምግባቸውንም ወደ ባእታቸው እንደሚወስዱላቸው፤ ለማንም እንደማይታዩ፤ አንዳንዴም ለሳምንት ያህል የተወሰደላቸው ምግብ ሳይቀምሱት እንደሚያገኙት ነገሩን፡፡

ያስፈልጋሉ ያልናቸውን መረጃዎች ከመሰብሰብ ወደ ኋላ አላልንም፡፡ እያንዳንዱ ጉዞ ሕመም አለው፡፡ የገዳማት የወደፊት እጣ ፈንታ ምን ይሆን እንድንል አስገድዶናል፡፡ የእያንዳንዳችን ሕሊና በምናያቸውና በምንሰማቸው ነገሮች መታመሙን ቀጥሏል፡፡

እጀበራ ማርያም ገዳም፡-
እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ለመሄድ ተነስተናል፡፡ እዚህ ደግሞ ምን ይገጥመን ይሆን?  ፍርሃት ፍርሃት አለኝ፡፡

እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ስንደርስ ቤተ ክርስቲያኑ ፈርሶ ግንባታው ተጀምሯል፡፡ ግንበኞች ድንጋይ ይከሰክሳሉ፤ ገሚሶቹ በአቅራቢያው ከሚገኘው አካባቢ በጀልባ ተጭኖ የመጣውን ድንጋይ ያራግፋሉ፡፡

ከአንዲት አነስተኛ ተግባር ቤት ውስጥ አንድ አባት አገኘን፡፡ አንድ ዛፍ ጥላ ሥር ሁላችንም ተሰባሰብን፡፡

ለተወሰኑ ደቂቃዎች ሁላችንም በዝምታ ተዋጥን፡፡ አባታችን ዝምታውን ሰብረው “ለምን መጣችሁ?” አሉን በየተራ እያንዳንዳችንን አየቃኙ፡፡

የመጣንበትን አስረዳን፡፡ ደስ አላላቸውም፡፡

እያለቀሱ የገዳማትን ችግሮች እየዘረዘሩ ይናገራሉ፡፡ በሚናገሯቸው ቃላቶች እያንዳንዳችን እየታመምን ነው፡፡ ማሳረጊያችንም በህመም ሊደመደም ሆነ፡፡

ከሃያ ዓመታት በፊት በዚሁ ገዳም ለሦስት ዓመታት መኖራቸውንና ገዳሙ ሊፈታ እንደሆነ በመስማታቸው ይህንን ለመታደግ ወደ ገዳሙ ከመጡ ገና ሦስት ወራት ብቻ እንደሆናቸው፤ የአቅማቸውን ያህል ጥረት በማድረግ ወደ ቀደመ ክብሩ ለመመለስ እየተፍጨረጨሩ እንደሚገኙ ገለጹልን፡፡ ከገዳሙ አቅራቢያ የሚገኙ ነዋሪዎችን በማስተባበር ቤተ ክርስቲያኑን በማሰራትና አንዳንድ የልማት ሥራዎችን እያስጀመሩ መሆናቸውን አስረዱን፡፡

ገዳሙ ምንም ዓይነት የልማት እንቅስቃሴ አይታይበትም፡፡ እኚህ አባት ወደፊት ከባድ ሥራ እንደሚጠብቃቸው ከሁኔታው መረዳት ይቻላል፡፡

debere gelela eyesuseእነዚህ ገዳማት ወደፊት ምን ይገጥማቸው ይሆን? ይፈልሱ ይሆን ወይስ ወደ ቀደመ ታላቅነታቸው ተመልሰው እናይ ይሆን? ገዳማት ከመፈታታቸው በፊት ልንደርስላቸው ግድ ይለናል፡፡ ይህ የቤት ሥራ ለእያንዳንዳችን የተቀመጠ ኃላፊነት ነው፡፡

ዝምታ እንደነገሰብን ወደ ጀልባችን አመራን፡፡ ጉዞ ወደ ጎርጎራ ወደብ፡፡

በጉዟችን አንድ ነገር አስደስቶናል፡፡ አባቶቻችን ለቅርሶች ያላቸው ግንዛቤና ቅርሶች እንዳይዘረፉ የሚያደርጉት ጥንቃቄ ያስገርማል፡፡ እንኳን ለማሳየት ያለበትንም አይጠቁሙም፡፡ በእያንዳንዱ ገዳም ውሰጥ የገጠመን ተመሳሳይ ጉዳይ ሆኖ አለፈ፡፡ ነገር ግን አብዛኞቹ ገዳማት ስጋት ቢኖርባቸውም በያዝናቸው ደብዳቤዎች እየተረዳን አሰተናግደውናል፡፡ በቅርስ ዙሪያ የሚያደርጉት ጥንቃቄ ሊበረrታ የሚገባው መሠረታዊ ጉዳይ ነው፡፡

የተፈቱና በመፈታት ላይ የሚገኙ ገዳማት ድረሱልን በማለት ላይ ናቸው፡፡ ጥሪያቸውን መስማት ብቻ ሳይሆን የማቅናትም ግዴታ እንሸከም ዘንድ ግድ ይለናል፡፡

ይቆየን፡፡

ቤተ ክርስቲያን ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ
ሚያዚያ 15 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ከጎንደር ከተማ በጎርጎራ ወደብ አድርገን ልንቃኛቸው በመረጥናቸው አምስት የጣና ሐይቅ ገዳማትን ለመዘገብ የተነሳነው ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ነው፡፡ የጀልባ ላይ ጉዞ አድርጌ አላውቅም፡፡ ነገር ግን ቅዱሳን አበውን ያፈሩ፤ በጾም በጸሎት፤ በተጋድሎ የጸኑባቸው ገዳማትን በረከት ለማግኘት፤ ታሪካቸውን ለመቃኘት ቸኩያለሁ፡፡ የጋዜጠኞቹ ቡድን በአንድነት ሆነን የ64 ኪሎ ሜትሩን መንገድ ተያያዝነው፡፡
አመሻሽ ላይ ጎርጎራ ወደብ ደረስን፡፡ የጠዋት ጉዟችንን ለማመቻቸት እንዲረዳን ወደቡ ላይ ከሚገኘው የደብረ ሲና ቅድስት ማርያም ገዳም የአባቶችን ፈቃድ በመጠየቅ የምንፈልገውን መረጃ ማሰባሰባችንን ቀጠልን፡፡ በምፈልገው አቅጣጫ ጥያቄዎችን እየጠየቅን፤ ምላሽ ከአባቶች እየተሰጠን አመሸን፡፡ አዳራችንንም እዚያው አደረግን፡፡
በጠዋት ተነስተን አንጋራ ተክለ ሃማኖት ገዳምና ብርጊዳ ቅድስት ማርያም ገዳምን ቃኝተን  ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም ስንደርስ በመምሸቱ አስፈላጊ ናቸው ያልናቸውን መረጃዎች ስናሰባስብ አደርን፡፡ በማግስቱም ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ ገዳም ዘልቀን እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ላይ ከተምን፡፡
የዛሬው የጸበል ጸዲቅ ጽሑፌ እንደ ሰሞኑ ታሪክ ላይ ያተኮረ አይደለም፡፡ በጉዟችን የቃኘናቸው የአባቶቻችን አሻራ ያረፈባቸው፤ እግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ የስልጣኔ ጫፍ የደረሰ አእምሯቸው ውጤቶች በነበሩ ነገር ግን የተፈቱና ለመፈታት በቋፍ ላይ የሚገኙት ጥንታዊ የጣና ደሴት በረከቶችን እንቃኝ ዘንድ ወደድኩ፡፡ ክፍል አራት ጸበል ጸዲቅን ተቃመሱ፡፡
አንጋራ አቡነ ተክለ ሃማኖት ገዳም፡-
አንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ለመድረስ ከደብረ ሲና ማርያም ገዳም የ20 ደቂቃ በጀልባ  የጣና ሐይቅን ማቋረጥ ይጠይቃል፡፡ በደብረ ሲና ማርያም ገዳም አገልጋይ የሆኑት ሁለት መነኮሳት አባቶች ወደ ማን እንደ አባ አቡነ ያሳይ መድኀኔዓለም ገዳም ስለሚሔዱ እንድናደርሳቸው ስለጠየቁን አብረን ለመጓዝ ተስማምተን ጸሎት አድርገውልን የጣና ሐይቅ የጀልባ ላይ ጉዞ ተጀመረ፡፡
አንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ስንደርስ ያልጠበቅነው ነገር ገጠመን፡፡ በድንጋያማው ደሴት ላይ ያረፈው ቤተ መቅደስ በዝምታ ተውጧል፡፡ አፍ አውጥቶ “የሰው ያለህ” በማለት የሚጣራ ይመስላል፡፡ በአካባቢው ሰው ዘር ያለ አይመስልም፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ስንጠጋ አንዲት ደሳሳ ጎጆ ቤት ደጃፍ ላይ አንድ አባት እድሜ ተጭኗቸው ኩርምት ብለው ተቀምጠዋል፡፡ ዓይነ ሥውር ናቸው፡፡ ዘጠና ዓመታቸው ሲሆን ወደ አንጋራ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ከመጡ 25 ዓመታታን አስቆጥረዋል፡፡
“አባታችን ስለዚህ ገዳም ታሪክና አሁን ያለበት ሁኔታ የሚነግረን ሰው እናገኝ ይሆን?” የሁላችንም ጥያቄ ነበር፡፡
“የምን ሰው?! ማን አለ ብላችሁ ነው?! ገዳሙ ሊፈታ ምንም አልቀረውም፡፡ እስቲ ወደ ታች ወረድ ብላችሁ ገበዙን ፈልጉት” አሉን፡፡
ውስጤ መረበሽ ጀመረ፡፡ ማንን እንጠይቅ? የኢየሩሳሌምን ጥፋት አታሳየኝ ያለውና እንደ ቃሉም የተፈጸመለት አቤሜሌክን አስታወስኩ፤፤ ከጓደኞቼ ገንጠል ብዬ የሚተናነቀኝን የቁጭት እንባ አፈሰስኩ፡፡ ቤተ መቅደሱ ላይ ዓይኖቼ እንደተተከሉ አባቶችን አሰብኩ፡፡ አባቶቻችን ይህንን ገዳም ሲገድሙት ምን ይመስል ነበር? በገዳማውያን አባቶች ተሞልቶ፤ መላእክትን መስለው እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑበት፤ በጸሎት አጋንንት ድል ሲነሱበት የነበረ፤ ቃል ኪዳን የተቀበሉበት ሥፍራ ምነው ዛሬ ነጠፈ?! ራሴንና ይህንን ትውልድ ተጠያቂ ከማድረግ ሌላ ምን ማለት እችላለሁ? አባቶቻችንን መስለን ያልተገኘን፤ የአባቶቻችን አደራ መሸከምም ሆነ መወጣት ያቃተን ትውልዶች እንደሆንን ተሰማኝ፡፡ ብቻዬን መሆን አማረኝ፡፡ ነገር ግን አልቻልኩም እንደተከፋሁ ከጓደኞቼ ጋር ተቀላቀልኩ፡፡ እንደ እኔው በዝምታ ቆዝመዋል፡፡  
የቤተ ክርስቲያኑን ገበዝ ከእኛ ጋር ከደብረ ሲና ቅድስት ማርያም ገዳም የመጡት መነኮሳት አባቶች ፈልገው ይዘዋቸው መጡ፡፡ በእርግና እድሜ ላይ ነው የሚገኙት፡፡ ደብዳቤያችንን አሳይተን መረጃ እንዲሰጡን ጠየቅናቸው፡፡ ታሪኩን በተደራጀ መልኩ መናገር ተሳናቸው፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን ቅድስት ቤተ ክርስተቲያንን ለትውልድ ይተላለፍ ዘንድ የከፈሉት መስዋእትነት እንደዋዛ ፈዛዛ ማለፉ ነው፡፡ ገዳሙ የእምነታችን መገለጫ የሆኑትን የአባቶቻችንን ታሪክና ቅርሶችን ታቅፎ ዝምታን መምረጡ ለምን ይሆን? ለመሆኑ ተጠያቂው ማነው? ውስጤን ሰላም ነሳኝ፡፡  
አገልጋዮቹ ከሦስት አይበልጡም፡፡ ቅዳሴ አይታሰብም፡፡ ከቀናቸው ኪዳን ያደርሳሉ፡፡ ካልሆነም በግል ጸሎት ይተጋሉ፡፡ የሚተካቸው የለም፡፡ ይህ ትውልድ ርቋቸዋል፡፡ አባቶቻችንን መምሰል፤ በቃልኪዳናቸው መጠቀምን ዘንግተን ይሆን? የወደፊት የእኛም ሆነ የተፈቱ ገዳማት እጣ ፈንታ ምን ይሆን? የቃረምነውን መረጃ ቋጥረን፤ በሐዘን አንገታችንን እንደደፋን ወደ ጀልባችን አመራን፡፡ ጉዞ ወደ ብርጊዳ ቅድስት ማርያም ገዳም፡፡
ብርጊዳ ማርያም ገዳም፡-
ወደ ብረጊዳ ማርያም ገዳም እያመራን ደሴት ስንመለከት ይህ ምንድነው ማለታችን አልቀረም፡፡ አብረውን ያሉት አባቶች ከእኛ የተሻለ መረጃ ስላላቸው የሰቀላ ሚካኤልን፤ የቅዱስ ጊዮርጊስንና የእመቤታችን ማርያም የጥንት ገዳማትን በጣታቸው እያሳዩን አለፍን፡፡ ሦስቱም ገዳማት ተፈትተው ዛሬ ሰው አልባ ሆነዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያኖቹም ፈርሰዋል፡፡ በምሰማው ነገር ታመምኩ፡፡
ብርጊዳ ማርያም ገዳምን  ከአንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ብዙም የተሻለ ነገር አለው ለማለት አያስደፍርም፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ክብ ሲሆን ዙሪያው ከመሠረቱ ጀምሮ አንድ ሜትር ያህል ከፍታ በድንጋይ ተገንብቷል፡፡ ቀሪው ክፍል በቀጫጭን ሸንበቆ የተሰራ በመሆኑ ለመፍረስ እየቃጣው ነው፡፡ ሕመሜ አገረሸ፡፡ እስኪበቃኝ አለቀስኩ፡፡ ለቅሶዬ ግን መፍትሔ ሰጪ አልነበረም፡፡ የቀድሞው ቤተ ክርስቲያን በመብረቅ ተመትቶ በመቃጠሉ ፍርስራሹ ብቻ ለታሪክ ነጋሪነት ተቀምጧል፡፡ አገልጋዮቹ ከአምስት አይበልጡም፡፡ አነስተኛ የእርሻ መሬት ከደሴቱ ወዲያ ማዶ ስላላቸው እያረሱ ይተዳደራሉ፡፡ ተተኪ ግን የላቸውም፡፡ ያገኘነውን አነስተኛ መረጃ ቋታችን ውስጥ አስገብተን ጉዟችንን ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም ቀጠልን፡፡ አዳራችንንም እዚያው ለማድረግ ተስማማን፡፡ የማን እንደ አባ ገዳምን ሁኔታ ስመለከት ደግሞ ሕመሜ በመጽናናት አስታገስኩት፡፡
ዛሬ ስለ ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም የምነግራችሁ አይኖረኝም፡፡ አንድ ነገር ብቻ ጠቁሜያችሁ ልለፍ፡፡ ገዳሙ ለሌሎች ገዳማት ምሳሌ ሊሆን የሚችልና ትክክለኛ የገዳም ገጽታና ሥርዓት የተላበሰ ስለመሆኑ ካየሁትና ከሰማሁት ነገር ተነስቼ መመስከር እችላለሁ፡፡ እግዚአብሔር ቢፈቅድ በሌላ ጊዜ እንመለስበታለን፡፡
በማግስቱ በጠዋት ወደ ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ አንድነት ገዳም የአንድ ሰዓት የሐይቅ ላይ ጉዞ ተጀመረ፡፡
ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ አንድነት ገዳም እስካሁን ካየናቸው ገዳማት በተራራማነቱ ለየት ይላል፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እየወጣን ተግባር ቤት አካባቢ ሁለት ሰዎችን አገኘን፡፡ የመጣንበትን አስረድተን መረጃ እንዲሰጡን ጠየቅናቸው፡፡ አገልጋዮቹ ሁሉም ወደ ሞፈር ቤት መሄዳቸውን ነገሩን፡፡ እነሱም የቤተ ክርስቲያኑን አባቶች የሚራዱ የአካባቢው ገበሬዎች እንደሆኑ ገለጹልን፡፡
ከመካከላቸውም አንዱ አባት ስለቤተ ክርስቲያኑ የሚያውቁትን ታሪክ ያጫወቱን ዘንድ ፈቃዳቸው ሆነ፡፡ ገዳሙ ደርቡሽ ጎንደርን በወረረበት ወቅት ገዳማትን ሲያፈርስ የየገዳማቱ ቅርሶች መሸሸጊያ ሆኗል፡፡ ደርቡሽ ሊደርስባቸው ካልቻላቸው ገዳማት አንዱ ነው፡፡ በገዳሙ በጾምና ጸሎት በመትጋት የዘጉ አባቶች መኖራቸውንና ምግባቸውንም ወደ ባእታቸው እንደሚወስዱላቸው፤ ለማንም እንደማይታዩ፤ አንዳንዴም ለሳምንት ያህል የተወሰደላቸው ምግብ ሳይቀምሱት እንደሚያገኙት ነገሩን፡፡
ያስፈልጋሉ ያልናቸውን መረጃዎች ከመሰብሰብ ወደ ኋላ አላልንም፡፡ እያንዳንዱ ጉዞ ሕመም አለው፡፡ የገዳማት የወደፊት እጣ ፈንታ ምን ይሆን እንድንል አስገድዶናል፡፡ የእያንዳንዳችን ሕሊና በምናያቸውና በምንሰማቸው ነገሮች መታመሙን ቀጥሏል፡፡
እጀበራ ማርያም ገዳም፡-
እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ለመሄድ ተነስተናል፡፡ እዚህ ደግሞ ምን ይገጥመን ይሆን?  ፍርሃት ፍርሃት አለኝ፡፡
እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ስንደርስ ቤተ ክርስቲያኑ ፈርሶ ግንባታው ተጀምሯል፡፡ ግንበኞች ድንጋይ ይከሰክሳሉ፤ ገሚሶቹ በአቅራቢያው ከሚገኘው አካባቢ በጀልባ ተጭኖ የመጣውን ድንጋይ ያራግፋሉ፡፡
ከአንዲት አነስተኛ ተግባር ቤት ውስጥ አንድ አባት አገኘን፡፡ አንድ ዛፍ ጥላ ሥር ሁላችንም ተሰባሰብን፡፡
ለተወሰኑ ደቂቃዎች ሁላችንም በዝምታ ተዋጥን፡፡ አባታችን ዝምታውን ሰብረው “ለምን መጣችሁ?” አሉን በየተራ እያንዳንዳችንን አየቃኙ፡፡
የመጣንበትን አስረዳን፡፡ ደስ አላላቸውም፡፡
እያለቀሱ የገዳማትን ችግሮች እየዘረዘሩ ይናገራሉ፡፡ በሚናገሯቸው ቃላቶች እያንዳንዳችን እየታመምን ነው፡፡ ማሳረጊያችንም በህመም ሊደመደም ሆነ፡፡
ከሃያ ዓመታት በፊት በዚሁ ገዳም ለሦስት ዓመታት መኖራቸውንና ገዳሙ ሊፈታ እንደሆነ በመስማታቸው ይህንን ለመታደግ ወደ ገዳሙ ከመጡ ገና ሦስት ወራት ብቻ እንደሆናቸው፤ የአቅማቸውን ያህል ጥረት በማድረግ ወደ ቀደመ ክብሩ ለመመለስ እየተፍጨረጨሩ እንደሚገኙ ገለጹልን፡፡ ከገዳሙ አቅራቢያ የሚገኙ ነዋሪዎችን በማስተባበር ቤተ ክርስቲያኑን በማሰራትና አንዳንድ የልማት ሥራዎችን እያስጀመሩ መሆናቸውን አስረዱን፡፡
ገዳሙ ምንም ዓይነት የልማት እንቅስቃሴ አይታይበትም፡፡ እኚህ አባት ወደፊት ከባድ ሥራ እንደሚጠብቃቸው ከሁኔታው መረዳት ይቻላል፡፡
እነዚህ ገዳማት ወደፊት ምን ይገጥማቸው ይሆን? ይፈልሱ ይሆን ወይስ ወደ ቀደመ ታላቅነታቸው ተመልሰው እናይ ይሆን? ገዳማት ከመፈታታቸው በፊት ልንደርስላቸው ግድ ይለናል፡፡ ይህ የቤት ሥራ ለእያንዳንዳችን የተቀመጠ ኃላፊነት ነው፡፡
ዝምታ እንደነገሰብን ወደ ጀልባችን አመራን፡፡ ጉዞ ወደ ጎርጎራ ወደብ፡፡
በጉዟችን አንድ ነገር አስደስቶናል፡፡ አባቶቻችን ለቅርሶች ያላቸው ግንዛቤና ቅርሶች እንዳይዘረፉ የሚያደርጉት ጥንቃቄ ያስገርማል፡፡ እንኳን ለማሳየት ያለበትንም አይጠቁሙም፡፡ በእያንዳንዱ ገዳም ውሰጥ የገጠመን ተመሳሳይ ጉዳይ ሆኖ አለፈ፡፡ ነገር ግን አብዛኞቹ ገዳማት ስጋት ቢኖርባቸውም በያዝናቸው ደብዳቤዎች እየተረዳን አሰተናግደውናል፡፡ በቅርስ ዙሪያ የሚያደርጉት ጥንቃቄ ሊበረrታ የሚገባው መሠረታዊ ጉዳይ ነው፡፡
የተፈቱና በመፈታት ላይ የሚገኙ ገዳማት ድረሱልን በማለት ላይ ናቸው፡፡ ጥሪያቸውን መስማት ብቻ ሳይሆን የማቅናትም ግዴታ እንሸከም ዘንድ ግድ ይለናል፡፡
ይቆየን፡፡
ቤተ ክርስቲያን ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ
ሚያዚያ 15 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ከጎንደር ከተማ በጎርጎራ ወደብ አድርገን ልንቃኛቸው በመረጥናቸው አምስት የጣና ሐይቅ ገዳማትን ለመዘገብ የተነሳነው ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ነው፡፡ የጀልባ ላይ ጉዞ አድርጌ አላውቅም፡፡ ነገር ግን ቅዱሳን አበውን ያፈሩ፤ በጾም በጸሎት፤ በተጋድሎ የጸኑባቸው ገዳማትን በረከት ለማግኘት፤ ታሪካቸውን ለመቃኘት ቸኩያለሁ፡፡ የጋዜጠኞቹ ቡድን በአንድነት ሆነን የ64 ኪሎ ሜትሩን መንገድ ተያያዝነው፡፡
አመሻሽ ላይ ጎርጎራ ወደብ ደረስን፡፡ የጠዋት ጉዟችንን ለማመቻቸት እንዲረዳን ወደቡ ላይ ከሚገኘው የደብረ ሲና ቅድስት ማርያም ገዳም የአባቶችን ፈቃድ በመጠየቅ የምንፈልገውን መረጃ ማሰባሰባችንን ቀጠልን፡፡ በምፈልገው አቅጣጫ ጥያቄዎችን እየጠየቅን፤ ምላሽ ከአባቶች እየተሰጠን አመሸን፡፡ አዳራችንንም እዚያው አደረግን፡፡
በጠዋት ተነስተን አንጋራ ተክለ ሃማኖት ገዳምና ብርጊዳ ቅድስት ማርያም ገዳምን ቃኝተን  ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም ስንደርስ በመምሸቱ አስፈላጊ ናቸው ያልናቸውን መረጃዎች ስናሰባስብ አደርን፡፡ በማግስቱም ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ ገዳም ዘልቀን እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ላይ ከተምን፡፡
የዛሬው የጸበል ጸዲቅ ጽሑፌ እንደ ሰሞኑ ታሪክ ላይ ያተኮረ አይደለም፡፡ በጉዟችን የቃኘናቸው የአባቶቻችን አሻራ ያረፈባቸው፤ እግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ የስልጣኔ ጫፍ የደረሰ አእምሯቸው ውጤቶች በነበሩ ነገር ግን የተፈቱና ለመፈታት በቋፍ ላይ የሚገኙት ጥንታዊ የጣና ደሴት በረከቶችን እንቃኝ ዘንድ ወደድኩ፡፡ ክፍል አራት ጸበል ጸዲቅን ተቃመሱ፡፡
አንጋራ አቡነ ተክለ ሃማኖት ገዳም፡-
አንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ለመድረስ ከደብረ ሲና ማርያም ገዳም የ20 ደቂቃ በጀልባ  የጣና ሐይቅን ማቋረጥ ይጠይቃል፡፡ በደብረ ሲና ማርያም ገዳም አገልጋይ የሆኑት ሁለት መነኮሳት አባቶች ወደ ማን እንደ አባ አቡነ ያሳይ መድኀኔዓለም ገዳም ስለሚሔዱ እንድናደርሳቸው ስለጠየቁን አብረን ለመጓዝ ተስማምተን ጸሎት አድርገውልን የጣና ሐይቅ የጀልባ ላይ ጉዞ ተጀመረ፡፡
አንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ስንደርስ ያልጠበቅነው ነገር ገጠመን፡፡ በድንጋያማው ደሴት ላይ ያረፈው ቤተ መቅደስ በዝምታ ተውጧል፡፡ አፍ አውጥቶ “የሰው ያለህ” በማለት የሚጣራ ይመስላል፡፡ በአካባቢው ሰው ዘር ያለ አይመስልም፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ስንጠጋ አንዲት ደሳሳ ጎጆ ቤት ደጃፍ ላይ አንድ አባት እድሜ ተጭኗቸው ኩርምት ብለው ተቀምጠዋል፡፡ ዓይነ ሥውር ናቸው፡፡ ዘጠና ዓመታቸው ሲሆን ወደ አንጋራ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ከመጡ 25 ዓመታታን አስቆጥረዋል፡፡
“አባታችን ስለዚህ ገዳም ታሪክና አሁን ያለበት ሁኔታ የሚነግረን ሰው እናገኝ ይሆን?” የሁላችንም ጥያቄ ነበር፡፡
“የምን ሰው?! ማን አለ ብላችሁ ነው?! ገዳሙ ሊፈታ ምንም አልቀረውም፡፡ እስቲ ወደ ታች ወረድ ብላችሁ ገበዙን ፈልጉት” አሉን፡፡
ውስጤ መረበሽ ጀመረ፡፡ ማንን እንጠይቅ? የኢየሩሳሌምን ጥፋት አታሳየኝ ያለውና እንደ ቃሉም የተፈጸመለት አቤሜሌክን አስታወስኩ፤፤ ከጓደኞቼ ገንጠል ብዬ የሚተናነቀኝን የቁጭት እንባ አፈሰስኩ፡፡ ቤተ መቅደሱ ላይ ዓይኖቼ እንደተተከሉ አባቶችን አሰብኩ፡፡ አባቶቻችን ይህንን ገዳም ሲገድሙት ምን ይመስል ነበር? በገዳማውያን አባቶች ተሞልቶ፤ መላእክትን መስለው እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑበት፤ በጸሎት አጋንንት ድል ሲነሱበት የነበረ፤ ቃል ኪዳን የተቀበሉበት ሥፍራ ምነው ዛሬ ነጠፈ?! ራሴንና ይህንን ትውልድ ተጠያቂ ከማድረግ ሌላ ምን ማለት እችላለሁ? አባቶቻችንን መስለን ያልተገኘን፤ የአባቶቻችን አደራ መሸከምም ሆነ መወጣት ያቃተን ትውልዶች እንደሆንን ተሰማኝ፡፡ ብቻዬን መሆን አማረኝ፡፡ ነገር ግን አልቻልኩም እንደተከፋሁ ከጓደኞቼ ጋር ተቀላቀልኩ፡፡ እንደ እኔው በዝምታ ቆዝመዋል፡፡ 
የቤተ ክርስቲያኑን ገበዝ ከእኛ ጋር ከደብረ ሲና ቅድስት ማርያም ገዳም የመጡት መነኮሳት አባቶች ፈልገው ይዘዋቸው መጡ፡፡ በእርግና እድሜ ላይ ነው የሚገኙት፡፡ ደብዳቤያችንን አሳይተን መረጃ እንዲሰጡን ጠየቅናቸው፡፡ ታሪኩን በተደራጀ መልኩ መናገር ተሳናቸው፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን ቅድስት ቤተ ክርስተቲያንን ለትውልድ ይተላለፍ ዘንድ የከፈሉት መስዋእትነት እንደዋዛ ፈዛዛ ማለፉ ነው፡፡ ገዳሙ የእምነታችን መገለጫ የሆኑትን የአባቶቻችንን ታሪክና ቅርሶችን ታቅፎ ዝምታን መምረጡ ለምን ይሆን? ለመሆኑ ተጠያቂው ማነው? ውስጤን ሰላም ነሳኝ፡፡ 
አገልጋዮቹ ከሦስት አይበልጡም፡፡ ቅዳሴ አይታሰብም፡፡ ከቀናቸው ኪዳን ያደርሳሉ፡፡ ካልሆነም በግል ጸሎት ይተጋሉ፡፡ የሚተካቸው የለም፡፡ ይህ ትውልድ ርቋቸዋል፡፡ አባቶቻችንን መምሰል፤ በቃልኪዳናቸው መጠቀምን ዘንግተን ይሆን? የወደፊት የእኛም ሆነ የተፈቱ ገዳማት እጣ ፈንታ ምን ይሆን? የቃረምነውን መረጃ ቋጥረን፤ በሐዘን አንገታችንን እንደደፋን ወደ ጀልባችን አመራን፡፡ ጉዞ ወደ ብርጊዳ ቅድስት ማርያም ገዳም፡፡
ብርጊዳ ማርያም ገዳም፡-
ወደ ብረጊዳ ማርያም ገዳም እያመራን ደሴት ስንመለከት ይህ ምንድነው ማለታችን አልቀረም፡፡ አብረውን ያሉት አባቶች ከእኛ የተሻለ መረጃ ስላላቸው የሰቀላ ሚካኤልን፤ የቅዱስ ጊዮርጊስንና የእመቤታችን ማርያም የጥንት ገዳማትን በጣታቸው እያሳዩን አለፍን፡፡ ሦስቱም ገዳማት ተፈትተው ዛሬ ሰው አልባ ሆነዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያኖቹም ፈርሰዋል፡፡ በምሰማው ነገር ታመምኩ፡፡
ብርጊዳ ማርያም ገዳምን  ከአንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ብዙም የተሻለ ነገር አለው ለማለት አያስደፍርም፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ክብ ሲሆን ዙሪያው ከመሠረቱ ጀምሮ አንድ ሜትር ያህል ከፍታ በድንጋይ ተገንብቷል፡፡ ቀሪው ክፍል በቀጫጭን ሸንበቆ የተሰራ በመሆኑ ለመፍረስ እየቃጣው ነው፡፡ ሕመሜ አገረሸ፡፡ እስኪበቃኝ አለቀስኩ፡፡ ለቅሶዬ ግን መፍትሔ ሰጪ አልነበረም፡፡ የቀድሞው ቤተ ክርስቲያን በመብረቅ ተመትቶ በመቃጠሉ ፍርስራሹ ብቻ ለታሪክ ነጋሪነት ተቀምጧል፡፡ አገልጋዮቹ ከአምስት አይበልጡም፡፡ አነስተኛ የእርሻ መሬት ከደሴቱ ወዲያ ማዶ ስላላቸው እያረሱ ይተዳደራሉ፡፡ ተተኪ ግን የላቸውም፡፡ ያገኘነውን አነስተኛ መረጃ ቋታችን ውስጥ አስገብተን ጉዟችንን ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም ቀጠልን፡፡ አዳራችንንም እዚያው ለማድረግ ተስማማን፡፡ የማን እንደ አባ ገዳምን ሁኔታ ስመለከት ደግሞ ሕመሜ በመጽናናት አስታገስኩት፡፡
ዛሬ ስለ ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም የምነግራችሁ አይኖረኝም፡፡ አንድ ነገር ብቻ ጠቁሜያችሁ ልለፍ፡፡ ገዳሙ ለሌሎች ገዳማት ምሳሌ ሊሆን የሚችልና ትክክለኛ የገዳም ገጽታና ሥርዓት የተላበሰ ስለመሆኑ ካየሁትና ከሰማሁት ነገር ተነስቼ መመስከር እችላለሁ፡፡ እግዚአብሔር ቢፈቅድ በሌላ ጊዜ እንመለስበታለን፡፡
በማግስቱ በጠዋት ወደ ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ አንድነት ገዳም የአንድ ሰዓት የሐይቅ ላይ ጉዞ ተጀመረ፡፡
ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ አንድነት ገዳም እስካሁን ካየናቸው ገዳማት በተራራማነቱ ለየት ይላል፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እየወጣን ተግባር ቤት አካባቢ ሁለት ሰዎችን አገኘን፡፡ የመጣንበትን አስረድተን መረጃ እንዲሰጡን ጠየቅናቸው፡፡ አገልጋዮቹ ሁሉም ወደ ሞፈር ቤት መሄዳቸውን ነገሩን፡፡ እነሱም የቤተ ክርስቲያኑን አባቶች የሚራዱ የአካባቢው ገበሬዎች እንደሆኑ ገለጹልን፡፡
ከመካከላቸውም አንዱ አባት ስለቤተ ክርስቲያኑ የሚያውቁትን ታሪክ ያጫወቱን ዘንድ ፈቃዳቸው ሆነ፡፡ ገዳሙ ደርቡሽ ጎንደርን በወረረበት ወቅት ገዳማትን ሲያፈርስ የየገዳማቱ ቅርሶች መሸሸጊያ ሆኗል፡፡ ደርቡሽ ሊደርስባቸው ካልቻላቸው ገዳማት አንዱ ነው፡፡ በገዳሙ በጾምና ጸሎት በመትጋት የዘጉ አባቶች መኖራቸውንና ምግባቸውንም ወደ ባእታቸው እንደሚወስዱላቸው፤ ለማንም እንደማይታዩ፤ አንዳንዴም ለሳምንት ያህል የተወሰደላቸው ምግብ ሳይቀምሱት እንደሚያገኙት ነገሩን፡፡
ያስፈልጋሉ ያልናቸውን መረጃዎች ከመሰብሰብ ወደ ኋላ አላልንም፡፡ እያንዳንዱ ጉዞ ሕመም አለው፡፡ የገዳማት የወደፊት እጣ ፈንታ ምን ይሆን እንድንል አስገድዶናል፡፡ የእያንዳንዳችን ሕሊና በምናያቸውና በምንሰማቸው ነገሮች መታመሙን ቀጥሏል፡፡
እጀበራ ማርያም ገዳም፡-
እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ለመሄድ ተነስተናል፡፡ እዚህ ደግሞ ምን ይገጥመን ይሆን?  ፍርሃት ፍርሃት አለኝ፡፡
እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ስንደርስ ቤተ ክርስቲያኑ ፈርሶ ግንባታው ተጀምሯል፡፡ ግንበኞች ድንጋይ ይከሰክሳሉ፤ ገሚሶቹ በአቅራቢያው ከሚገኘው አካባቢ በጀልባ ተጭኖ የመጣውን ድንጋይ ያራግፋሉ፡፡
ከአንዲት አነስተኛ ተግባር ቤት ውስጥ አንድ አባት አገኘን፡፡ አንድ ዛፍ ጥላ ሥር ሁላችንም ተሰባሰብን፡፡
ለተወሰኑ ደቂቃዎች ሁላችንም በዝምታ ተዋጥን፡፡ አባታችን ዝምታውን ሰብረው “ለምን መጣችሁ?” አሉን በየተራ እያንዳንዳችንን አየቃኙ፡፡
የመጣንበትን አስረዳን፡፡ ደስ አላላቸውም፡፡
እያለቀሱ የገዳማትን ችግሮች እየዘረዘሩ ይናገራሉ፡፡ በሚናገሯቸው ቃላቶች እያንዳንዳችን እየታመምን ነው፡፡ ማሳረጊያችንም በህመም ሊደመደም ሆነ፡፡
ከሃያ ዓመታት በፊት በዚሁ ገዳም ለሦስት ዓመታት መኖራቸውንና ገዳሙ ሊፈታ እንደሆነ በመስማታቸው ይህንን ለመታደግ ወደ ገዳሙ ከመጡ ገና ሦስት ወራት ብቻ እንደሆናቸው፤ የአቅማቸውን ያህል ጥረት በማድረግ ወደ ቀደመ ክብሩ ለመመለስ እየተፍጨረጨሩ እንደሚገኙ ገለጹልን፡፡ ከገዳሙ አቅራቢያ የሚገኙ ነዋሪዎችን በማስተባበር ቤተ ክርስቲያኑን በማሰራትና አንዳንድ የልማት ሥራዎችን እያስጀመሩ መሆናቸውን አስረዱን፡፡
ገዳሙ ምንም ዓይነት የልማት እንቅስቃሴ አይታይበትም፡፡ እኚህ አባት ወደፊት ከባድ ሥራ እንደሚጠብቃቸው ከሁኔታው መረዳት ይቻላል፡፡
እነዚህ ገዳማት ወደፊት ምን ይገጥማቸው ይሆን? ይፈልሱ ይሆን ወይስ ወደ ቀደመ ታላቅነታቸው ተመልሰው እናይ ይሆን? ገዳማት ከመፈታታቸው በፊት ልንደርስላቸው ግድ ይለናል፡፡ ይህ የቤት ሥራ ለእያንዳንዳችን የተቀመጠ ኃላፊነት ነው፡፡
ዝምታ እንደነገሰብን ወደ ጀልባችን አመራን፡፡ ጉዞ ወደ ጎርጎራ ወደብ፡፡
በጉዟችን አንድ ነገር አስደስቶናል፡፡ አባቶቻችን ለቅርሶች ያላቸው ግንዛቤና ቅርሶች እንዳይዘረፉ የሚያደርጉት ጥንቃቄ ያስገርማል፡፡ እንኳን ለማሳየት ያለበትንም አይጠቁሙም፡፡ በእያንዳንዱ ገዳም ውሰጥ የገጠመን ተመሳሳይ ጉዳይ ሆኖ አለፈ፡፡ ነገር ግን አብዛኞቹ ገዳማት ስጋት ቢኖርባቸውም በያዝናቸው ደብዳቤዎች እየተረዳን አሰተናግደውናል፡፡ በቅርስ ዙሪያ የሚያደርጉት ጥንቃቄ ሊበረrታ የሚገባው መሠረታዊ ጉዳይ ነው፡፡
የተፈቱና በመፈታት ላይ የሚገኙ ገዳማት ድረሱልን በማለት ላይ ናቸው፡፡ ጥሪያቸውን መስማት ብቻ ሳይሆን የማቅናትም ግዴታ እንሸከም ዘንድ ግድ ይለናል፡፡
ይቆየን፡፡

sera 2 1

ሠራተኛ ጉባኤያት በቤተ ክርስቲያን ትልቅ ድርሻ እንደሚጠበቅባቸው ተገለጸ

ሚያዚያ 15 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዳዊት ደስታ

sera 2 1የማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል የሠራተኛ ጉባኤ የአንድነት መርሐ ግብር ሚያዚያ 13 ቀን 2005 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብከተ ወንጌል አዳራሽ በተካሄደው መርሐ ግብር ሠራተኛ ጉባኤያት በቤተ ክርስቲያን ትልቅ ድርሻ እንደሚጠበቅባቸው ተገለጸ፡፡

የመርሐ ግብሩን ዓላማ አስመልክቶ የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል ሓላፊ የሆኑት ኀይለ ማርያም መድኅን “በአዲስ አበባ ማእከል ሥር ሆነው የሚማሩ 22 የሚደርሱ የሠራተኛ ጉባኤያት ለቤተ ክርስቲያን እውቀታቸውን፣ ገንዘባቸውን፣ ጊዜያቸውን ሊያበረክቱ የሚያስችላቸውን ነገር ማስጨበጥና በተደራጀ ሁኔታ ቤተ ክርስቲያንን በአቅም ማገልገል የሚችሉበትን ሁኔታ ለመፍጠር ነው” በማለት ገልጸዋል፡፡

አያይዘውም እንደዚህ ዓይነት መርሐ ግብር ሲዘጋጅ የመጀመሪያ ጊዜ በመሆኑ ወደፊት የተለያዩ የሠራተኛ ጉባኤያትን በአንድነት ለማጠናከር በቤተ ክርስቲያን ከዚህ ቀደም ከሚሠሩት የተሻለ ሥራ እንዲሠሩ ለማድረግ የታሰበ ነው በማለት ሓላፊው ተናግረዋል፡፡

በዕለቱ በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ “የቤተ ክርስቲያን ተልዕኮና ዓላማ እና የልጆቿ ድርሻ” በሚል ጥናታዊ ጽሑፍ፣ ትምህርተ ወንጌልና መዝሙር ቀርቧል፡፡ በቀረበው ጥናታዊ ጽሑፍsera 2 2 አስተያየትና ጥያቄዎች ቀርበው ከጥናት አቅራቢው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ ላይ ሲሳተፉ ያገኘናቸው አቶ ተስፋዬ አሻግሬ “በዛሬዋ ቀን በመገኘቴ ትልቅ ደስታ ተሰምቶኛል፡፡ ምክንያቱም በርካታ መሥሪያ ቤቶች ጉባኤ ያካሂዳሉ፡፡ ከመማር ባለፈ ምንም ድርሻ እንዳለን እንኳ አናውቅም ነበር፡፡ ዛሬ ግን ቤተ ክርስቲያናችን ከኛ ከልጆቿ ብዙ ነገር እንደምትጠብቅና መሥራት እንደምንችል አውቄበታለው” በማለት ገልጸዋል፡፡

በዕለቱ በተደረገው መርሐ ግብር ከአምስት መቶ በላይ የሆኑ በተለያየ መሥሪያ ቤት የሚሠሩ የሠራተኛ ጉባኤ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል፡፡

health

ለአብነት ተማሪዎች በጤና አጠባበቅ ላይ ያተኮረ ሥልጠና ተሰጠ

ሚያዚያ 14 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

healthበማኅበረ ቅዱሳን የቅዱሳት መካናት ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዋና ክፍል ከጎንደር ማእከል ጋር በመተባበር በጎንደር ውስጥ ከሚገኙ አብነት ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ ተማሪዎች በግልና በአካባቢ ንጽህና አጠባበቅ ላይ ያተኮረና አንድ ቀን የወሰደ ስልጠና በደብረ ኀይል ወደብረ ጥበብ በዓት ለማርያም ቤተ ክርስቲያን አዳራሽ  ሚያዚያ 12 ቀን 2005 ዓ.ም. ተሰጠ፡፡

“ጤና ሀብት ነው” በሚል መሪ ቃል የተሰጠውን ሥልጠና በማስመልከት በማኅበረ ቅዱሳን የቅዱሳት መካናት ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የአብነት ትምህርት ቤቶች ክትትል ክፍል ምክትል ኃላፊና የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ሊቀ ዲያቆን መሐሪ መዘምር የሥልጠናውን ዓላማ አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ “በአብነት ትምህርት ቤቶች ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የጤና ችግሮች ይታያሉ፡፡ ይህንንም መነሻ በማድረግ 25 ሺህ ተማሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ፕሮጀክት በመቅረጽ የጤና አጠባበቅ ትምህርት ለአብነት ትምህርት ተማሪዎች ለመስጠት አቅደን ወደ ትግበራ በመሸጋገር ላይ እንገኛለን፡፡ ጎንደር ከተማ ውስጥ እስከ 2000 ተማሪዎች ይገኛሉ ተብሎ ስለሚገመት ለሁሉም ሥልጠና ለመስጠት ስለሚያዳግት ከየአብነት ትምህርት ቤቱ ለተውጣጡ 200 ተማሪዎች ሥልጠናውን እየሰጠን እንገኛለን፡፡ ተማሪዎቹም በአብነት ትምህርት ቤቶቻቸው ውስጥ ለሚገኙ ጓደኞቻቸው የአቻ ለአቻ ሥልጠና እንዲሰጡ እናደርጋለን፡፡” ብለዋል፡፡

በጎንደር ማኅበረ ቅዱሳን ማእከል የአብነት ትምህርት ቤቶቹን የጤና አጠባበቅ ሁኔታ የሚከታተልና የሚቆጣጠር ኮሚቴ እንደሚዋቀር የተገለጸ ሲሆን የግልና የአካባቢ ንጽህና ለመጠበቅ የሚረዱ ቁሳቁሶች እደላና አጠቃሙን ለማሳየት በየአብነት ትምህርት ቤቶቹ የሙከራ ሥራ እንደሚሠራ ሊቀ ዲያቆን መሐሪ መዘምር ገልጸዋል፡፡

ከመንበረ ፀሐይ ቁስቋም ማርያም ገዳም የቅኔ ጉባኤ ቤት ተማሪ የሆኑት መሪ ጌታ ዮሴፍ ታረቀኝ ስለ ሥልጠናው ጠቀሜታ ሲገልጹ “አብሮ ስላደገብን ቀሸሽ ብለን ስለምንታይ ለተለያዩ በሽታዎች ስንጋለጥ ኖረናል፡፡ ንጽሕናችንን መጠበቅ የሚጠቅመው ራሳችንን ስለሆነ ማኅበረ ቅዱሳን እየሰጠን ያለውን ስልጠና ወስጄ ለተማሪዎች በቅኔ ነገራ ወቅትም ሆነ አመቺ በሆነ ስዓት ለማስተማር ተዘጋጅቻለሁ” ብለዋል፡፡

ስልጠናው የግልና የአካባቢ ንጽሕና አጠባበቅ፤ የውኃ አያያዝና አጠቃቀም፤ የምግብ አያዝና አጠቃቀም፤ የበሽታ መንስኤዎች፤ የበሽታ መተላለፊያ መንገዶች፤ ተላላፊ በሽታዎችን መከላከል፤ ወባ፤ የግርሻ በሽታ፤ . . . የሚሉ ርዕሶችን ያካተተ ሲሆን ለሃያ አምስት ሺህ ተማሪዎች በአራት ዓመታት ውስጥ ተጠቃሚ ለማድረግ እስከ አንድ ሚሊዮን ብር እንደሚፈጅ ተገልጧል፡፡  

kuskuam 01

ጎንደር – የቅዱሳት መካናት ማኅደር

ሚያዚያ 14 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

ጸበል ጸዲቅ /ክፍል ሦስት/


ጎንደር ገብተናል፡፡ ዞር ዞር እያልኩ ለመቃኘት ጊዜ አልወሰድኩም፡፡ የምችለውን ያህል እግሬ እሰከመራኝ ተጓዝኩ፡፡ ጎንደር ውስጥ አንድ ቤተ ክርስቲያን ለማግኘት አንድ ኪሎ ሜትር መጓዝ አይጠበቅብዎትም፡፡ ቀና ብለው አካባቢውን በዓይንዎ መቃኘት ብቻ ይበቃዎታል፡፡  ከሰሜን ወደ ደቡብ፤ ከምስራቅ ወደ ምዕራብ ቢመለከቱ በእርግጠኝነት የቤተ ክርስቲያን የጉልላት መስቀል እንዳሻዎት ያገኛሉ፡፡ በቃ ወደ ተመለከቱበት አቅጣጫ ማምራት፡፡ 44ቱ ተቦት የሚለው አባባል ቀድሞ በጎንደር 44 ታቦታት ስለነበሩ አይደል?

ወቅቱ የዐብይ ጾም በመሆኑ ከሌሊት ጀምሮ ስብሐተ እግዚአብሔር እንደ ጅረት ውኃ ያለማቋረጥ ከሊቃውንቱ አንደበት ይፈስሳል፡፡ ተኝተውም ይሁን ሥራ ላይ ሆነው አብረው ለማዜም ይገደዳሉ፡፡ ይህንን ዓለም አስረስተው ሰማያዊውን መንግሥት በተመስጦ ያስባሉ፡፡ ነፍስዎ በሚደርሰው ስብሐተ እግዚአብሔር ይለመልማል፡፡

ከጠዋት እስከ ስድስት ሰዓት፤ ከዚያም እስከ 9፡00 ሰዓት ምግብ ቤቶች፤ ሆቴሎችና ሻይ ቤቶች ሳይቀር ወንበሮቻቸውን ታቅፈው የሰው ያለህ ማለታቸው ጎንደር ውስጥ በጾም ወራት የተለመደ ነው፡፡ አንገቱ ላይ ክር ያላሰረ ለማየት ይቸግራል፡፡ ጎንደር ፈካ ደመቅ ማለት የምትጀምረው ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ሥርዓተ ቅዳሴ ከተጠናቀቀ በኋላ ነው፡፡ ጎንደር! የታላላቅ ቅዱሳት መካናት፤  የሊቃውንት ማኅደር፤ የነገሥታት አሻራ ያገዘፋት ከተማ!!

የጋዜጠኞቹ ቡድን ጎንደርን ተከፋፈልናት፡፡ በውስጧ ሸሽጋ ያኖረቻቸውን የአብያተ ክርስቲያናት ታሪክ፤ የሊቃውንቱ የሕይወት ተሞክሮ ለሌሎች ለማቃመስ ቸኩለናል፡፡ ለዛሬ ጎንደር ካቀፈቻቸው ቅዱሳት መካናት መከካል አንዱን ከብዙ በጥቂቱ እንካችሁ ጸበል ጸዲቅ ቅመሱ፡፡

የደብረ ፀሐይ ቁስቋም ማርያም ገዳም
kuskuam 01የደብረ ፀሐይ ቁስቋም ማርያም ገዳም ከጎንደር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በስተ ሰሜን አቅጣጫ ተራራው አናት ላይ በጥንታዊ ስልጣኔ አሻራ ባረፈበት ግንብ አጥር ታቅፎ ለሚያየው ውስጡን ይመረምሩ ዘንድ ይጋብዛል፡፡ ዓይኔም ልቦናዬም አርፎበታልና ስለዚህ ቤተ ክርስቲያንና ቤተ መንግሥት ለማወቅ ጉዞ ጀመርኩ፡፡ አቀበቱን እንደወጣሁ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የአብነት ትምህርት ተማሪዎች ጎጆዎችን አገኘሁ፡፡ ከተማሪዎቹ መካካል አንዱን እንኳን ማግኘት አልቻልኩም፡፡ ወደ ገዳሙ የሚያስገባው መንገድ እየተሠራ በመሆኑ አንዱን ሠራተኛ ጠየቅሁት፡፡ ወደ ጫካ ለቅኔ ቆጠራ ሄደዋል አለኝ፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ መግቢያ ተጠጋሁ፡፡ ከሦስት ሜትር በላይ እርዝመት ያለውና በኢትዮጵያውያን  ጠቢባን በድንጋይ የተገነባ ግንብ ጥንታዊነቱን በሚመሰክር ሁኔታ እርጅና ቢጫጫነውም ጥንካሬው ጎልቶ ይታያል፡፡ አጥሩ በዐፄ ፋሲል ግንብ ዲዛይን የተሠራ ነው፡፡   

ተሳልሜ ደጀ ሰላሙን እንዳለፍኩ አባቶችን ሳፈላልግ የገዳሙ የሙዝየም አስጎብኚና የቅኔ መምህሩ የኔታ ዳንኤል ኃይሉን አገኘሁ፡፡ የመጣሁበትን አስረድቼ፤ የተጻፈልኝን የፈቃድ ደብዳቤ በማሳየት ለምጠይቃቸው ጥያቄ ይመልሱ ዘንድ ፈቃደኛ በመሆናቸው አንድ ጥግ ያዝን፡፡ የነገሩኝን እንዲህ አዘጋጀሁት?!

አመሠራረቱ፡-
የደብረ ጸሐይ ቁስቋም ማርያም ገዳም በ1930ዎቹ ዓ.ም በአፄ በካፋ ባለቤት በእቴጌ ምንትዋብ አማካይነት የተሠራ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ አመሠራረቱም ዐፄ በካፋ ከሞቱ በኋላ እቴጌ ምንትዋብ ልጃቸውን ኢያሱን አንግሠው ከዐፄ ፋሲል ቤተ መንግሥት ግቢ በመውጣት ይህ ዓለም ይቅርብኝ፡ እመቤቴ ቅድስት ድንግል ማርያም በስደት በግብፅ በደብረ ቁስቋም ተራራ ላይ እንደተገኘች ሁሉ እኔም ለብቻዬ ልቀመጥ በማለት ቤተ መንግሥታቸውን ጥለው ቤተ ክርስቲያኑን በማሠራት ተቀመጡ፡፡  ከዚሁ ጋር በማያያዝም ቤተ መንግሥታቸውን አሠሩ፡፡ ቤተ ክርስቲያኑንና ቤተ መንግሥቱን ለማሠራት አንድ ሺሕ ግንበኞችና ባለሙያዎች የተሳተፉበት ሲሆን ለሁለት በመክፈል አምስት መቶው ሠራተኞች አንድ ቀን ሲሠሩ ሌሎቹ ደግሞ እያረፉ በየተራ ሠርተውታል፡፡ቤተ ክርስቲያኑንም ስደታቸውን በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስደት ጋር በማያያዝ በደብረ ቁስቋም ሰየሙት፡፡ ከሁለት ሃምሳ በላይ ቀሳውስትና ካህናት አገልጋዮች ነበሩት፡፡

እቴጌ ምንትዋብ ሲያርፉም በቤተ ክርስቲያኑ ምድር ቤት ውስጥ ባሠሩት መቃብር ቤታቸው አስከሬናቸው እንዲያርፍ የተደረገ ሲሆን ልጃቸው ኢያሱና የኢያሱ ልጅ ኢዮአስkuskuam 03 ሲያርፉም አብረው በእቴጌ ምንትዋብ መቃብር ቤት ተቀብረዋል፡፡

በ1881 ዓ.ም. ደርቡሽ ጎንደርን ሲወርር ጎንደር የሚገኙትን ብዙዎቹን ቤተ ክርስቲያናት ስያቀጥልና ሲያወድም ካህናቱ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ታቦት ወደ በለሳ በማሸሽ አስቀመጡት፡፡ ደብረ ቁስቋም ቤተ ክርስቲያንም ሙሉ ለሙሉ ወደመ፡፡ ቤተ መንግሥቱንም ደርቡሽ አፈራረሰው፡፡ አብዛኞቹ ቅርሶችም ተቃጠሉ፡፡ የተረፉትም ቢሆን ተዘርፈው ተወሰዱ፡፡ ካህናቱም ወደተለያዩ ቦታዎች ተበተኑ፡፡

ቅርሶች፡- ከጦርነቱ በኋላ ታቦቱን ወደነበረበት በመመለስ ቀድሞ እቃ ቤት የነበረውን  ቤት ቤተ መቅደስ በማድረግ በጥቂት ካህናት ብቻ ለሰማኒያ ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ ከቆየ በኋላ በ1960ዎቹ ዓ.ም. ዐፄ ኃይለ ሥላሴ አሁን ያለውን ቤተ ክርስቲያን አሠሩት፡፡ የእቴጌ ምንትዋብና የልጃቸው ኢያሱ፤ እንደሁም የኢያሱ ልጅ ኢዮአስን ዓፅም በአንድ ላይ በመሰብሰብ በሳጥን ውስጥ እዲቀመጥ ተደረገ፡፡ በአሁኑ ወቅትም በሙዝየሙ ውስጥ ከሚጎበኙ ቅርሶች መካከል አንዱ ነው፡፡

በሙዝየሙ ውስጥ የእቴጌ ምንትዋብና የልጆቻቸው በእንጨትና በጠፍር/ቆዳ/ የተሠራ አልጋ፤ በቀርከሃና በቆዳ የተሠሩ የከበሩ ዕቃዎች ማስቀመጫ ሻንጣዎች፤ ሚዛን፤ የደርቡሽ ጦር ካወደማቸው ሃይማኖታዊ የብራና መጻሕፍት የተረፉት ወንጌል ቅዱስ፤ ተአምረ ኢየሱስ፤ ግንዘት፤ ስንክሳር፤ ነገረ ማርያም፤ ሃማኖተ አበው፤ አሥራ አራቱ ቅዳሴያት፤ ግብረ ሕማማት፤ ገድለ ሠማዕታት፤. . . ከበሮ፤ የተለያዩ መጠን ያላቸው መስቀሎች፤ ነጋሪት፤ ከሙዝየሙ ውጪ በሩ አጠገብ የእቴጌ ምንትዋብ የድንጋይ ወፍጮ፤ . . .  ይገኛሉ፡፡

kuskuamቅዱሳት ሥዕላት፡- በሙዝየሙ ውስጥ በቅርስነት ከተያዙት ውስጥ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምስለ ፍቁር ወልዳና የቅዱስ መርቆርዮስ ቅዱሳት ሥዕላት ይገኙበታል፡፡

ቤተ መንግሥት፡- ቤተ መንግሥቱ ሰባት በሮች አሉት፡፡ የእቴጌ ምንትዋብ መኝታ ቤት፤ የገላ መታጠቢያ ቤት፤ ሣሎን፤ በዘመኑ የነበረው ታሪክ ጸሐፊው ጀምስ ብሩስ ይኖርበት የነበረው ክፍል፤ ካህናቱና ቀሳውስቱ የሚመገቡበት የግብር ቤት፤ ቤተ ክርስቲያኑንና ቤተ ክርስቲያኑን ያነጹት ባለሙያዎች ማረፊያ ክፍሎችና ዕቃ ማስቀመጫ ክፍሎች፤ . . . ፈራርሰው ይታያሉ፡፡

ጉባኤ ቤት፡- ጥንት የድጓ፤ የቅኔ፤ የአቋቋም፤ የቅዳሴ ጉባኤ ቤቶች እንደነበሩና ደርቡሽ ቤተ ክርስቲያኑን ካፈረሰ በኋላ ግን ጉባኤ ቤቶቹkuskuam 08 ተፈትተው ለረጅም ዘመናት ሳይተከሉ ኖረዋል፡፡ ጉባኤ ቤቱ በተደራጀ መልኩ ከተተከለ ሃያ ዓመታት ብቻ አስቆጥሯል፡፡ የቅኔ፤ የአቋቋም፤ የድጓና የቅዳሴ ጉባኤ ትምህርት እየተሰጠ ይገኛል፡፡ ከ500 በላይ ተማሪዎች ሲኖሩ 280 የሚደርሱት የቅኔ ተማሪዎች ናቸው፡፡

መረጃዎቻችንን እንዳሰባሰብን ያመራነው ወደ ጉባኤ ቤት ነው፡፡ ከየኔታ ዳንኤል ኃይሉ ጋር ተያይዘን ስንሄድ የቅኔ ተማሪዎቻቸው ከያሉበት ብቅ ብቅ ማለት ጀመሩ፡፡ ሌሊት ዕለቱን በማስመልከት የኔታ ካስረዷቸው በኋላ ለቅኔ ቆጠራ ይሠማራሉ፡፡ የኔታ በተማሪዎቻቸው ተከበቡ፡፡ የነገራ ሰዓት በመሆኑ ለጥቂት ደቂቃዎች እንድታገስ ጠየቁኝ፡፡ አላመነታሁም፡፡ ተማሪዎቹ ወንበር አውጥተው እንዲቀመጡ ካመቻቹላቸው በኋላ በአእምሯቸው ሲያመላልሱት የቆዩበትን ቅኔ ቆጠራ መዝረፍ ጀመሩ፡፡ ሲሳሳቱ እያረሙ፤ ያልተሳካለትን እየገሰጹ ቆዩ፡፡

 
የተማሪዎቹን የውድድር ስሜትና ለትምህርቱ ያላቸው ፍላጎት እያስገረመኝ ከተማሪዎቹ መካከል አይኖቼ ድንገት በለጋነት እድሜ ክልል የሚገኙ መነኩሲት ላይ አረፉ፡፡ ላነጋግራቸውም ወሰንኩ፡፡

የኔታ ከዚህ በላይ ሊያስቆዩኝ አልፈለጉም፡፡  ጉባኤውን አቋረጡት፡፡ እኔም እማሆይን ለመጠየቅ በመፍጠን ማንነታቸውን፤ ለምን መማር እንደፈጉ ጠየቅኋቸው፡፡

kuskuam 07“እማሆ ወለተ መድኅን እባላለሁ፡፡ ከአክሱም ነው የመጣሁት፡፡ በልጅነት ከመነኮስኩ አይቀር ጉባኤ ቤት መግባት አለብኝ ብዬ ስለወሰንኩ እዚህ እየተማርኩ እገኛለሁ፡፡ ትምህርቱንከጀመርኩ አንድ ዓመት ሆኖኛል፡፡ ጉባኤ ቃና፤ ዘአምላክየ፤ ሚበዝኁ፤ ዋዜማ፤ ሥላሴ፤ ዘይእዜ፤ ክብር ይእቲ፤ እጣነ ሞገርን አልፌ መወድስ ላይ ደርሻለሁ፡፡ እግዘአብሔር ቢፈቅድ ትምህርቴን አጽንቼ በመያዝ እግዚአብሔር ቢፈቅድ እንደ እማሆይ ገላነሽ ለመሆን ነው ምኞቴ” አሉኝ፡፡ ምኞታቸው እንዲሳካ ተመኘሁ፡፡

ከቀደሙት ነገሥታት የሃይማኖት ጽናትንና ቅርስን ለትውልድ ማቆየትን ተማርኩ፡፡ ከጉባኤ ቤቶቹ ደግሞ ቤተ ክርስቲያን የማይነጥፍ የሊቃውንት ምንጭ እንዳላት ተገነዘብኩ፡፡   
የኔታንና ተማሪዎቹን ተሰናብቼ ሌላ መረጃ ልቆፍር ተጓዝኩ፡፡

ይቆየን