tana desate

ቤተ ክርስቲያን ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ

ሚያዚያ 15 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

ጸበል ጸዲቅ /ክፍል አራት/

tana desateከጎንደር ከተማ በጎርጎራ ወደብ አድርገን ልንቃኛቸው በመረጥናቸው አምስት የጣና ሐይቅ ገዳማትን ለመዘገብ የተነሳነው ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ነው፡፡ የጀልባ ላይ ጉዞ አድርጌ አላውቅም፡፡ ነገር ግን ቅዱሳን አበውን ያፈሩ፤ በጾም በጸሎት፤ በተጋድሎ የጸኑባቸው ገዳማትን በረከት ለማግኘት፤ ታሪካቸውን ለመቃኘት ቸኩያለሁ፡፡ የጋዜጠኞቹ ቡድን በአንድነት ሆነን የ64 ኪሎ ሜትሩን መንገድ ተያያዝነው፡፡

አመሻሽ ላይ ጎርጎራ ወደብ ደረስን፡፡ የጠዋት ጉዟችንን ለማመቻቸት እንዲረዳን ወደቡ ላይ ከሚገኘው የደብረ ሲና ቅድስት ማርያም ገዳም የአባቶችን ፈቃድ በመጠየቅ የምንፈልገውን መረጃ ማሰባሰባችንን ቀጠልን፡፡ በምፈልገው አቅጣጫ ጥያቄዎችን እየጠየቅን፤ ምላሽ ከአባቶች እየተሰጠን አመሸን፡፡ አዳራችንንም እዚያው አደረግን፡፡

በጠዋት ተነስተን አንጋራ ተክለ ሃማኖት ገዳምና ብርጊዳ ቅድስት ማርያም ገዳምን ቃኝተን  ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም ስንደርስ በመምሸቱ አስፈላጊ ናቸው ያልናቸውን መረጃዎች ስናሰባስብ አደርን፡፡ በማግስቱም ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ ገዳም ዘልቀን እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ላይ ከተምን፡፡

የዛሬው የጸበል ጸዲቅ ጽሑፌ እንደ ሰሞኑ ታሪክ ላይ ያተኮረ አይደለም፡፡ በጉዟችን የቃኘናቸው የአባቶቻችን አሻራ ያረፈባቸው፤ እግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ የስልጣኔ ጫፍ የደረሰ አእምሯቸው ውጤቶች በነበሩ ነገር ግን የተፈቱና ለመፈታት በቋፍ ላይ የሚገኙት ጥንታዊ የጣና ደሴት በረከቶችን እንቃኝ ዘንድ ወደድኩ፡፡ ክፍል አራት ጸበል ጸዲቅን ተቃመሱ፡፡

አንጋራ አቡነ ተክለ ሃማኖት ገዳም፡-
angawa tekelehaymanoteአንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ለመድረስ ከደብረ ሲና ማርያም ገዳም የ20 ደቂቃ በጀልባ  የጣና ሐይቅን ማቋረጥ ይጠይቃል፡፡ በደብረ ሲና ማርያም ገዳም አገልጋይ የሆኑት ሁለት መነኮሳት አባቶች ወደ ማን እንደ አባ አቡነ ያሳይ መድኀኔዓለም ገዳም ስለሚሔዱ እንድናደርሳቸው ስለጠየቁን አብረን ለመጓዝ ተስማምተን ጸሎት አድርገውልን የጣና ሐይቅ የጀልባ ላይ ጉዞ ተጀመረ፡፡ 

አንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ስንደርስ ያልጠበቅነው ነገር ገጠመን፡፡ በድንጋያማው ደሴት ላይ ያረፈው ቤተ መቅደስ በዝምታ ተውጧል፡፡ አፍ አውጥቶ “የሰው ያለህ” በማለት የሚጣራ ይመስላል፡፡ በአካባቢው ሰው ዘር ያለ አይመስልም፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ስንጠጋ አንዲት ደሳሳ ጎጆ ቤት ደጃፍ ላይ አንድ አባት እድሜ ተጭኗቸው ኩርምት ብለው ተቀምጠዋል፡፡ ዓይነ ሥውር ናቸው፡፡ ዘጠና ዓመታቸው ሲሆን ወደ አንጋራ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ከመጡ 25 ዓመታታን አስቆጥረዋል፡፡

“አባታችን ስለዚህ ገዳም ታሪክና አሁን ያለበት ሁኔታ የሚነግረን ሰው እናገኝ ይሆን?” የሁላችንም ጥያቄ ነበር፡፡

“የምን ሰው?! ማን አለ ብላችሁ ነው?! ገዳሙ ሊፈታ ምንም አልቀረውም፡፡ እስቲ ወደ ታች ወረድ ብላችሁ ገበዙን ፈልጉት” አሉን፡፡

ውስጤ መረበሽ ጀመረ፡፡ ማንን እንጠይቅ? የኢየሩሳሌምን ጥፋት አታሳየኝ ያለውና እንደ ቃሉም የተፈጸመለት አቤሜሌክን አስታወስኩ፤፤ ከጓደኞቼ ገንጠል ብዬ የሚተናነቀኝን የቁጭት እንባ አፈሰስኩ፡፡ ቤተ መቅደሱ ላይ ዓይኖቼ እንደተተከሉ አባቶችን አሰብኩ፡፡ አባቶቻችን ይህንን ገዳም ሲገድሙት ምን ይመስል ነበር? በገዳማውያን አባቶች ተሞልቶ፤ መላእክትን መስለው እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑበት፤ በጸሎት አጋንንት ድል ሲነሱበት የነበረ፤ ቃል ኪዳን የተቀበሉበት ሥፍራ ምነው ዛሬ ነጠፈ?! ራሴንና ይህንን ትውልድ ተጠያቂ ከማድረግ ሌላ ምን ማለት እችላለሁ? አባቶቻችንን መስለን ያልተገኘን፤ የአባቶቻችን አደራ መሸከምም ሆነ መወጣት ያቃተን ትውልዶች እንደሆንን ተሰማኝ፡፡ ብቻዬን መሆን አማረኝ፡፡ ነገር ግን አልቻልኩም እንደተከፋሁ ከጓደኞቼ ጋር ተቀላቀልኩ፡፡ እንደ እኔው በዝምታ ቆዝመዋል፡፡ 

የቤተ ክርስቲያኑን ገበዝ ከእኛ ጋር ከደብረ ሲና ቅድስት ማርያም ገዳም የመጡት መነኮሳት አባቶች ፈልገው ይዘዋቸው መጡ፡፡ በእርግና እድሜ ላይ ነው የሚገኙት፡፡ ደብዳቤያችንን አሳይተን መረጃ እንዲሰጡን ጠየቅናቸው፡፡ ታሪኩን በተደራጀ መልኩ መናገር ተሳናቸው፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን ቅድስት ቤተ ክርስተቲያንን ለትውልድ ይተላለፍ ዘንድ የከፈሉት መስዋእትነት እንደዋዛ ፈዛዛ ማለፉ ነው፡፡ ገዳሙ የእምነታችን መገለጫ የሆኑትን የአባቶቻችንን ታሪክና ቅርሶችን ታቅፎ ዝምታን መምረጡ ለምን ይሆን? ለመሆኑ ተጠያቂው ማነው? ውስጤን ሰላም ነሳኝ፡፡ 

አገልጋዮቹ ከሦስት አይበልጡም፡፡ ቅዳሴ አይታሰብም፡፡ ከቀናቸው ኪዳን ያደርሳሉ፡፡ ካልሆነም በግል ጸሎት ይተጋሉ፡፡ የሚተካቸው የለም፡፡ ይህ ትውልድ ርቋቸዋል፡፡ አባቶቻችንን መምሰል፤ በቃልኪዳናቸው መጠቀምን ዘንግተን ይሆን? የወደፊት የእኛም ሆነ የተፈቱ ገዳማት እጣ ፈንታ ምን ይሆን? የቃረምነውን መረጃ ቋጥረን፤ በሐዘን አንገታችንን እንደደፋን ወደ ጀልባችን አመራን፡፡ ጉዞ ወደ ብርጊዳ ቅድስት ማርያም ገዳም፡፡

ብርጊዳ ማርያም ገዳም፡-
ወደ ብረጊዳ ማርያም ገዳም እያመራን ደሴት ስንመለከት ይህ ምንድነው ማለታችን አልቀረም፡፡ አብረውን ያሉት አባቶች ከእኛ የተሻለ መረጃ ስላላቸው የሰቀላ ሚካኤልን፤ የቅዱስbergeda mariyame ጊዮርጊስንና የእመቤታችን ማርያም የጥንት ገዳማትን በጣታቸው እያሳዩን አለፍን፡፡ ሦስቱም ገዳማት ተፈትተው ዛሬ ሰው አልባ ሆነዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያኖቹም ፈርሰዋል፡፡ በምሰማው ነገር ታመምኩ፡፡ 

ብርጊዳ ማርያም ገዳምን  ከአንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ብዙም የተሻለ ነገር አለው ለማለት አያስደፍርም፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ክብ ሲሆን ዙሪያው ከመሠረቱ ጀምሮ አንድ ሜትር ያህል ከፍታ በድንጋይ ተገንብቷል፡፡ ቀሪው ክፍል በቀጫጭን ሸንበቆ የተሰራ በመሆኑ ለመፍረስ እየቃጣው ነው፡፡ ሕመሜ አገረሸ፡፡ እስኪበቃኝ አለቀስኩ፡፡ ለቅሶዬ ግን መፍትሔ ሰጪ አልነበረም፡፡ የቀድሞው ቤተ ክርስቲያን በመብረቅ ተመትቶ በመቃጠሉ ፍርስራሹ ብቻ ለታሪክ ነጋሪነት ተቀምጧል፡፡ አገልጋዮቹ ከአምስት አይበልጡም፡፡ አነስተኛ የእርሻ መሬት ከደሴቱ ወዲያ ማዶ ስላላቸው እያረሱ ይተዳደራሉ፡፡ ተተኪ ግን የላቸውም፡፡ ያገኘነውን አነስተኛ መረጃ ቋታችን ውስጥ አስገብተን ጉዟችንን ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም ቀጠልን፡፡ አዳራችንንም እዚያው ለማድረግ ተስማማን፡፡ የማን እንደ አባ ገዳምን ሁኔታ ስመለከት ደግሞ ሕመሜ በመጽናናት አስታገስኩት፡፡

ዛሬ ስለ ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም የምነግራችሁ አይኖረኝም፡፡ አንድ ነገር ብቻ ጠቁሜያችሁ ልለፍ፡፡ ገዳሙ ለሌሎች ገዳማት ምሳሌ ሊሆን የሚችልና ትክክለኛ የገዳም ገጽታና ሥርዓት የተላበሰ ስለመሆኑ ካየሁትና ከሰማሁት ነገር ተነስቼ መመስከር እችላለሁ፡፡ እግዚአብሔር ቢፈቅድ በሌላ ጊዜ እንመለስበታለን፡፡

በማግስቱ በጠዋት ወደ ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ አንድነት ገዳም የአንድ ሰዓት የሐይቅ ላይ ጉዞ ተጀመረ፡፡

ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ አንድነት ገዳም እስካሁን ካየናቸው ገዳማት በተራራማነቱ ለየት ይላል፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እየወጣን ተግባር ቤት አካባቢ ሁለት ሰዎችን አገኘን፡፡ የመጣንበትን አስረድተን መረጃ እንዲሰጡን ጠየቅናቸው፡፡ አገልጋዮቹ ሁሉም ወደ ሞፈር ቤት መሄዳቸውን ነገሩን፡፡ እነሱም የቤተ ክርስቲያኑን አባቶች የሚራዱ የአካባቢው ገበሬዎች እንደሆኑ ገለጹልን፡፡

ከመካከላቸውም አንዱ አባት ስለቤተ ክርስቲያኑ የሚያውቁትን ታሪክ ያጫወቱን ዘንድ ፈቃዳቸው ሆነ፡፡ ገዳሙ ደርቡሽ ጎንደርን በወረረበት ወቅት ገዳማትን ሲያፈርስ የየገዳማቱ ቅርሶች መሸሸጊያ ሆኗል፡፡ ደርቡሽ ሊደርስባቸው ካልቻላቸው ገዳማት አንዱ ነው፡፡ በገዳሙ በጾምና ጸሎት በመትጋት የዘጉ አባቶች መኖራቸውንና ምግባቸውንም ወደ ባእታቸው እንደሚወስዱላቸው፤ ለማንም እንደማይታዩ፤ አንዳንዴም ለሳምንት ያህል የተወሰደላቸው ምግብ ሳይቀምሱት እንደሚያገኙት ነገሩን፡፡

ያስፈልጋሉ ያልናቸውን መረጃዎች ከመሰብሰብ ወደ ኋላ አላልንም፡፡ እያንዳንዱ ጉዞ ሕመም አለው፡፡ የገዳማት የወደፊት እጣ ፈንታ ምን ይሆን እንድንል አስገድዶናል፡፡ የእያንዳንዳችን ሕሊና በምናያቸውና በምንሰማቸው ነገሮች መታመሙን ቀጥሏል፡፡

እጀበራ ማርያም ገዳም፡-
እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ለመሄድ ተነስተናል፡፡ እዚህ ደግሞ ምን ይገጥመን ይሆን?  ፍርሃት ፍርሃት አለኝ፡፡

እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ስንደርስ ቤተ ክርስቲያኑ ፈርሶ ግንባታው ተጀምሯል፡፡ ግንበኞች ድንጋይ ይከሰክሳሉ፤ ገሚሶቹ በአቅራቢያው ከሚገኘው አካባቢ በጀልባ ተጭኖ የመጣውን ድንጋይ ያራግፋሉ፡፡

ከአንዲት አነስተኛ ተግባር ቤት ውስጥ አንድ አባት አገኘን፡፡ አንድ ዛፍ ጥላ ሥር ሁላችንም ተሰባሰብን፡፡

ለተወሰኑ ደቂቃዎች ሁላችንም በዝምታ ተዋጥን፡፡ አባታችን ዝምታውን ሰብረው “ለምን መጣችሁ?” አሉን በየተራ እያንዳንዳችንን አየቃኙ፡፡

የመጣንበትን አስረዳን፡፡ ደስ አላላቸውም፡፡

እያለቀሱ የገዳማትን ችግሮች እየዘረዘሩ ይናገራሉ፡፡ በሚናገሯቸው ቃላቶች እያንዳንዳችን እየታመምን ነው፡፡ ማሳረጊያችንም በህመም ሊደመደም ሆነ፡፡

ከሃያ ዓመታት በፊት በዚሁ ገዳም ለሦስት ዓመታት መኖራቸውንና ገዳሙ ሊፈታ እንደሆነ በመስማታቸው ይህንን ለመታደግ ወደ ገዳሙ ከመጡ ገና ሦስት ወራት ብቻ እንደሆናቸው፤ የአቅማቸውን ያህል ጥረት በማድረግ ወደ ቀደመ ክብሩ ለመመለስ እየተፍጨረጨሩ እንደሚገኙ ገለጹልን፡፡ ከገዳሙ አቅራቢያ የሚገኙ ነዋሪዎችን በማስተባበር ቤተ ክርስቲያኑን በማሰራትና አንዳንድ የልማት ሥራዎችን እያስጀመሩ መሆናቸውን አስረዱን፡፡

ገዳሙ ምንም ዓይነት የልማት እንቅስቃሴ አይታይበትም፡፡ እኚህ አባት ወደፊት ከባድ ሥራ እንደሚጠብቃቸው ከሁኔታው መረዳት ይቻላል፡፡

debere gelela eyesuseእነዚህ ገዳማት ወደፊት ምን ይገጥማቸው ይሆን? ይፈልሱ ይሆን ወይስ ወደ ቀደመ ታላቅነታቸው ተመልሰው እናይ ይሆን? ገዳማት ከመፈታታቸው በፊት ልንደርስላቸው ግድ ይለናል፡፡ ይህ የቤት ሥራ ለእያንዳንዳችን የተቀመጠ ኃላፊነት ነው፡፡

ዝምታ እንደነገሰብን ወደ ጀልባችን አመራን፡፡ ጉዞ ወደ ጎርጎራ ወደብ፡፡

በጉዟችን አንድ ነገር አስደስቶናል፡፡ አባቶቻችን ለቅርሶች ያላቸው ግንዛቤና ቅርሶች እንዳይዘረፉ የሚያደርጉት ጥንቃቄ ያስገርማል፡፡ እንኳን ለማሳየት ያለበትንም አይጠቁሙም፡፡ በእያንዳንዱ ገዳም ውሰጥ የገጠመን ተመሳሳይ ጉዳይ ሆኖ አለፈ፡፡ ነገር ግን አብዛኞቹ ገዳማት ስጋት ቢኖርባቸውም በያዝናቸው ደብዳቤዎች እየተረዳን አሰተናግደውናል፡፡ በቅርስ ዙሪያ የሚያደርጉት ጥንቃቄ ሊበረrታ የሚገባው መሠረታዊ ጉዳይ ነው፡፡

የተፈቱና በመፈታት ላይ የሚገኙ ገዳማት ድረሱልን በማለት ላይ ናቸው፡፡ ጥሪያቸውን መስማት ብቻ ሳይሆን የማቅናትም ግዴታ እንሸከም ዘንድ ግድ ይለናል፡፡

ይቆየን፡፡

ቤተ ክርስቲያን ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ
ሚያዚያ 15 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ከጎንደር ከተማ በጎርጎራ ወደብ አድርገን ልንቃኛቸው በመረጥናቸው አምስት የጣና ሐይቅ ገዳማትን ለመዘገብ የተነሳነው ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ነው፡፡ የጀልባ ላይ ጉዞ አድርጌ አላውቅም፡፡ ነገር ግን ቅዱሳን አበውን ያፈሩ፤ በጾም በጸሎት፤ በተጋድሎ የጸኑባቸው ገዳማትን በረከት ለማግኘት፤ ታሪካቸውን ለመቃኘት ቸኩያለሁ፡፡ የጋዜጠኞቹ ቡድን በአንድነት ሆነን የ64 ኪሎ ሜትሩን መንገድ ተያያዝነው፡፡
አመሻሽ ላይ ጎርጎራ ወደብ ደረስን፡፡ የጠዋት ጉዟችንን ለማመቻቸት እንዲረዳን ወደቡ ላይ ከሚገኘው የደብረ ሲና ቅድስት ማርያም ገዳም የአባቶችን ፈቃድ በመጠየቅ የምንፈልገውን መረጃ ማሰባሰባችንን ቀጠልን፡፡ በምፈልገው አቅጣጫ ጥያቄዎችን እየጠየቅን፤ ምላሽ ከአባቶች እየተሰጠን አመሸን፡፡ አዳራችንንም እዚያው አደረግን፡፡
በጠዋት ተነስተን አንጋራ ተክለ ሃማኖት ገዳምና ብርጊዳ ቅድስት ማርያም ገዳምን ቃኝተን  ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም ስንደርስ በመምሸቱ አስፈላጊ ናቸው ያልናቸውን መረጃዎች ስናሰባስብ አደርን፡፡ በማግስቱም ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ ገዳም ዘልቀን እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ላይ ከተምን፡፡
የዛሬው የጸበል ጸዲቅ ጽሑፌ እንደ ሰሞኑ ታሪክ ላይ ያተኮረ አይደለም፡፡ በጉዟችን የቃኘናቸው የአባቶቻችን አሻራ ያረፈባቸው፤ እግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ የስልጣኔ ጫፍ የደረሰ አእምሯቸው ውጤቶች በነበሩ ነገር ግን የተፈቱና ለመፈታት በቋፍ ላይ የሚገኙት ጥንታዊ የጣና ደሴት በረከቶችን እንቃኝ ዘንድ ወደድኩ፡፡ ክፍል አራት ጸበል ጸዲቅን ተቃመሱ፡፡
አንጋራ አቡነ ተክለ ሃማኖት ገዳም፡-
አንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ለመድረስ ከደብረ ሲና ማርያም ገዳም የ20 ደቂቃ በጀልባ  የጣና ሐይቅን ማቋረጥ ይጠይቃል፡፡ በደብረ ሲና ማርያም ገዳም አገልጋይ የሆኑት ሁለት መነኮሳት አባቶች ወደ ማን እንደ አባ አቡነ ያሳይ መድኀኔዓለም ገዳም ስለሚሔዱ እንድናደርሳቸው ስለጠየቁን አብረን ለመጓዝ ተስማምተን ጸሎት አድርገውልን የጣና ሐይቅ የጀልባ ላይ ጉዞ ተጀመረ፡፡
አንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ስንደርስ ያልጠበቅነው ነገር ገጠመን፡፡ በድንጋያማው ደሴት ላይ ያረፈው ቤተ መቅደስ በዝምታ ተውጧል፡፡ አፍ አውጥቶ “የሰው ያለህ” በማለት የሚጣራ ይመስላል፡፡ በአካባቢው ሰው ዘር ያለ አይመስልም፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ስንጠጋ አንዲት ደሳሳ ጎጆ ቤት ደጃፍ ላይ አንድ አባት እድሜ ተጭኗቸው ኩርምት ብለው ተቀምጠዋል፡፡ ዓይነ ሥውር ናቸው፡፡ ዘጠና ዓመታቸው ሲሆን ወደ አንጋራ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ከመጡ 25 ዓመታታን አስቆጥረዋል፡፡
“አባታችን ስለዚህ ገዳም ታሪክና አሁን ያለበት ሁኔታ የሚነግረን ሰው እናገኝ ይሆን?” የሁላችንም ጥያቄ ነበር፡፡
“የምን ሰው?! ማን አለ ብላችሁ ነው?! ገዳሙ ሊፈታ ምንም አልቀረውም፡፡ እስቲ ወደ ታች ወረድ ብላችሁ ገበዙን ፈልጉት” አሉን፡፡
ውስጤ መረበሽ ጀመረ፡፡ ማንን እንጠይቅ? የኢየሩሳሌምን ጥፋት አታሳየኝ ያለውና እንደ ቃሉም የተፈጸመለት አቤሜሌክን አስታወስኩ፤፤ ከጓደኞቼ ገንጠል ብዬ የሚተናነቀኝን የቁጭት እንባ አፈሰስኩ፡፡ ቤተ መቅደሱ ላይ ዓይኖቼ እንደተተከሉ አባቶችን አሰብኩ፡፡ አባቶቻችን ይህንን ገዳም ሲገድሙት ምን ይመስል ነበር? በገዳማውያን አባቶች ተሞልቶ፤ መላእክትን መስለው እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑበት፤ በጸሎት አጋንንት ድል ሲነሱበት የነበረ፤ ቃል ኪዳን የተቀበሉበት ሥፍራ ምነው ዛሬ ነጠፈ?! ራሴንና ይህንን ትውልድ ተጠያቂ ከማድረግ ሌላ ምን ማለት እችላለሁ? አባቶቻችንን መስለን ያልተገኘን፤ የአባቶቻችን አደራ መሸከምም ሆነ መወጣት ያቃተን ትውልዶች እንደሆንን ተሰማኝ፡፡ ብቻዬን መሆን አማረኝ፡፡ ነገር ግን አልቻልኩም እንደተከፋሁ ከጓደኞቼ ጋር ተቀላቀልኩ፡፡ እንደ እኔው በዝምታ ቆዝመዋል፡፡  
የቤተ ክርስቲያኑን ገበዝ ከእኛ ጋር ከደብረ ሲና ቅድስት ማርያም ገዳም የመጡት መነኮሳት አባቶች ፈልገው ይዘዋቸው መጡ፡፡ በእርግና እድሜ ላይ ነው የሚገኙት፡፡ ደብዳቤያችንን አሳይተን መረጃ እንዲሰጡን ጠየቅናቸው፡፡ ታሪኩን በተደራጀ መልኩ መናገር ተሳናቸው፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን ቅድስት ቤተ ክርስተቲያንን ለትውልድ ይተላለፍ ዘንድ የከፈሉት መስዋእትነት እንደዋዛ ፈዛዛ ማለፉ ነው፡፡ ገዳሙ የእምነታችን መገለጫ የሆኑትን የአባቶቻችንን ታሪክና ቅርሶችን ታቅፎ ዝምታን መምረጡ ለምን ይሆን? ለመሆኑ ተጠያቂው ማነው? ውስጤን ሰላም ነሳኝ፡፡  
አገልጋዮቹ ከሦስት አይበልጡም፡፡ ቅዳሴ አይታሰብም፡፡ ከቀናቸው ኪዳን ያደርሳሉ፡፡ ካልሆነም በግል ጸሎት ይተጋሉ፡፡ የሚተካቸው የለም፡፡ ይህ ትውልድ ርቋቸዋል፡፡ አባቶቻችንን መምሰል፤ በቃልኪዳናቸው መጠቀምን ዘንግተን ይሆን? የወደፊት የእኛም ሆነ የተፈቱ ገዳማት እጣ ፈንታ ምን ይሆን? የቃረምነውን መረጃ ቋጥረን፤ በሐዘን አንገታችንን እንደደፋን ወደ ጀልባችን አመራን፡፡ ጉዞ ወደ ብርጊዳ ቅድስት ማርያም ገዳም፡፡
ብርጊዳ ማርያም ገዳም፡-
ወደ ብረጊዳ ማርያም ገዳም እያመራን ደሴት ስንመለከት ይህ ምንድነው ማለታችን አልቀረም፡፡ አብረውን ያሉት አባቶች ከእኛ የተሻለ መረጃ ስላላቸው የሰቀላ ሚካኤልን፤ የቅዱስ ጊዮርጊስንና የእመቤታችን ማርያም የጥንት ገዳማትን በጣታቸው እያሳዩን አለፍን፡፡ ሦስቱም ገዳማት ተፈትተው ዛሬ ሰው አልባ ሆነዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያኖቹም ፈርሰዋል፡፡ በምሰማው ነገር ታመምኩ፡፡
ብርጊዳ ማርያም ገዳምን  ከአንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ብዙም የተሻለ ነገር አለው ለማለት አያስደፍርም፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ክብ ሲሆን ዙሪያው ከመሠረቱ ጀምሮ አንድ ሜትር ያህል ከፍታ በድንጋይ ተገንብቷል፡፡ ቀሪው ክፍል በቀጫጭን ሸንበቆ የተሰራ በመሆኑ ለመፍረስ እየቃጣው ነው፡፡ ሕመሜ አገረሸ፡፡ እስኪበቃኝ አለቀስኩ፡፡ ለቅሶዬ ግን መፍትሔ ሰጪ አልነበረም፡፡ የቀድሞው ቤተ ክርስቲያን በመብረቅ ተመትቶ በመቃጠሉ ፍርስራሹ ብቻ ለታሪክ ነጋሪነት ተቀምጧል፡፡ አገልጋዮቹ ከአምስት አይበልጡም፡፡ አነስተኛ የእርሻ መሬት ከደሴቱ ወዲያ ማዶ ስላላቸው እያረሱ ይተዳደራሉ፡፡ ተተኪ ግን የላቸውም፡፡ ያገኘነውን አነስተኛ መረጃ ቋታችን ውስጥ አስገብተን ጉዟችንን ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም ቀጠልን፡፡ አዳራችንንም እዚያው ለማድረግ ተስማማን፡፡ የማን እንደ አባ ገዳምን ሁኔታ ስመለከት ደግሞ ሕመሜ በመጽናናት አስታገስኩት፡፡
ዛሬ ስለ ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም የምነግራችሁ አይኖረኝም፡፡ አንድ ነገር ብቻ ጠቁሜያችሁ ልለፍ፡፡ ገዳሙ ለሌሎች ገዳማት ምሳሌ ሊሆን የሚችልና ትክክለኛ የገዳም ገጽታና ሥርዓት የተላበሰ ስለመሆኑ ካየሁትና ከሰማሁት ነገር ተነስቼ መመስከር እችላለሁ፡፡ እግዚአብሔር ቢፈቅድ በሌላ ጊዜ እንመለስበታለን፡፡
በማግስቱ በጠዋት ወደ ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ አንድነት ገዳም የአንድ ሰዓት የሐይቅ ላይ ጉዞ ተጀመረ፡፡
ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ አንድነት ገዳም እስካሁን ካየናቸው ገዳማት በተራራማነቱ ለየት ይላል፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እየወጣን ተግባር ቤት አካባቢ ሁለት ሰዎችን አገኘን፡፡ የመጣንበትን አስረድተን መረጃ እንዲሰጡን ጠየቅናቸው፡፡ አገልጋዮቹ ሁሉም ወደ ሞፈር ቤት መሄዳቸውን ነገሩን፡፡ እነሱም የቤተ ክርስቲያኑን አባቶች የሚራዱ የአካባቢው ገበሬዎች እንደሆኑ ገለጹልን፡፡
ከመካከላቸውም አንዱ አባት ስለቤተ ክርስቲያኑ የሚያውቁትን ታሪክ ያጫወቱን ዘንድ ፈቃዳቸው ሆነ፡፡ ገዳሙ ደርቡሽ ጎንደርን በወረረበት ወቅት ገዳማትን ሲያፈርስ የየገዳማቱ ቅርሶች መሸሸጊያ ሆኗል፡፡ ደርቡሽ ሊደርስባቸው ካልቻላቸው ገዳማት አንዱ ነው፡፡ በገዳሙ በጾምና ጸሎት በመትጋት የዘጉ አባቶች መኖራቸውንና ምግባቸውንም ወደ ባእታቸው እንደሚወስዱላቸው፤ ለማንም እንደማይታዩ፤ አንዳንዴም ለሳምንት ያህል የተወሰደላቸው ምግብ ሳይቀምሱት እንደሚያገኙት ነገሩን፡፡
ያስፈልጋሉ ያልናቸውን መረጃዎች ከመሰብሰብ ወደ ኋላ አላልንም፡፡ እያንዳንዱ ጉዞ ሕመም አለው፡፡ የገዳማት የወደፊት እጣ ፈንታ ምን ይሆን እንድንል አስገድዶናል፡፡ የእያንዳንዳችን ሕሊና በምናያቸውና በምንሰማቸው ነገሮች መታመሙን ቀጥሏል፡፡
እጀበራ ማርያም ገዳም፡-
እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ለመሄድ ተነስተናል፡፡ እዚህ ደግሞ ምን ይገጥመን ይሆን?  ፍርሃት ፍርሃት አለኝ፡፡
እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ስንደርስ ቤተ ክርስቲያኑ ፈርሶ ግንባታው ተጀምሯል፡፡ ግንበኞች ድንጋይ ይከሰክሳሉ፤ ገሚሶቹ በአቅራቢያው ከሚገኘው አካባቢ በጀልባ ተጭኖ የመጣውን ድንጋይ ያራግፋሉ፡፡
ከአንዲት አነስተኛ ተግባር ቤት ውስጥ አንድ አባት አገኘን፡፡ አንድ ዛፍ ጥላ ሥር ሁላችንም ተሰባሰብን፡፡
ለተወሰኑ ደቂቃዎች ሁላችንም በዝምታ ተዋጥን፡፡ አባታችን ዝምታውን ሰብረው “ለምን መጣችሁ?” አሉን በየተራ እያንዳንዳችንን አየቃኙ፡፡
የመጣንበትን አስረዳን፡፡ ደስ አላላቸውም፡፡
እያለቀሱ የገዳማትን ችግሮች እየዘረዘሩ ይናገራሉ፡፡ በሚናገሯቸው ቃላቶች እያንዳንዳችን እየታመምን ነው፡፡ ማሳረጊያችንም በህመም ሊደመደም ሆነ፡፡
ከሃያ ዓመታት በፊት በዚሁ ገዳም ለሦስት ዓመታት መኖራቸውንና ገዳሙ ሊፈታ እንደሆነ በመስማታቸው ይህንን ለመታደግ ወደ ገዳሙ ከመጡ ገና ሦስት ወራት ብቻ እንደሆናቸው፤ የአቅማቸውን ያህል ጥረት በማድረግ ወደ ቀደመ ክብሩ ለመመለስ እየተፍጨረጨሩ እንደሚገኙ ገለጹልን፡፡ ከገዳሙ አቅራቢያ የሚገኙ ነዋሪዎችን በማስተባበር ቤተ ክርስቲያኑን በማሰራትና አንዳንድ የልማት ሥራዎችን እያስጀመሩ መሆናቸውን አስረዱን፡፡
ገዳሙ ምንም ዓይነት የልማት እንቅስቃሴ አይታይበትም፡፡ እኚህ አባት ወደፊት ከባድ ሥራ እንደሚጠብቃቸው ከሁኔታው መረዳት ይቻላል፡፡
እነዚህ ገዳማት ወደፊት ምን ይገጥማቸው ይሆን? ይፈልሱ ይሆን ወይስ ወደ ቀደመ ታላቅነታቸው ተመልሰው እናይ ይሆን? ገዳማት ከመፈታታቸው በፊት ልንደርስላቸው ግድ ይለናል፡፡ ይህ የቤት ሥራ ለእያንዳንዳችን የተቀመጠ ኃላፊነት ነው፡፡
ዝምታ እንደነገሰብን ወደ ጀልባችን አመራን፡፡ ጉዞ ወደ ጎርጎራ ወደብ፡፡
በጉዟችን አንድ ነገር አስደስቶናል፡፡ አባቶቻችን ለቅርሶች ያላቸው ግንዛቤና ቅርሶች እንዳይዘረፉ የሚያደርጉት ጥንቃቄ ያስገርማል፡፡ እንኳን ለማሳየት ያለበትንም አይጠቁሙም፡፡ በእያንዳንዱ ገዳም ውሰጥ የገጠመን ተመሳሳይ ጉዳይ ሆኖ አለፈ፡፡ ነገር ግን አብዛኞቹ ገዳማት ስጋት ቢኖርባቸውም በያዝናቸው ደብዳቤዎች እየተረዳን አሰተናግደውናል፡፡ በቅርስ ዙሪያ የሚያደርጉት ጥንቃቄ ሊበረrታ የሚገባው መሠረታዊ ጉዳይ ነው፡፡
የተፈቱና በመፈታት ላይ የሚገኙ ገዳማት ድረሱልን በማለት ላይ ናቸው፡፡ ጥሪያቸውን መስማት ብቻ ሳይሆን የማቅናትም ግዴታ እንሸከም ዘንድ ግድ ይለናል፡፡
ይቆየን፡፡
ቤተ ክርስቲያን ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ
ሚያዚያ 15 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ከጎንደር ከተማ በጎርጎራ ወደብ አድርገን ልንቃኛቸው በመረጥናቸው አምስት የጣና ሐይቅ ገዳማትን ለመዘገብ የተነሳነው ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ነው፡፡ የጀልባ ላይ ጉዞ አድርጌ አላውቅም፡፡ ነገር ግን ቅዱሳን አበውን ያፈሩ፤ በጾም በጸሎት፤ በተጋድሎ የጸኑባቸው ገዳማትን በረከት ለማግኘት፤ ታሪካቸውን ለመቃኘት ቸኩያለሁ፡፡ የጋዜጠኞቹ ቡድን በአንድነት ሆነን የ64 ኪሎ ሜትሩን መንገድ ተያያዝነው፡፡
አመሻሽ ላይ ጎርጎራ ወደብ ደረስን፡፡ የጠዋት ጉዟችንን ለማመቻቸት እንዲረዳን ወደቡ ላይ ከሚገኘው የደብረ ሲና ቅድስት ማርያም ገዳም የአባቶችን ፈቃድ በመጠየቅ የምንፈልገውን መረጃ ማሰባሰባችንን ቀጠልን፡፡ በምፈልገው አቅጣጫ ጥያቄዎችን እየጠየቅን፤ ምላሽ ከአባቶች እየተሰጠን አመሸን፡፡ አዳራችንንም እዚያው አደረግን፡፡
በጠዋት ተነስተን አንጋራ ተክለ ሃማኖት ገዳምና ብርጊዳ ቅድስት ማርያም ገዳምን ቃኝተን  ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም ስንደርስ በመምሸቱ አስፈላጊ ናቸው ያልናቸውን መረጃዎች ስናሰባስብ አደርን፡፡ በማግስቱም ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ ገዳም ዘልቀን እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ላይ ከተምን፡፡
የዛሬው የጸበል ጸዲቅ ጽሑፌ እንደ ሰሞኑ ታሪክ ላይ ያተኮረ አይደለም፡፡ በጉዟችን የቃኘናቸው የአባቶቻችን አሻራ ያረፈባቸው፤ እግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ የስልጣኔ ጫፍ የደረሰ አእምሯቸው ውጤቶች በነበሩ ነገር ግን የተፈቱና ለመፈታት በቋፍ ላይ የሚገኙት ጥንታዊ የጣና ደሴት በረከቶችን እንቃኝ ዘንድ ወደድኩ፡፡ ክፍል አራት ጸበል ጸዲቅን ተቃመሱ፡፡
አንጋራ አቡነ ተክለ ሃማኖት ገዳም፡-
አንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ለመድረስ ከደብረ ሲና ማርያም ገዳም የ20 ደቂቃ በጀልባ  የጣና ሐይቅን ማቋረጥ ይጠይቃል፡፡ በደብረ ሲና ማርያም ገዳም አገልጋይ የሆኑት ሁለት መነኮሳት አባቶች ወደ ማን እንደ አባ አቡነ ያሳይ መድኀኔዓለም ገዳም ስለሚሔዱ እንድናደርሳቸው ስለጠየቁን አብረን ለመጓዝ ተስማምተን ጸሎት አድርገውልን የጣና ሐይቅ የጀልባ ላይ ጉዞ ተጀመረ፡፡
አንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ስንደርስ ያልጠበቅነው ነገር ገጠመን፡፡ በድንጋያማው ደሴት ላይ ያረፈው ቤተ መቅደስ በዝምታ ተውጧል፡፡ አፍ አውጥቶ “የሰው ያለህ” በማለት የሚጣራ ይመስላል፡፡ በአካባቢው ሰው ዘር ያለ አይመስልም፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ስንጠጋ አንዲት ደሳሳ ጎጆ ቤት ደጃፍ ላይ አንድ አባት እድሜ ተጭኗቸው ኩርምት ብለው ተቀምጠዋል፡፡ ዓይነ ሥውር ናቸው፡፡ ዘጠና ዓመታቸው ሲሆን ወደ አንጋራ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ከመጡ 25 ዓመታታን አስቆጥረዋል፡፡
“አባታችን ስለዚህ ገዳም ታሪክና አሁን ያለበት ሁኔታ የሚነግረን ሰው እናገኝ ይሆን?” የሁላችንም ጥያቄ ነበር፡፡
“የምን ሰው?! ማን አለ ብላችሁ ነው?! ገዳሙ ሊፈታ ምንም አልቀረውም፡፡ እስቲ ወደ ታች ወረድ ብላችሁ ገበዙን ፈልጉት” አሉን፡፡
ውስጤ መረበሽ ጀመረ፡፡ ማንን እንጠይቅ? የኢየሩሳሌምን ጥፋት አታሳየኝ ያለውና እንደ ቃሉም የተፈጸመለት አቤሜሌክን አስታወስኩ፤፤ ከጓደኞቼ ገንጠል ብዬ የሚተናነቀኝን የቁጭት እንባ አፈሰስኩ፡፡ ቤተ መቅደሱ ላይ ዓይኖቼ እንደተተከሉ አባቶችን አሰብኩ፡፡ አባቶቻችን ይህንን ገዳም ሲገድሙት ምን ይመስል ነበር? በገዳማውያን አባቶች ተሞልቶ፤ መላእክትን መስለው እግዚአብሔርን ሲያመሰግኑበት፤ በጸሎት አጋንንት ድል ሲነሱበት የነበረ፤ ቃል ኪዳን የተቀበሉበት ሥፍራ ምነው ዛሬ ነጠፈ?! ራሴንና ይህንን ትውልድ ተጠያቂ ከማድረግ ሌላ ምን ማለት እችላለሁ? አባቶቻችንን መስለን ያልተገኘን፤ የአባቶቻችን አደራ መሸከምም ሆነ መወጣት ያቃተን ትውልዶች እንደሆንን ተሰማኝ፡፡ ብቻዬን መሆን አማረኝ፡፡ ነገር ግን አልቻልኩም እንደተከፋሁ ከጓደኞቼ ጋር ተቀላቀልኩ፡፡ እንደ እኔው በዝምታ ቆዝመዋል፡፡ 
የቤተ ክርስቲያኑን ገበዝ ከእኛ ጋር ከደብረ ሲና ቅድስት ማርያም ገዳም የመጡት መነኮሳት አባቶች ፈልገው ይዘዋቸው መጡ፡፡ በእርግና እድሜ ላይ ነው የሚገኙት፡፡ ደብዳቤያችንን አሳይተን መረጃ እንዲሰጡን ጠየቅናቸው፡፡ ታሪኩን በተደራጀ መልኩ መናገር ተሳናቸው፡፡ ቅዱሳን አባቶቻችን ቅድስት ቤተ ክርስተቲያንን ለትውልድ ይተላለፍ ዘንድ የከፈሉት መስዋእትነት እንደዋዛ ፈዛዛ ማለፉ ነው፡፡ ገዳሙ የእምነታችን መገለጫ የሆኑትን የአባቶቻችንን ታሪክና ቅርሶችን ታቅፎ ዝምታን መምረጡ ለምን ይሆን? ለመሆኑ ተጠያቂው ማነው? ውስጤን ሰላም ነሳኝ፡፡ 
አገልጋዮቹ ከሦስት አይበልጡም፡፡ ቅዳሴ አይታሰብም፡፡ ከቀናቸው ኪዳን ያደርሳሉ፡፡ ካልሆነም በግል ጸሎት ይተጋሉ፡፡ የሚተካቸው የለም፡፡ ይህ ትውልድ ርቋቸዋል፡፡ አባቶቻችንን መምሰል፤ በቃልኪዳናቸው መጠቀምን ዘንግተን ይሆን? የወደፊት የእኛም ሆነ የተፈቱ ገዳማት እጣ ፈንታ ምን ይሆን? የቃረምነውን መረጃ ቋጥረን፤ በሐዘን አንገታችንን እንደደፋን ወደ ጀልባችን አመራን፡፡ ጉዞ ወደ ብርጊዳ ቅድስት ማርያም ገዳም፡፡
ብርጊዳ ማርያም ገዳም፡-
ወደ ብረጊዳ ማርያም ገዳም እያመራን ደሴት ስንመለከት ይህ ምንድነው ማለታችን አልቀረም፡፡ አብረውን ያሉት አባቶች ከእኛ የተሻለ መረጃ ስላላቸው የሰቀላ ሚካኤልን፤ የቅዱስ ጊዮርጊስንና የእመቤታችን ማርያም የጥንት ገዳማትን በጣታቸው እያሳዩን አለፍን፡፡ ሦስቱም ገዳማት ተፈትተው ዛሬ ሰው አልባ ሆነዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያኖቹም ፈርሰዋል፡፡ በምሰማው ነገር ታመምኩ፡፡
ብርጊዳ ማርያም ገዳምን  ከአንጋራ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ብዙም የተሻለ ነገር አለው ለማለት አያስደፍርም፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ ክብ ሲሆን ዙሪያው ከመሠረቱ ጀምሮ አንድ ሜትር ያህል ከፍታ በድንጋይ ተገንብቷል፡፡ ቀሪው ክፍል በቀጫጭን ሸንበቆ የተሰራ በመሆኑ ለመፍረስ እየቃጣው ነው፡፡ ሕመሜ አገረሸ፡፡ እስኪበቃኝ አለቀስኩ፡፡ ለቅሶዬ ግን መፍትሔ ሰጪ አልነበረም፡፡ የቀድሞው ቤተ ክርስቲያን በመብረቅ ተመትቶ በመቃጠሉ ፍርስራሹ ብቻ ለታሪክ ነጋሪነት ተቀምጧል፡፡ አገልጋዮቹ ከአምስት አይበልጡም፡፡ አነስተኛ የእርሻ መሬት ከደሴቱ ወዲያ ማዶ ስላላቸው እያረሱ ይተዳደራሉ፡፡ ተተኪ ግን የላቸውም፡፡ ያገኘነውን አነስተኛ መረጃ ቋታችን ውስጥ አስገብተን ጉዟችንን ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም ቀጠልን፡፡ አዳራችንንም እዚያው ለማድረግ ተስማማን፡፡ የማን እንደ አባ ገዳምን ሁኔታ ስመለከት ደግሞ ሕመሜ በመጽናናት አስታገስኩት፡፡
ዛሬ ስለ ማን እንደ አባ ያሳይ መድኀኔዓለም አንድነት ገዳም የምነግራችሁ አይኖረኝም፡፡ አንድ ነገር ብቻ ጠቁሜያችሁ ልለፍ፡፡ ገዳሙ ለሌሎች ገዳማት ምሳሌ ሊሆን የሚችልና ትክክለኛ የገዳም ገጽታና ሥርዓት የተላበሰ ስለመሆኑ ካየሁትና ከሰማሁት ነገር ተነስቼ መመስከር እችላለሁ፡፡ እግዚአብሔር ቢፈቅድ በሌላ ጊዜ እንመለስበታለን፡፡
በማግስቱ በጠዋት ወደ ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ አንድነት ገዳም የአንድ ሰዓት የሐይቅ ላይ ጉዞ ተጀመረ፡፡
ደብረ ገሊላ ኢየሱስ ወአቡነ ዘካርያስ አንድነት ገዳም እስካሁን ካየናቸው ገዳማት በተራራማነቱ ለየት ይላል፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ እየወጣን ተግባር ቤት አካባቢ ሁለት ሰዎችን አገኘን፡፡ የመጣንበትን አስረድተን መረጃ እንዲሰጡን ጠየቅናቸው፡፡ አገልጋዮቹ ሁሉም ወደ ሞፈር ቤት መሄዳቸውን ነገሩን፡፡ እነሱም የቤተ ክርስቲያኑን አባቶች የሚራዱ የአካባቢው ገበሬዎች እንደሆኑ ገለጹልን፡፡
ከመካከላቸውም አንዱ አባት ስለቤተ ክርስቲያኑ የሚያውቁትን ታሪክ ያጫወቱን ዘንድ ፈቃዳቸው ሆነ፡፡ ገዳሙ ደርቡሽ ጎንደርን በወረረበት ወቅት ገዳማትን ሲያፈርስ የየገዳማቱ ቅርሶች መሸሸጊያ ሆኗል፡፡ ደርቡሽ ሊደርስባቸው ካልቻላቸው ገዳማት አንዱ ነው፡፡ በገዳሙ በጾምና ጸሎት በመትጋት የዘጉ አባቶች መኖራቸውንና ምግባቸውንም ወደ ባእታቸው እንደሚወስዱላቸው፤ ለማንም እንደማይታዩ፤ አንዳንዴም ለሳምንት ያህል የተወሰደላቸው ምግብ ሳይቀምሱት እንደሚያገኙት ነገሩን፡፡
ያስፈልጋሉ ያልናቸውን መረጃዎች ከመሰብሰብ ወደ ኋላ አላልንም፡፡ እያንዳንዱ ጉዞ ሕመም አለው፡፡ የገዳማት የወደፊት እጣ ፈንታ ምን ይሆን እንድንል አስገድዶናል፡፡ የእያንዳንዳችን ሕሊና በምናያቸውና በምንሰማቸው ነገሮች መታመሙን ቀጥሏል፡፡
እጀበራ ማርያም ገዳም፡-
እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ለመሄድ ተነስተናል፡፡ እዚህ ደግሞ ምን ይገጥመን ይሆን?  ፍርሃት ፍርሃት አለኝ፡፡
እጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳም ስንደርስ ቤተ ክርስቲያኑ ፈርሶ ግንባታው ተጀምሯል፡፡ ግንበኞች ድንጋይ ይከሰክሳሉ፤ ገሚሶቹ በአቅራቢያው ከሚገኘው አካባቢ በጀልባ ተጭኖ የመጣውን ድንጋይ ያራግፋሉ፡፡
ከአንዲት አነስተኛ ተግባር ቤት ውስጥ አንድ አባት አገኘን፡፡ አንድ ዛፍ ጥላ ሥር ሁላችንም ተሰባሰብን፡፡
ለተወሰኑ ደቂቃዎች ሁላችንም በዝምታ ተዋጥን፡፡ አባታችን ዝምታውን ሰብረው “ለምን መጣችሁ?” አሉን በየተራ እያንዳንዳችንን አየቃኙ፡፡
የመጣንበትን አስረዳን፡፡ ደስ አላላቸውም፡፡
እያለቀሱ የገዳማትን ችግሮች እየዘረዘሩ ይናገራሉ፡፡ በሚናገሯቸው ቃላቶች እያንዳንዳችን እየታመምን ነው፡፡ ማሳረጊያችንም በህመም ሊደመደም ሆነ፡፡
ከሃያ ዓመታት በፊት በዚሁ ገዳም ለሦስት ዓመታት መኖራቸውንና ገዳሙ ሊፈታ እንደሆነ በመስማታቸው ይህንን ለመታደግ ወደ ገዳሙ ከመጡ ገና ሦስት ወራት ብቻ እንደሆናቸው፤ የአቅማቸውን ያህል ጥረት በማድረግ ወደ ቀደመ ክብሩ ለመመለስ እየተፍጨረጨሩ እንደሚገኙ ገለጹልን፡፡ ከገዳሙ አቅራቢያ የሚገኙ ነዋሪዎችን በማስተባበር ቤተ ክርስቲያኑን በማሰራትና አንዳንድ የልማት ሥራዎችን እያስጀመሩ መሆናቸውን አስረዱን፡፡
ገዳሙ ምንም ዓይነት የልማት እንቅስቃሴ አይታይበትም፡፡ እኚህ አባት ወደፊት ከባድ ሥራ እንደሚጠብቃቸው ከሁኔታው መረዳት ይቻላል፡፡
እነዚህ ገዳማት ወደፊት ምን ይገጥማቸው ይሆን? ይፈልሱ ይሆን ወይስ ወደ ቀደመ ታላቅነታቸው ተመልሰው እናይ ይሆን? ገዳማት ከመፈታታቸው በፊት ልንደርስላቸው ግድ ይለናል፡፡ ይህ የቤት ሥራ ለእያንዳንዳችን የተቀመጠ ኃላፊነት ነው፡፡
ዝምታ እንደነገሰብን ወደ ጀልባችን አመራን፡፡ ጉዞ ወደ ጎርጎራ ወደብ፡፡
በጉዟችን አንድ ነገር አስደስቶናል፡፡ አባቶቻችን ለቅርሶች ያላቸው ግንዛቤና ቅርሶች እንዳይዘረፉ የሚያደርጉት ጥንቃቄ ያስገርማል፡፡ እንኳን ለማሳየት ያለበትንም አይጠቁሙም፡፡ በእያንዳንዱ ገዳም ውሰጥ የገጠመን ተመሳሳይ ጉዳይ ሆኖ አለፈ፡፡ ነገር ግን አብዛኞቹ ገዳማት ስጋት ቢኖርባቸውም በያዝናቸው ደብዳቤዎች እየተረዳን አሰተናግደውናል፡፡ በቅርስ ዙሪያ የሚያደርጉት ጥንቃቄ ሊበረrታ የሚገባው መሠረታዊ ጉዳይ ነው፡፡
የተፈቱና በመፈታት ላይ የሚገኙ ገዳማት ድረሱልን በማለት ላይ ናቸው፡፡ ጥሪያቸውን መስማት ብቻ ሳይሆን የማቅናትም ግዴታ እንሸከም ዘንድ ግድ ይለናል፡፡
ይቆየን፡፡