Beke 1

በችግር ላይ የሚገኘው የበኬ ቅድስት ማርያም የአብነት ትምህርት ቤት እርዳታ ተደረገለት፡፡

ጥር 5/2004 ዓ.ም

በይበልጣል ሙላት
Beke 1

በአዲስ አበባ ማእከል ማኅበራዊና ልማት ክፍል የተዘጋጀ ጉዞ ወደ በኬ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የአብነት ትምህርት ቤት የተካሔደ ሲሆን የጉዞውም ዋነኛ አላማ በአስከፊ ሁኔታ ላይ ለሚገኙት ለደብሯ የአብነት መምህራንና ተማሪዎች ጊዜያዊ የቁሳቁስ እርዳታ /ድጋፍ/ ለማድረግ እንደሆነ ተነግሯል፡፡

በጉዞውም በክፍሉ አስተባባሪነት ከምእመናንና ከማኅበሩ አባላት የተሰበሰቡና የተዘጋጁ  11 ኩንታል ስንዴ ዱቄት፣ 230 ሱሪ፣ 398 ሹራብና ቲሸርት፣ 145 ኮትና ጃኬት፣ 25 የአልጋ ልብስና አንሶላ፣ 43 የተለያዩ ልብሶች፣ 230 ግራም 249 የልብስ ሳሙና እና ለመማሪያ የሚሆኑ 11 መጻሕፍት ተበርክተዋል፡፡

በአሁኑ ሰዓት በአብነት ትምህርት ቤቱ ከ160 በላይ ተማሪዎች በ3ቱ ጉባኤያት ማለትም በቅዳሴ፣ የአቋቋም እና የቅኔ ትምህርት በመማር ላይ የሚገኙ ሲሆን ከቅርብ ጊዜBeke 3  (1) በፊት ቁጥራቸው 300 ይደርስ እንደነበር የገለጹት በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት አባ ገ/አማኑኤል አሮጌ አያኔ እንዲህ ቁጥራቸው ሊቀንስ የቻለው በአብነት ትምህርት ቤቱ ባለው ስር የሰደደ ችግር እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ በፊትም ሆነ አሁን ተማሪዎቹ ሲማሩ የነበሩትና በመማር ላይ የሚገኙት የቀን ሥራ እየሠሩ ሲሆን ምንም ዓይነት የገቢ ምንጭ እንደሌላቸውና ሲያገኙ በልተው ሲያጡ ጾማቸውን እያደሩ እንደሚማሩ ገልጸዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ጥሙን እርዛቱን መቋቋም ያልቻሉ ትምህርታቸውን እያቋረጡ የተሻለ እናገኛለን እያሉ መሔዳቸውን የደብሩ አስተዳዳሪ ገልጸው አያይዘውም በቦታው የድጓ መምህርና ተማሪዎች የነበሩ ሲሆን  ማለትም በምግብ፣ በልብስ፣ በመጠለያ ችግር ምክንያት ጉባኤው ሊበተን እንደቻለ አስታውሰዋል፡፡ ችግሩ በዚሁ ከቀጠለ አሁንም በመካሔድ ላይ ያሉት በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ልክ እንደ ድጓው ቁጥራቸው ቀንሶ የማይችልበት ምንም ምክንያት እንደማይኖር አስገንዝበዋል፡፡ ስለዚህ የሚመለከተው ሁሉ ከላይም ከታችም ከሊቅ እስከ ደቂቅ በጋራ ሁነን ይህ የቤተ ክርስቲያናችን ጌጥ፣ ምንጭ የሆነውን የአብነት ትምህርት ቤት በተለይም በአሁኑ ሰዓት በአስከፊ ሁኔታ ላይ ለሚገኘው ለበኬ ቅድስት ማርያም አብነት ትምህርት ቤት ልንደርስለትና ዘላቂ መፍትሔ እንዲፈለግለት በአብነት ትምህርት ቤቱ መምህራንና ተማሪዎች እንዲሁም በቤተ ክርስቲያን ስም ተማጽኖአቸውን አቅርበዋል፡፡

Beke 4ይህንንም ጥሪ ሰምቶና አጣርቶ የአዲስ አበባ ማእከል ማኅበራዊና ልማት ክፍል ከምእመኑና የማኅበሩ አባላት ጋር በመሆን ከላይ የተጠቀሰውን ጊዜያዊ ድጋፍ እንዳደረጉ የክፍሉ ተጠሪ ወ/ሪት መቅደስ አለሙ ገልጸዋል፡፡ ለወደፊትም የአብነት ትምህርቱን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ከምእመኑና አባላቱ እና ድጋፍ ሰጪ አካላት ጋር በመተባበር ትልቅ የጉዞ መርሐ ግብር እንደሚያዘጋጅና ቋሚ ፕሮጀክት በመቅረጽ የአብነት ትምህርት ቤቱን የመጠለያና የምግብ ችግር ለመፍታት በመንቀሳቀስ ላይ እንዳለ የገለጹት የክፍሉ ተጠሪ  አያይዘውም ምእመኑና ድጋፍ ሰጭ አካላት በዚህ የተቀደሰ አላማ እንዲሳተፉ አሳስበዋል፡፡

ከርክክቡ በኋላ ዐሳባቸውን የገለጹት አንዳንድ መምህራንና ተማሪዎች በተደረገላቸው ነገር ሁሉ መደሰታቸውን ነው፡፡

 

Beke 3  (2)የደብሩ የአቋቋም መምህር የሆኑ አባት ይህ የተደረገላቸው ድጋፍ በጣም ከመጠን በላይ እንዳስደሰታቸውና ለመግለጽ ቃላት እንደሚያጥራቸው ገልጸው ይህን ነገር እግዚአብሔር ተመልክቶ የበለጠ እንድትሠሩ ያደርጋል፤ ብለው አያይዘውም በቋሚነት ችግራቸው የሚፈታበትን መንገድ እንዲፈለግ ተማጽነዋል፡፡

 

የቅዳሴ ተማሪ የሆኑት አክሊለ ማርያም ይህ ከስጦታ ሁሉ በላይ እንደሆነና ከሁሉም በላይ ያስደሰታቸው የክርስቲያናዊ ወንድማማችነቱ የመጠያየቁ የአብሮነቱ እንዲሁም የመተሳሰቡ  ስሜት እንደሆነና ይህን ከላይ ከቤተ ክህነት ነበር የምንጠብቀው ብለው ተስፋችን ለምልሟል ልባችንም አርፏል በማለት ስሜታቸውን አጋርተዋል፡፡ አያይዘውም ለወደፊቱ በቋሚነት ልባችን ተረጋግቶ ጸንተን የምንማርበት ሁኔታ እንዲታሰብበት እና ዘላቂ መፍትሔ የሚመጣበት ሁኔታ እንዲፈጠር ተማጽነዋል፡፡

 

በአጠቃላይ የአብነት ትምህርት ቤት ችግር የቤተ ክርስቲያን ችግር የቤተ ክርስቲያን የመኖርና ያለመኖር፣ የመሠረተ እምነቷ ችግር መሆኑን አውቆ ሁሉም የዚህ የአብነት ትምህርት ቤት ችግር እንዲቀረፍ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክትየአዲስ አበባ ማእከል ማኅበራዊና ልማት ክፍል አስተባባሪዋ አሳስበዋል፡፡

lideteEgzie

እድለኞቹ እረኞች /ለሕፃናት/

ጥር 3/2004 ዓ.ም

በእኅተ ፍሬስብሐት
lideteEgzie
በአንድ ምሽት በቤተለሔም አካባቢ እረኞች በጎቻቸውን ተኩላዎች እንዳይበሉባቸው ይጠብቁ ነበር፡፡ እኩለ ሌሊት ሲሆን በዚያ አካባቢ ልዩ ብርሃን ታየ፡፡ እረኞቹ ያንን ብርሃን ሲያዩ በጣም ተገረሙ፡፡ በዚያም መልአክ መጣ እና በዚያች ሌሊት የዓለም መድኀኒት የሚሆን ሕፃን መወለዱን፤ ያም ሕፃን የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ለእረኞቹ ነገራቸው፡፡ እረኞቹም ተደሰቱ ፈጥነው ሕፃኑ ወደ ተወለደበት ወደ ቤተልሔም ሔዱ፡፡ መልአኩ ቦታውን ነግሯቸው ነበር፡፡ በዚያም ሲደርሱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሕፃኑን ታቅፋ አገኟት፡፡ በአጠገቧም አንድ ሽማግሌ ሰው ቆሞ ነበር፡፡ ያ ሽማግሌ እመቤታችንን ይጠብቃት የነበረው ዮሴፍ ነበር፡፡ እረኞቹም ወደ ሕፃኑ ቀርበው ሰገዱለት ምስጋናም አቀረቡ፡፡

መካነ ጉባኤያት ወላዴ ሊቃዉንት ደብረ ሃይማኖት መካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ዕድሳት ሊደረግለት ነዉ፡፡

ታኅሣሥ 27/2004 ዓ.ም

በእንዳለ ደምስስ
  • ለዕድሳቱ 1.5 ሚሊዮን ብር ያስፈልጋል፡፡

frontመካነ ጉባኤያት የሆነዉን ታሪካዊዉንና ጥንታዊዉን ደብረ ሃይማኖት መካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ለማደስ የገቢ ማሰባሰቢያ ጉባኤ ተካሔደ፡፡ታኅሣሥ 22 ቀን 2004 ዓ.ም . በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሁለገብ አዳራሽ በተካሄደዉ በዚህ ጉባኤ የአራቱ ጉባኤያት የትርጓሜ መምህር የሆኑት ሊቀ ሊቃዉንት ዕዝራ ሐዲስና የደብረ ሃይማኖት መካነ ኢየሱስ አስተዳዳሪና የድጓ መምህር የሆኑት መልአከ ሃይማኖት ሲሳይ አሰፋ ጉባኤያቸዉን ትተዉ የተገኙበት ሲሆን፣ ከአዲስ አበባም በአሁኑ ጊዜ የሊቃዉንት ጉባኤ ሰብሳቢ የሆኑት መልአከ ሰላም ዐምደ ብርሃን እና  መልአከ ታቦር ተሾመ ዘሪሁን፣ ሊቀ ስዩማን ራደ አስረስና ሌሎች የሊቃዉንት ጉባኤ አባላት እንዲሁ ም በሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳዉሎስ ከፍተኛ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ መምህር የሆኑትን መጋቤ ሐዲስ ስቡሕ አዳምጤን ጨምሮ በቦታዉ የተማሩና የጉባኤ ቤቱን ታሪክ የሚያዉቁ በርካታ ሊቃዉንት በጉባኤዉ ላይ ተገኝተዋል፡፡

 

 

በጉባኤዉ ላይ ዲያቆን ያረጋል አበጋዝና ሊቀ ሊቃዉን ዕዝራ ሐዲስ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል፡፡የቦታዉ የድጓ መምህርና የቤተ ክርስቲያኑ አgubae z mekane Eyesus 047ስተዳዳሪ መልአከ ሃይማኖት ሲሳይ አሰፋ አጂግ በሚመስጠዉ ድምጻቸዉ ያሬዳዊ ወረቦችን ሲያንቆረቆሩ ሊቃዉንቱን ሁሉ አስደምመዋል፡፡

የቀዳሜ ዜማ ሊቃዉንት ማኅበር አባላት የሆኑት ሊቃዉንተ ቤተ ክርስቲያን፣ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም ሰንበት ትምህርት ቤትgubae z mekane Eyesus 118 መዘምራን ልምላሜ ነፍስ የሚያስገኙ ወረቦችን አቅርበዋል፡፡ የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ጎልማሶች ጉባኤ መዘምራንና ዲያቆን ምንዳዬ ብርሃኑም ሕዝቡን ያሳተፉ ጥዑም ዝማሬዎችን አሰምተዋል፡፡ ጉባኤዉ ከላይ ከተገለጹት መርሐ ግብራት በተጨማሪ የቦታዉን መልክአ ምድራዊ አቀማመጥ፣ ቤተ ክርስቲያኑን፣ አብያተ ጉባኤያቱንና የክብረ በዓል ሥርዓቱን የሚያሳይ 10 ደቂቃ ቪዲዮ ከቀረበ በኋላ  በሊቀ ስዩማን ራደ አስረስና በመልአከ ታቦር ተሾመ ዘሪሁን ከቦታዉ ተምረዉ ለታላቅ መዓርግ ስለበቁት ሊቃዉንትና ስለ ጉባኤቤቱና ስለ ቤተ ክርስቲያኑ ታሪክ ሰፊ ገለጻ ቀርቧል፡፡

 

በዐጼ አድያም ሰገድ ኢያሱ ዘመነ መንግሥት የተተከለዉ ጥንታዊዉና ታሪካዊዉ ደብረ ሃማኖት መካነ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን በሦስት ታላላቅ ጉባኤያቱ የታወቀ ነበር፡፡በቅዱሳት መጻሕፍት ትርጓሜ ቤተ ጉባኤ፣ በቅኔ ቤተ ጉባኤ እና በድጓ ቤተ ጉባኤ፡፡በሦስቱም አብያተ ጉባኤያት ታላላቅ ሊቃዉንትን ለሀገሪቱም ሆነ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ሲያበረክት የቆየዉ ይህ ታሪካዊ ቦታ እስከ 1950ዎቹ ሦስቱም ጉባኤያት የነበሩት ቢሆንም በአሁኑ ጊዜ ግን የቅኔ ጉባኤ ቤቱ ታጥፎ የትርጓሜ መጻሕፍቱና የድጓ ጉባኤዎቹ ግን አሁንም ሳይታጎሉ የሚሰጥበት ቦታ ነዉ፡፡

ቤተ ክርስቲያኑ በንግሥተ ንግሥታት ዘዉዲቱ ዘመን በጥሩ ሁኔታ በዘመናዊ መንገድ ተሠርቶ ከተጠናቀቀ በኋላ ወዲያዉኑ ጠላት (ጣልያን) ወደ ሀገራችን በመግባቱ ምክንያት ቤተ ክርስቲያኑ ተቃጥሎ ነበር፡፡ በጊዜዉ በአካባቢዉ ከነበሩት ስዉራን አበዉ አንዱ በግንቦት ወር መጀመሪያ ላይ ተገልጠዉ በ 7 እሳት ይወgubae z mekane Eyesus 018ርዳል እያሉ ትንቢት ሲናገሩ የሰሙት አበዉ ታቦታቱን መጻሓፍቱንና ንዋያተ ቅድሳቱን በሙሉ ይዘዉ በአቅራቢያዉ ወደምትገኘዉ ዋሻ ማርያም የምትባል የዋሻ ዉስጥ ቤተ ክርስቲያን አስገቡት፡፡ እንደ ተነገረዉም በተጠቀሰዉ ቀን ጣሊያን አካባቢዉንና ቤተ ክርስቲያኑን ሲያቃጥል የተጠቀሱት ንብረቶች በሙሉ ከዉድመት ዳኑ፡፡ ጣልያን ድል ተነሥቶ ከሀገር እስኪወጣ ድረስም ለሦስተ ዐመታት ያህል በዚያ ዋሻ ዉስጥ ተቀምጦ ሊቃዉንቱና ማኅበሩም በየዐመቱ የልደትን በዓል በዚያ ዋሻ ዉስጥ በሐዘን ሲያከብሩ አሳልፈዋል፡፡ እንደ ሊቀ ስዩማን ራደ አስረስ ገለጻ የመልክአ ኢየሱስ ነግሦች ከሆኑት (ከሚወረቡት) የመጨረሻ የሆነዉ ከምዕራጉ ‹‹ኢየሱስ ክርስቶስ ሊቀ ካህናቲነ፣ አስተጋብአነ ኀበ ትረፍቅ መካነ፤ እስመ ዝርዋን አግብርቲከ ንህነ›› በለቅሶና በሐዘን ይወረብ ነበርና ሐዘኑና ሱባኤዉ ጠላት ጣሊያንን ለመመለስ ጠቅሟል፡፡ ጣሊያን ከሀገራችን ከወጣ በኋላ በመቃረቢያ ታቦቱ ገብቶ መምህራኑም ጉባኤያቸዉን ተክለዉ ጥቂት ዐመታት እንደቆየ በቦታዉ ላይ የትርጓሜ መምህር በነበሩትና ከጠላት መመለስ በኋላ ከመጀመሪያዎቹ ጳጳሳት አንዱ በነበሩት የጥንቱ አቡነ ሚካኤል ( የቅዳሴ ትርጓሜን አዘጋጅተዉ ያሳተሙት) አሳሳቢነትና አስተባባሪነትም ጭምር በንጉሡ በዐፄ ኃይለ ሥላሴ ፈቃድ እንደገና አሁን በሚታየዉ መልኩ ተሠርቶ በእግዚአብሔር ቸርነት ተጠናቀቀ፡፡

ይህ አሁን ያለዉ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ግንባታዉ ከተጀመረ ከአንድ ዐመት በኋላ ራሳቸዉ ንጉሠ ነገሥቱ እቦታዉ ድረስ ሄደዉ ግንባታዉንም በቦታዉ ተቀምጠዉ በማሰራት ላይ የነበሩትን ብጹዕ አቡነ ሚካኤልንም አይተዉ ተመልሰዋል፡፡በጊዜዉ በቦታዉ ላይ ቅኔዉንና ትርጓሜ መጻሕፍቱን አንድ ላይ አድርገዉ ያስተምሩ የነበሩት እጅግ ስመ ጥር የነበሩት የኔታ  ገብረ ጊዮርጊስ ነበር፡፡ በዚህ ወቅት በድጓ ቤት ያሉትን ሳይጨምር ከ450 በላይ የቅኔና የትርጓሜ መጻሕፍት ተማሪዎች የነበሩበት ጊዜ ነበር፡፡

ይህ አሁን ያለዉ ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሞ በሚመረቅበት ጊዜ ደግሞ ንጉሠ ነገሥቱ ተጠብቀዉ ባይገኙም የጎንደሩ ገዥ ደጃዝማች ክፍሌ ዳዲ እና   የዚያን ጊዜዉ ጳጳስ የኋላዉ ፓትርያርክ አቡነ ቴዎፍሎስና ታላቁ አቡነ ዮሐንስ ከሌሎች የጊዜዉ የመንግሥት ባለ ሥልጣናትና ሊቃዉንተ ቤተ ክርስቲያን ጋር ተገኝተዉ እንደነበርም ተገልጾአል፡፡

Beataደብረ ሃይማኖት መካነ ኢየሱስ የሃይማኖት አባቶችን ለሀገሪቱ ከማበርከቱም በላይ በኢትዮጵያ ካቶሊኮች ገብተዉ ከወጡበት የጥንቱ ጊዜ በኋላ መልኩን ቀይሮ የቤተ ክርስቲያን ሊቃዉንትን ሲያበጣብጥ የቆየዉ የቅባትና የጸጋ ሰርጎ ገብ ፈጽሞ ካልረገጣቸዉ የሰሜን ኢትዮጵያ የትርጓሜ ትምህርት ቤቶች አንዱ መሆኑ በሊቃዉንቱ በተደጋጋሚ ተመስክሮለታል፡፡የደብሩ አስተዳዳሪና የድጓ መምህር መልአከ ሃይማኖት ሲሳይ አሰፋ በታሪክ የሚታወሱትን ሊቃዉንት ሲያወሱ የታች ቤት ትርጓሜ መሥራች የሚባሉት መምህር ኤስድሮስ የዚህ ቦታ መምህር እንደ ነበሩና ጣና ገብተዉ መጻሕፍትን መርምረዉ የታች ቤቱን ትርጓሜ ጎንደር ልደታ ላይ ከማስተማራቸዉ በፊት መካነ ኢየሱስ ላይ ተምረዉ ከዚያም ወንበሩን ተረክበዉ ማስተማራቸዉንና በኋላም መጥተዉ በቦታዉ ጥቂት ጊዜያትን ከቆዩ በኋላ እዚያዉ አርፈዉ መቀበራቸዉን አስረድተዋል፡፡ የቦታዉን ታላቅነት አስመልክቶ በሊቃዉንቱ ዘንድ ብዙ የሚነገርለት መሆኑን ያወሱት መልአከ ታቦር ተሾመ ዘሪሁንም በታላቁ ሊቅ የኔታ ገብረ ጊዮርጊስ ከተቀኙት መወድስ ዉስጥ ፤

‹‹… ቤተ ጽድቅሂ ቤተ ሥላሴ መካነ ኢየሱስ ዉእቱ፣
እስመ ኢያንቀለቅል ለዓለም ሃይማኖት መሠረቱ፣
ባሕቱ ድልዉ መልዕልተ ሰማያት ሰባቱ፣
መካነ ኢየሱስ መንበረ አብ ዘይጸዉርዎ አርባዕቱ፡፡…››

የሚለዉን ዘርዕ በማሰማት በምሥጢር ‹ ልክ እንደ አርባእቱ እንስሳ ኪሩቤል አራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍትን በመዘርጋትና የማይናወጽ የሃይማኖት መሠረት በመሆን ኑፋቄንም ባለማስደረስ  መካነ ኢየሱስ በእዉነት የሥላሴ ቤት የእግዚአብሔር መንበሩ ነዉ › ተብሎ ይነገርለት እንደነበር አስረድተዋል፡፡ መልአከ ሰላም ዐምደ ብርሃንም የኔታ ገብረ ጊዮርጊስን ከመካነ ኢየሱስ ወደ አክሱም እንዲሄዱ ለአክሱሞች ከፍተኛ ዋስትና የሰጠዉ ይሄዉ በሃይማኖት ነቅዕ ጥርጣሬ የሌለዉ ጉባዔ የሚሰጥበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ቦታዉ ለቅርቧ ኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ያበረከታቸዉ ሊቃዉንት እጅግ ብዙዎች ናቸዉ፡፡እንደ ሊቀ ስዩማን ራደ አስረስ ገላጻ በ1921 ዓ ም ግብጽ ወርደዉ ከተሾሙት ከዐራቱ አንዱ የሆኑት ጎሬ ላይ በጣልያን እንደ አቡነ ጴጥሮስ ሰማዕትነት የተቀበሉት ብጹዕ አቡነ ሚካኤል በዚህ ቦታ በትምህርት ካለፉት ዉስጥ አንዱ ናቸዉ፡፡ በኋላም በጣልያን ሁለቱ አበዉ ማረፋቸዉን በማየት የኢትዮያ ሊቃዉንት ከሾሟቸዉ ዉስጥ አቡነ ዮሐንስ የተባሉት ሐዲስ ተክሌ የተማሩት ደብረ ሃይማኖት መካነ ኢየሱስ ነበር፡፡ ከጣልያን መመለስ በኋላም በ1941 ከተሾሙት ከቀዳሚዎቹ ሊቃነ ጳጳሳት አንዱ ከሆኑት ከብጹዕ አቡነ ሚካኤል ጀምሮ እነ አቡነ በርተሎሜዎስ፣ አቡነ ኤልያስ (አሁን ስዊድን ያሉት) የኋላዉ አቡነ ኤልያስ (የቀለም ቀንዱ ሊቀ ጉባኤ አስበ)፣ ተጠቃሾች ሲሆኑ ከሊቃዉንቱም እነ ርዕሰ ደብር ጥዑመ ልሣን፣ መልአከ ታቦር ተሾመ ዘሪሁን፣ ሊቀ ሥዩማን ራደ አስረስ፣ መልአከ ሰላም መርዓዊ ተበጀ፣ … ተቆጥረዉ የማያልቁ የብሉይ፣ የሐዲስ፣የመጻሕፍተ ሊቃዉንት፣ የመጻሕፍተ መነኮሳት፣ የቅኔና የዜማ ሊቃዉንትን አፍርቷል፡፡

ቤተ ክርስቲያኑ ባለፉት ሃምሳ ዐመታት ዉስጥም በቦታዉ ብሉይና ሐዲስን በማስተማር፣ የተጣሉትን ከማስታረቅ ጋር በብሕትዉና በመኖር የgubae z mekane Eyesus 130ሚታወቁት መጋቤ ሐዲስ ኃይለ ሚካኤል ብዙ ደቀ መዛሙርትን በማፍራት ያገለገሉበት ሲሆን እርሳቸዉ በዕርጅና ማስተማሩን ሲያቆሙ በአሁኑ ጊዜ ደግሞ ሐዲሳቱን ከእርሳቸዉ ብሉያቱን ደግሞ ጎንደር ዐቢየ እግዚእ ከየኔታ ፀሐይ የተማሩት የኔታ ሐረገወይን ተተክተዉ በማስተማር ላይ ይገኛሉ፡፡ የደብሩ አስተዳዳሪ የሆኑት መልአከ ሃይማኖት ሲሳይ አሰፋም በቦታዉ ላይ ድጓዉን በማስተማርና ብዙ መምህራንና ደቀ መዛሙርትን በማፍራት ከሃያ አምስት ዐመት በላይ ኖረዉበታል፡፡

ቦታዉ ብዙ ታሪካዊ ቅርሶችን የያዘ ከመሆኑም በላይ ከጥንት ጀምሮ እጅግ ብዙ ሕመምተኞች (ብዙ የእስልምና ተከታዮችን ጨምሮ) የሚፈወሱባት የኪዳነ ምሕረት ጸበል ይገኝበታል፡፡

በአሁኑ ጊዜ ቆርቆሮዉ አርጅቶ በማፍሰስ ላይ ከመሆኑም በላይ ሌሎቹንም ጨምሮ ከ 1.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሚጠይቅ እድሳት እንደሚያስፈልገዉ በባለሞያዎች የተጠናዉ ጥናት ያመለክታል፡፡ እንደ ባለሞያዎቹ ገለጻ 750 ቆርቆሮና ለጣራ ሥራዉ የሚሆኑ የተለያዩ ጣዉላዎች፣በጣዉላ የሚሰራ ኮርኒስ፣ የኤሌክትሪክ፣የፍሳሽ፤ 24 ቆመ ብእሲዎች ወይም አምዶች (Columns)፣ የግቢዉን በርና ሌሎቹንም ያካትታል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ የሚገኘዉ ገጠር ዉስጥ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የሌሎቻችንን በተለይም በቦታዉ ላይ በመማርና ከተማሩት አገልግሎት በማግኘት ላይ ያሉትን እንዲሁም ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን አሁንም ድረስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ የሚገኘዉን ታሪካዊዉን ቦታ በመርዳት እንደ ቀድሞዉ ሁሉ ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ያለዉን አስተዋጥኦ ማሳደግ እንደሚጠበቅ በዕለቱ ከነበሩት በመልአከ ታቦር ተሾመ ዘሪሁንና በሊቃዉንት ጉባኤ ሰብሳቢዉ መልአከ ሰላም ዐምደ ብርሃን በአጽንዖት ተገልጾአል፡፡

በመርሐ ግብሩ ተሳታፊዎች ጥያቄ መሠረት ሥራዉን ለመርዳት ለሚፈልጉ በስልክ ቁጥሮች
0911 68 93 22
0911 10 95 84
0911 13 73 50

በመደወልና በማነጋገር በዐይነትም ሆነ በገንዘብ መርዳትና ለለገሱት እርዳታም ሕጋዊ ደረሰኝና በዐይነትም ከሆነ የተላከዉ ዕቃ መድረሱን ማረጋገጫ ባለ ማኅተም ደብዳቤ መቀብል እንደሚገባ ተገልጾ ጉባኤዉ በጸሎት ተጠናቅቋል፡፡ በዚህ አጋጣሚ ከቀኑ 8፡30 ጀምሮ እስከ 12፡ 30 ድረስ በቆየዉ በዚህ ረጂም ጉባኤ ተሳታፊዎቹ በትዕግስት ጸንተዉ የሊቃዉንቱን ትምህርቶችና ገለጻዎች እነዲሁም ወረቦችና ዝማሬዎች ሲኮመኩሙ እንዲዉሉ ያስቻለዉ ጉባኤዉ የገቢ ማሰባሰቢያ ሳይሆን የትምህርትና የዝማሬ ብቻ መስሎ በመዘጋጀቱ እያመሰገንን ሌሎቹም አራአያዉን ሊከተሉት የሚገባ መሆኑን ሳንጠቁም አናልፍም፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!

“እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኅን ተወልዶላችኋል” (ሉቃ.2፡11)

ታኅሣሥ 27/2004 ዓ.ም

በዲ/ን በረከት አዝመራው እና በዲ/ን አሉላ መብራቱ


“ዘሎቱ ሰብአ ሰገል ሰገዱ ሎቱ፤ አማን መንክር ስብሐተ ልደቱ፤

ለእርሱ ሰብአ ሰገል የሰገዱለት፣ የልደቱ ክብር ድንቅ ነው።”

{gallery count=1 width=350 height=300 counter=1 links=0 alignment=center animation=3000}ledete2004{/gallery}

እግዚአብሔርን በእምነት ደስ ያሰኙ ቅዱሳን ከእስራኤላውያን ተነሥተው ነበር።(ዕብ.11) የአባቶች አለቃ ከሆነው ከአብርሃም ጀምሮ እስከ ጌታችን ሰው መሆን (ዘመነ ሥጋዌ) ድረስ ብዙ ታላላቅ አባቶችና እናቶች በእስራኤል ዘንድ ተገኝተዋል።

 

የእስራኤል ታሪክ ሁልጊዜ መልካም ታሪክ ብቻ ግን አይደለም፤ እግዚአብሔርን ያሳዘኑባቸው ጊዜያት ጥቂቶች አይደሉም። በዚህ ጊዜ በዙሪያቸው ባሉ ነገሥታት እየተማረኩ ወደ ፋርስ፣ ባቢሎንና ግብጽ እየወረዱ ለአሕዛብ የተገዙበትና የገበሩበት ጊዜም ነበር። ንስሐ ገብተው ወደ እግዚአብሔር ሲመለሱ ደግሞ እግዚአብሔር ከእነርሱ መካከል ሰው እያስነሣ ያድናቸው ነበር። ለአባቶቻቸው የገባውን የዘለዓለም ቃልኪዳን እያሰበ ይረዳቸውም ነበር። (መዝ.77 (78))

እነሆ በዚህ የታሪክ መስመር ውስጥ ወደር የሌለው፣ ሁለተኛ በዓለም ታሪክ የማይደገም ታላቅ ነገር ተከሰተ። የእግዚአብሔር ልጅ የሰውን ሥጋ ለብሶ እንደ ሰው በምድር ላይ ተገለጠ። ጥበበኛው ሰሎሞን “አበባ በምድራችን ታየ” ብሎ የተናገረው ትንቢት ተፈጸመ፤ አበባ ክርስቶስ ምድር በተባለ ሥጋችን ተገልጧልና(መኃ.2፥12)። የዓለም መድኃኒት እግዚአብሔርነቱን ሳይተው ሰው ሆነ። እነሆ የእግዚአብሔር ልጅ የአብርሃም ልጅ ተባለ፤ የዳዊት ጌታ የዳዊት ልጅ ተባለ። (ማቴ.1፥1) የዳዊት ፈጣሪ በዳዊት ከተማ በቤተልሔም በከብቶች በረት ተወለደ። አባቶቻቸው በአንድ ዘመን ዳዊት የነገሠባትን ከተማ ያፈረሱ፣ የዳዊትን ልጆች በባርነት የገዙ የፋርስና የአረብ ነገሥታት የዳዊትን መንግሥት ለዘለዓለም ለሚያጸናው ሕፃን ለኢየሱስ ክርስቶስ ሰገዱ፤ ተገዙ።

 

ልጁን ለእግዚአብሔር መስዋዕት አድርጎ ለማቅረብ እንኳ እንቢ ያላለውን፣ የአብርሃምን ልጆች ያስገበሩት የአሕዛብ ነገሥታት ዛሬ ለአብርሃም ልጅ ወርቅ፣ እጣን፣ ከርቤ ገበሩ። (ማቴ.1፥11) በበደለኞች እስራኤላውያን ልጆቻቸው ኃጢአት ምክንያት ዝቅ ዝቅ ያለው የእስራኤል ክብር ከእነርሱ ዘር ሥጋን በነሣው በኢየሱስ ክርስቶስ ለዘላለም ከፍ ከፍ አለ።

 

የክርስቶስ ሰው መሆን ግን ከእስራኤል ታሪክ ያለፈ የሰው ልጅ ሁሉ ደስታ ነው። እነሆ ሰው የመሆኑ ዜና የሰው ልጆችን ሁሉ ደስታ አሰኘ “እነሆ ለህዝቡ ሁሉ የሚሆንchristmas ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።” የሚል ዜና በሰማያውያን መላእክት ተሰበከ። (ለቃ.2፥11) የምድር ኃያላን ነገሥታት በከብቶች በረት ውስጥ በጨርቅ ተጠቅልሎ ለተኛው ሕፃን መብዐ አቀረቡ። ንጹሐንና ኃያላን የሚሆኑ የሰማይ መላእክት እግዚአብሔር ለሰው ፍቅር ሲል እንደ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግም ተኝቶ ሲያዩ በታላቅ ትሕትና ከእረኞች ጋር ዘመሩ። (ሉቃ.2፥13)

 

“ብርሃንህንና እውነትህን ላክ፤ እነርሱ ይምሩኝ፣ ወደ ቅድስናህ ተራራና ወደ ማደሪያህ ይውሰዱኝ።” ያለው የዳዊት ጸሎት መልስ አገኘ (መዝ. 42፥3)። ማንም ሊቀርበው በማይችል ዘለዓለማዊ ብርሃን ዉስጥ ከአባቱ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የሚኖር ብርሃን ወልድ ለጨለማው ዓለም ብርሃን ይሆን ዘንድ ተወለደ። ወደ ጽድቅ ፀሐይ ያደርሳቸው ዘንድ የእርሱ የሆነው ኮከብ ሰብአ ሰገልን ከምሥራቅ መራቸው። እነሆ ለዘለዓለም የሚያበራው ፀሐይ በቤተ ልሔም ወጣ። ነቢዩ ኢሳይያስ “በጨለማ የሄደ ሕዝብ ብርሃን አየ በሞት ጥላ አገርም ለኖሩ ብርሃን ወጣላቸው” ብሎ የተናገረው ትንቢት ተፈጸመ (ኢሳ.9፥2)። እርሱ የቅድስናው ተራራና ማደሪያው ወደ ሆነች ወደ መንግሥተ ሰማያት ይወስደናል፤ በዚች የዘለዓለም አገራችንም የሚያበራልን ፀሐይ እርሱ ነው(ራእይ.21፥23)።

 

በዳዊት ከተማ በቤተልሔም ድንቅ ነገር ተደረገ። ዳዊት በወርቅ ያጌጠ የተልባ እግር መጎናጸፊያ የለበሰባት ቤተልሔም የሰማይና የምድር ፈጣሪ በጨርቅ ተጠቅልሎ ተገኘባት። ቤተልሔም ከዳዊት ዘመን አብልጣ ከበረች፤ የእግዚአብሔር ክብር አብርቶባታልና፤ የልዑላን መላእክት ዝማሬ ተሰምቶባታልና።(ሚክ.5፥2)

 

Picture2“የእሥራኤል እረኛ ሆይ አድምጥ …በኪሩቤል ላይ የምትቀመጥ ተገለጥ” ብሎ የለመነው የዳዊት ልመና በእውነት ተፈጸመ።(መዝ.70(71)፥1) የእስራኤል እረኛ በእረኞች መካከል በከብቶች በረት ተወለደ። (ሉቃ.2፥7)እረኞች ለእረኛቸው ዘመሩ፤ ላሞችና በጎች በበረት የተኛውን ሕፃን በትንፋሻቸው አሟሟቁት። በኦሪት ድንኳን በሙሴ ሕግ መሠረት ለመስዋዕት ይቀርቡ የነበሩ እንስሳት በልደቱ ደስ ተሰኙ፤ የእነርሱን መሥዋዕት የሚያስቀር አማናዊው የእግዚአብሔር በግ ተወልዷልና።

 

ለሰው ሁሉ ብርሃን የሚሰጥ እግዚአብሔር በጨለማው ዓለማችን ተወለደ።(ዮሐ.1፥9-14) ነቢያትና መምህራን ጠፍተውባት፣ የኃጢአት ጨለማ ዉጧት፣ በድንቁርና ባሕር ውስጥ ሰጥማ በነበረችው የሰው ልጆች ዓለም የእውነት ፀሐይ ወጣ። እነሆ ይህን ይገልጥ ዘንድ መድኅን በእኩለ ሌሊት ተወለደ፤ በተወለደ ጊዜ ግን የእግዚአብሔር ክብር በዙርያው አበራ። (ሉቃ.2፥8-9)

 

ለመንግሥቱ ወርቅ ተገበረለት። ኃያል መንግሥቱን ግን በምድር ላይ በትሕትና ገለጠው፤ በከብቶች በረት በመወለድና በአህያ ውርንጭላ ተቀምጦ በመሄድ።Picture1 (ሉቃ.19፥28-38) የአባታችን የዳዊት መንግሥት ያለልክ ከፍ ከፍ አለች፤ እግዚአብሔር ሰው ሆኖ የዳዊት ልጅ ሆኗልና። ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት ድንግል ማርያምን ባበሠራት ጊዜ “እርሱ ታላቅ ይሆናል፣ የልዑል ልጅም ይባላል፤ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፣ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለዓለም ይነግሣል፣ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለዉም” ብሎ የተናገረው ዛሬ ተፈጸመ(ሉቃ.1፥32) በባሕርይው የፍጥረት ሁሉ ገዥ የሆነው የእግዚአብሔር ልጅ ከዳዊት ልጅ ሥጋን ነሥቶ ሰው በሆነ ጊዜ የአባቱን የዳዊትን ዙፋን እስከ ጽርአ አርያም ድረስ ከፍ ከፍ አደረጋት። እነሆ ንጉሥ ክርስቶስ በያዕቆብ ቤት(በምዕመናን) ላይ ለዘለዓለም ነገሠ። ለመንግሥቱ የአሕዛብ  ነገሥታት ተገዙላት፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ናትና ፍጥረታት ሁሉ ይገዙላታል።(ኤር.23፥5)

 

ለክህነቱ እጣን ተሰጠው። ክህነቱም የአበውን እና የሌዋውያንን ክህነት የምትፈጽም የዘለዓለም ሰማያዊት ሥራው ናት። እነሆ የአብ ሊቀ ካህናት እርሱ የሰውን ባሕርይ ከራሱ ጋር አስማማ። ራሱ ካህን፣ ራሱ መስዋዕት፣ ራሱ ተቀባይ ሆኖ የፈጸማት የክህነት ሥራው የዘለዓለም ድኅነትን አስገኘች።

 

ለሞቱ ከርቤ ቀረበለት። እነሆ እግዚአብሔር ሰው የሆነበት ዋናው ምክንያት በሞቱ ሞትን ድል ለመንሣት ነውና በልደቱ ሞቱ ተሰበከ። ከርቤ ለሞቱ ሲቀርብለት የማይሞተው እርሱ ለሰው ልጆች ሲል የሚሞት ሥጋን እንደለበሰ ታወቀ።

 

የአሕዛብ ነገሥታት ወርቅ ገበሩለት፤ ምእመናን ደግሞ ጽሩይ፣ ንጹሕ፣ ሰማያዊ የሆነ ልቦናን እና እምነትን ለእርሱ እናቀርባለን። (1ኛ ጴጥ.1፥6) ሰብዐ ሰገል እርሱ የፈጠረውን ወርቅ ገበሩለት፤ እኛም በርሱ ጸጋና ሥራ ያገኘነውን ንጹሕና ሰማያዊ እምነታችንን እናቀርብለታለን።(ይሁ.3)

 

ነገሥታቱ ዕጣን ገበሩለት፤ ምእመናን ደግሞ ቂም በቀል የሌለበትን፣ ከመልካም እና ንጹሕ ልብ የሚወጣ የምስጋና ጸሎት እናቀርባለን፤ “ጸሎቴን በፊትህ እንደ ዕጣን ተቀበልልኝ፥ እጅ መንሣቴንም እንደ ሠርክ መስዋዕት ትሁን።” እንዳለ ንጉሥ ዳዊት።(መዝ.140፥2)

 

ስለሰው ልጆች ፍቅር ሲል ለሚቀበለው ሞት ከርቤ ገበሩለት፤ ምእመናን ደግሞ ለእግዚአብሔርና ለሰው ልጆች ያለንን ፍቅር ለእርሱ እናቀርባለን። ነገሥታቱ እርሱ ከፈጠረው ከርቤ ወስደው እጅ መንሻ አቀረቡ፤ ምእመናን ደግሞ ከእርሱ ከተማርነው፣ ከመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ከተቀበልነው ፍቅር መልሰን ለእርሱ እናቀርባለን። “እርሱ ስለኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቷልና በዚህ ፍቅርን አውቀናል፤ እኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን ልንሰጥ ይገባናል(1ኛ ዮሐ.3፥16)።”

ስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክብር አሜን!!

 

 

“እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኅን ተወልዶላችኋል”(ሉቃ.2፡11)

ታኅሣሥ 27/2004 ዓ.ም

በዲ/ን በረከት አዝመራው እና በዲ/ን አሉላ መብራቱ

“ዘሎቱ ሰብአ ሰገል ሰገዱ ሎቱ፤ አማን መንክር ስብሐተ ልደቱ፤

ለእርሱ ሰብአ ሰገል የሰገዱለት፣ የልደቱ ክብር ድንቅ ነው።”

እግዚአብሔርን በእምነት ደስ ያሰኙ ቅዱሳን ከእስራኤላውያን ተነሥተው ነበር።(ዕብ.11) የአባቶች አለቃ ከሆነው ከአብርሃም ጀምሮ እስከ ጌታችን ሰው መሆን (ዘመነ ሥጋዌ) ድረስ ብዙ ታላላቅ አባቶችና እናቶች በእስራኤል ዘንድ ተገኝተዋል።

የእስራኤል ታሪክ ሁልጊዜ መልካም ታሪክ ብቻ ግን አይደለም፤ እግዚአብሔርን ያሳዘኑባቸው ጊዜያት ጥቂቶች አይደሉም። በዚህ ጊዜ በዙሪያቸው ባሉ ነገሥታት እየተማረኩ ወደ ፋርስ፣ ባቢሎንና ግብጽ እየወረዱ ለአሕዛብ የተገዙበትና የገበሩበት ጊዜም ነበር። ንስሐ ገብተው ወደ እግዚአብሔር ሲመለሱ ደግሞ እግዚአብሔር ከእነርሱ መካከል ሰው እያስነሣ ያድናቸው ነበር። ለአባቶቻቸው የገባውን የዘለዓለም ቃልኪዳን እያሰበ ይረዳቸውም ነበር። (መዝ.77 (78))

እነሆ በዚህ የታሪክ መስመር ውስጥ ወደር የሌለው፣ ሁለተኛ በዓለም ታሪክ የማይደገም ታላቅ ነገር ተከሰተ። የእግዚአብሔር ልጅ የሰውን ሥጋ ለብሶ እንደ ሰው በምድር ላይ ተገለጠ። ጥበበኛው ሰሎሞን “አበባ በምድራችን ታየ” ብሎ የተናገረው ትንቢት ተፈጸመ፤ አበባ ክርስቶስ ምድር በተባለ ሥጋችን ተገልጧልና(መኃ.2፥12)። የዓለም መድኃኒት እግዚአብሔርነቱን ሳይተው ሰው ሆነ። እነሆ የእግዚአብሔር ልጅ የአብርሃም ልጅ ተባለ፤ የዳዊት ጌታ የዳዊት ልጅ ተባለ። (ማቴ.1፥1) የዳዊት ፈጣሪ በዳዊት ከተማ በቤተልሔም በከብቶች በረት ተወለደ። አባቶቻቸው በአንድ ዘመን ዳዊት የነገሠባትን ከተማ ያፈረሱ፣ የዳዊትን ልጆች በባርነት የገዙ የፋርስና የአረብ ነገሥታት የዳዊትን መንግሥት ለዘለዓለም ለሚያጸናው ሕፃን ለኢየሱስ ክርስቶስ ሰገዱ፤ ተገዙ።

ልጁን ለእግዚአብሔር መስዋዕት አድርጎ ለማቅረብ እንኴ እንቢ ያላለውን፣ የአብርሃምን ልጆች ያስገበሩት የአሕዛብ ነገሥታት ዛሬ ለአብርሃም ልጅ ወርቅ፣ እጣን፣ ከርቤ ገበሩ። (ማቴ.1፥11) በበደለኞች እስራኤላውያን ልጆቻቸው ኃጢአት ምክንያት ዝቅ ዝቅ ያለው የእስራኤል ክብር ከእነርሱ ዘር ሥጋን በነሣው በኢየሱስ ክርስቶስ ለዘላለም ከፍ ከፍ አለ።

የክርስቶስ ሰው መሆን ግን ከእስራኤል ታሪክ ያለፈ የሰው ልጅ ሁሉ ደስታ ነው። እነሆ ሰው የመሆኑ ዜና የሰው ልጆችን ሁሉ ደስታ አሰኘ “እነሆ ለህዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።” የሚል ዜና በሰማያውያን መላእክት ተሰበከ። (ለቃ.2፥11)

የምድር ኃያላን ነገሥታት በከብቶች በረት ውስጥ በጨርቅ ተጠቅልሎ ለተኛው ሕፃን መብዐ አቀረቡ። ንጹሐንና ኃያላን የሚሆኑ የሰማይ መላእክት እግዚአብሔር ለሰው ፍቅር ሲል እንደ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግም ተኝቶ ሲያዩ በታላቅ ትሕትና ከእረኞች ጋር ዘመሩ። (ሉቃ.2፥13)

“ብርሃንህንና እውነትህን ላክ፤ እነርሱ ይምሩኝ፣ ወደ ቅድስናህ ተራራና ወደ ማደሪያህ ይውሰዱኝ።” ያለው የዳዊት ጸሎት መልስ አገኘ (መዝ. 42፥3)። ማንም ሊቀርበው በማይችል ዘለዓለማዊ ብርሃን ዉስጥ ከአባቱ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የሚኖር ብርሃን ወልድ ለጨለማው ዓለም ብርሃን ይሆን ዘንድ ተወለደ። ወደ ጽድቅ ፀሐይ ያደርሳቸው ዘንድ የእርሱ የሆነው ኮከብ ሰብአ ሰገልን ከምሥራቅ መራቸው። እነሆ ለዘለዓለም የሚያበራው ፀሐይ በቤተ ልሔም ወጣ። ነቢዩ ኢሳይያስ “በጨለማ የሄደ ሕዝብ ብርሃን አየ በሞት ጥላ አገርም ለኖሩ ብርሃን ወጣላቸው” ብሎ የተናገረው ትንቢት ተፈጸመ (ኢሳ.9፥2)። እርሱ የቅድስናው ተራራና ማደሪያው ወደ ሆነች ወደ መንግሥተ ሰማያት ይወስደናል፤ በዚች የዘለዓለም አገራችንም የሚያበራልን ፀሐይ እርሱ ነው(ራእይ.21፥23)።

በዳዊት ከተማ በቤተልሔም ድንቅ ነገር ተደረገ። ዳዊት በወርቅ ያጌጠ የተልባ እግር መጎናጸፊያ የለበሰባት ቤተልሔም የሰማይና የምድር ፈጣሪ በጨርቅ ተጠቅልሎ ተገኘባት። ቤተልሔም ከዳዊት ዘመን አብልጣ ከበረች፤ የእግዚአብሔር ክብር አብርቶባታልና፤ የልዑላን መላእክት ዝማሬ ተሰምቶባታልና።(ሚክ.5፥2)

“የእሥራኤል እረኛ ሆይ አድምጥ …በኪሩቤል ላይ የምትቀመጥ ተገለጥ” ብሎ የለመነው የዳዊት ልመና በእውነት ተፈጸመ።(መዝ.70(71)፥1) የእስራኤል እረኛ በእረኞች መካከል በከብቶች በረት ተወለደ። (ሉቃ.2፥7)እረኞች ለእረኛቸው ዘመሩ፤ ላሞችና በጎች በበረት የተኛውን ሕፃን በትንፋሻቸው አሟሟቁት። በኦሪት ድንኳን በሙሴ ሕግ መሠረት ለመስዋዕት ይቀርቡ የነበሩ እንስሳት በልደቱ ደስ ተሰኙ፤ የእነርሱን መሥዋዕት የሚያስቀር አማናዊው የእግዚአብሔር በግ ተወልዷልና።

ለሰው ሁሉ ብርሃን የሚሰጥ እግዚአብሔር በጨለማው ዓለማችን ተወለደ።(ዮሐ.1፥9-14) ነቢያትና መምህራን ጠፍተውባት፣ የኃጢአት ጨለማ ዉጧት፣ በድንቁርና ባሕር ውስጥ ሰጥማ በነበረችው የሰው ልጆች ዓለም የእውነት ፀሐይ ወጣ። እነሆ ይህን ይገልጥ ዘንድ መድኅን በእኩለ ሌሊት ተወለደ፤ በተወለደ ጊዜ ግን የእግዚአብሔር ክብር በዙርያው አበራ። (ሉቃ.2፥8-9)

ለመንግሥቱ ወርቅ ተገበረለት። ኃያል መንግሥቱን ግን በምድር ላይ በትሕትና ገለጠው፤ በከብቶች በረት በመወለድና በአህያ ውርንጭላ ተቀምጦ በመሄድ። (ሉቃ.19፥28-38) የአባታችን የዳዊት መንግሥት ያለልክ ከፍ ከፍ አለች፤ እግዚአብሔር ሰው ሆኖ የዳዊት ልጅ ሆኗልና። ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት ድንግል ማርያምን ባበሠራት ጊዜ “እርሱ ታላቅ ይሆናል፣ የልዑል ልጅም ይባላል፤ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፣ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለዓለም ይነግሣል፣ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለዉም” ብሎ የተናገረው ዛሬ ተፈጸመ(ሉቃ.1፥32) በባሕርይው የፍጥረት ሁሉ ገዥ የሆነው የእግዚአብሔር ልጅ ከዳዊት ልጅ ሥጋን ነሥቶ ሰው በሆነ ጊዜ የአባቱን የዳዊትን ዙፋን እስከ ጽርአ አርያም ድረስ ከፍ ከፍ አደረጋት። እነሆ ንጉሥ ክርስቶስ በያዕቆብ ቤት(በምዕመናን) ላይ ለዘለዓለም ነገሠ። ለመንግሥቱ የአሕዛብ  ነገሥታት ተገዙላት፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ናትና ፍጥረታት ሁሉ ይገዙላታል።(ኤር.23፥5)

ለክህነቱ እጣን ተሰጠው። ክህነቱም የአበውን እና የሌዋውያንን ክህነት የምትፈጽም የዘለዓለም ሰማያዊት ሥራው ናት። እነሆ የአብ ሊቀ ካህናት እርሱ የሰውን ባሕርይ ከራሱ ጋር አስማማ። ራሱ ካህን፣ ራሱ መስዋዕት፣ ራሱ ተቀባይ ሆኖ የፈጸማት የክህነት ሥራው የዘለዓለም ድኅነትን አስገኘች።

ለሞቱ ከርቤ ቀረበለት። እነሆ እግዚአብሔር ሰው የሆነበት ዋናው ምክንያት በሞቱ ሞትን ድል ለመንሣት ነውና በልደቱ ሞቱ ተሰበከ። ከርቤ ለሞቱ ሲቀርብለት የማይሞተው እርሱ ለሰው ልጆች ሲል የሚሞት ሥጋን እንደለበሰ ታወቀ።

የአሕዛብ ነገሥታት ወርቅ ገበሩለት፤ ምእመናን ደግሞ ጽሩይ፣ ንጹሕ፣ ሰማያዊ የሆነ ልቦናን እና እምነትን ለእርሱ እናቀርባለን። (1ኛ ጴጥ.1፥6) ሰብዐ ሰገል እርሱ የፈጠረውን ወርቅ ገበሩለት፤ እኛም በርሱ ጸጋና ሥራ ያገኘነውን ንጹሕና ሰማያዊ እምነታችንን እናቀርብለታለን።(ይሁ.3)

ነገሥታቱ ዕጣን ገበሩለት፤ ምእመናን ደግሞ ቂም በቀል የሌለበትን፣ ከመልካም እና ንጹሕ ልብ የሚወጣ የምስጋና ጸሎት እናቀርባለን፤ “ጸሎቴን በፊትህ እንደ ዕጣን ተቀበልልኝ፥ እጅ መንሣቴንም እንደ ሠርክ መስዋዕት ትሁን።” እንዳለ ንጉሥ ዳዊት።(መዝ.140፥2)

ስለሰው ልጆች ፍቅር ሲል ለሚቀበለው ሞት ከርቤ ገበሩለት፤ ምእመናን ደግሞ ለእግዚአብሔርና ለሰው ልጆች ያለንን ፍቅር ለእርሱ እናቀርባለን። ነገሥታቱ እርሱ ከፈጠረው ከርቤ ወስደው እጅ መንሻ አቀረቡ፤ ምእመናን ደግሞ ከእርሱ ከተማርነው፣ ከመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ከተቀበልነው ፍቅር መልሰን ለእርሱ እናቀርባለን። “እርሱ ስለኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቷልና በዚህ ፍቅርን አውቀናል፤ እኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን ልንሰጥ ይገባናል(1ኛ ዮሐ.3፥16)።” ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክብር አሜን!!

 

“እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኅን ተወልዶላችኋል”(ሉቃ.2፡11)

ታኅሣሥ 27/2004 ዓ.ም

በዲ/ን በረከት አዝመራው እና በዲ/ን አሉላ መብራቱ

“ዘሎቱ ሰብአ ሰገል ሰገዱ ሎቱ፤ አማን መንክር ስብሐተ ልደቱ፤

ለእርሱ ሰብአ ሰገል የሰገዱለት፣ የልደቱ ክብር ድንቅ ነው።”

እግዚአብሔርን በእምነት ደስ ያሰኙ ቅዱሳን ከእስራኤላውያን ተነሥተው ነበር።(ዕብ.11) የአባቶች አለቃ ከሆነው ከአብርሃም ጀምሮ እስከ ጌታችን ሰው መሆን (ዘመነ ሥጋዌ) ድረስ ብዙ ታላላቅ አባቶችና እናቶች በእስራኤል ዘንድ ተገኝተዋል።

የእስራኤል ታሪክ ሁልጊዜ መልካም ታሪክ ብቻ ግን አይደለም፤ እግዚአብሔርን ያሳዘኑባቸው ጊዜያት ጥቂቶች አይደሉም። በዚህ ጊዜ በዙሪያቸው ባሉ ነገሥታት እየተማረኩ ወደ ፋርስ፣ ባቢሎንና ግብጽ እየወረዱ ለአሕዛብ የተገዙበትና የገበሩበት ጊዜም ነበር። ንስሐ ገብተው ወደ እግዚአብሔር ሲመለሱ ደግሞ እግዚአብሔር ከእነርሱ መካከል ሰው እያስነሣ ያድናቸው ነበር። ለአባቶቻቸው የገባውን የዘለዓለም ቃልኪዳን እያሰበ ይረዳቸውም ነበር። (መዝ.77 (78))

እነሆ በዚህ የታሪክ መስመር ውስጥ ወደር የሌለው፣ ሁለተኛ በዓለም ታሪክ የማይደገም ታላቅ ነገር ተከሰተ። የእግዚአብሔር ልጅ የሰውን ሥጋ ለብሶ እንደ ሰው በምድር ላይ ተገለጠ። ጥበበኛው ሰሎሞን “አበባ በምድራችን ታየ” ብሎ የተናገረው ትንቢት ተፈጸመ፤ አበባ ክርስቶስ ምድር በተባለ ሥጋችን ተገልጧልና(መኃ.2፥12)። የዓለም መድኃኒት እግዚአብሔርነቱን ሳይተው ሰው ሆነ። እነሆ የእግዚአብሔር ልጅ የአብርሃም ልጅ ተባለ፤ የዳዊት ጌታ የዳዊት ልጅ ተባለ። (ማቴ.1፥1) የዳዊት ፈጣሪ በዳዊት ከተማ በቤተልሔም በከብቶች በረት ተወለደ። አባቶቻቸው በአንድ ዘመን ዳዊት የነገሠባትን ከተማ ያፈረሱ፣ የዳዊትን ልጆች በባርነት የገዙ የፋርስና የአረብ ነገሥታት የዳዊትን መንግሥት ለዘለዓለም ለሚያጸናው ሕፃን ለኢየሱስ ክርስቶስ ሰገዱ፤ ተገዙ።

ልጁን ለእግዚአብሔር መስዋዕት አድርጎ ለማቅረብ እንኴ እንቢ ያላለውን፣ የአብርሃምን ልጆች ያስገበሩት የአሕዛብ ነገሥታት ዛሬ ለአብርሃም ልጅ ወርቅ፣ እጣን፣ ከርቤ ገበሩ። (ማቴ.1፥11) በበደለኞች እስራኤላውያን ልጆቻቸው ኃጢአት ምክንያት ዝቅ ዝቅ ያለው የእስራኤል ክብር ከእነርሱ ዘር ሥጋን በነሣው በኢየሱስ ክርስቶስ ለዘላለም ከፍ ከፍ አለ።

የክርስቶስ ሰው መሆን ግን ከእስራኤል ታሪክ ያለፈ የሰው ልጅ ሁሉ ደስታ ነው። እነሆ ሰው የመሆኑ ዜና የሰው ልጆችን ሁሉ ደስታ አሰኘ “እነሆ ለህዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።” የሚል ዜና በሰማያውያን መላእክት ተሰበከ። (ለቃ.2፥11)

የምድር ኃያላን ነገሥታት በከብቶች በረት ውስጥ በጨርቅ ተጠቅልሎ ለተኛው ሕፃን መብዐ አቀረቡ። ንጹሐንና ኃያላን የሚሆኑ የሰማይ መላእክት እግዚአብሔር ለሰው ፍቅር ሲል እንደ ሕፃን ተጠቅልሎ በግርግም ተኝቶ ሲያዩ በታላቅ ትሕትና ከእረኞች ጋር ዘመሩ። (ሉቃ.2፥13)

“ብርሃንህንና እውነትህን ላክ፤ እነርሱ ይምሩኝ፣ ወደ ቅድስናህ ተራራና ወደ ማደሪያህ ይውሰዱኝ።” ያለው የዳዊት ጸሎት መልስ አገኘ (መዝ. 42፥3)። ማንም ሊቀርበው በማይችል ዘለዓለማዊ ብርሃን ዉስጥ ከአባቱ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የሚኖር ብርሃን ወልድ ለጨለማው ዓለም ብርሃን ይሆን ዘንድ ተወለደ። ወደ ጽድቅ ፀሐይ ያደርሳቸው ዘንድ የእርሱ የሆነው ኮከብ ሰብአ ሰገልን ከምሥራቅ መራቸው። እነሆ ለዘለዓለም የሚያበራው ፀሐይ በቤተ ልሔም ወጣ። ነቢዩ ኢሳይያስ “በጨለማ የሄደ ሕዝብ ብርሃን አየ በሞት ጥላ አገርም ለኖሩ ብርሃን ወጣላቸው” ብሎ የተናገረው ትንቢት ተፈጸመ (ኢሳ.9፥2)። እርሱ የቅድስናው ተራራና ማደሪያው ወደ ሆነች ወደ መንግሥተ ሰማያት ይወስደናል፤ በዚች የዘለዓለም አገራችንም የሚያበራልን ፀሐይ እርሱ ነው(ራእይ.21፥23)።

በዳዊት ከተማ በቤተልሔም ድንቅ ነገር ተደረገ። ዳዊት በወርቅ ያጌጠ የተልባ እግር መጎናጸፊያ የለበሰባት ቤተልሔም የሰማይና የምድር ፈጣሪ በጨርቅ ተጠቅልሎ ተገኘባት። ቤተልሔም ከዳዊት ዘመን አብልጣ ከበረች፤ የእግዚአብሔር ክብር አብርቶባታልና፤ የልዑላን መላእክት ዝማሬ ተሰምቶባታልና።(ሚክ.5፥2)

“የእሥራኤል እረኛ ሆይ አድምጥ …በኪሩቤል ላይ የምትቀመጥ ተገለጥ” ብሎ የለመነው የዳዊት ልመና በእውነት ተፈጸመ።(መዝ.70(71)፥1) የእስራኤል እረኛ በእረኞች መካከል በከብቶች በረት ተወለደ። (ሉቃ.2፥7)እረኞች ለእረኛቸው ዘመሩ፤ ላሞችና በጎች በበረት የተኛውን ሕፃን በትንፋሻቸው አሟሟቁት። በኦሪት ድንኳን በሙሴ ሕግ መሠረት ለመስዋዕት ይቀርቡ የነበሩ እንስሳት በልደቱ ደስ ተሰኙ፤ የእነርሱን መሥዋዕት የሚያስቀር አማናዊው የእግዚአብሔር በግ ተወልዷልና።

ለሰው ሁሉ ብርሃን የሚሰጥ እግዚአብሔር በጨለማው ዓለማችን ተወለደ።(ዮሐ.1፥9-14) ነቢያትና መምህራን ጠፍተውባት፣ የኃጢአት ጨለማ ዉጧት፣ በድንቁርና ባሕር ውስጥ ሰጥማ በነበረችው የሰው ልጆች ዓለም የእውነት ፀሐይ ወጣ። እነሆ ይህን ይገልጥ ዘንድ መድኅን በእኩለ ሌሊት ተወለደ፤ በተወለደ ጊዜ ግን የእግዚአብሔር ክብር በዙርያው አበራ። (ሉቃ.2፥8-9)

ለመንግሥቱ ወርቅ ተገበረለት። ኃያል መንግሥቱን ግን በምድር ላይ በትሕትና ገለጠው፤ በከብቶች በረት በመወለድና በአህያ ውርንጭላ ተቀምጦ በመሄድ። (ሉቃ.19፥28-38) የአባታችን የዳዊት መንግሥት ያለልክ ከፍ ከፍ አለች፤ እግዚአብሔር ሰው ሆኖ የዳዊት ልጅ ሆኗልና። ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት ድንግል ማርያምን ባበሠራት ጊዜ “እርሱ ታላቅ ይሆናል፣ የልዑል ልጅም ይባላል፤ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፣ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለዓለም ይነግሣል፣ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለዉም” ብሎ የተናገረው ዛሬ ተፈጸመ(ሉቃ.1፥32) በባሕርይው የፍጥረት ሁሉ ገዥ የሆነው የእግዚአብሔር ልጅ ከዳዊት ልጅ ሥጋን ነሥቶ ሰው በሆነ ጊዜ የአባቱን የዳዊትን ዙፋን እስከ ጽርአ አርያም ድረስ ከፍ ከፍ አደረጋት። እነሆ ንጉሥ ክርስቶስ በያዕቆብ ቤት(በምዕመናን) ላይ ለዘለዓለም ነገሠ። ለመንግሥቱ የአሕዛብ  ነገሥታት ተገዙላት፤ የእግዚአብሔር መንግሥት ናትና ፍጥረታት ሁሉ ይገዙላታል።(ኤር.23፥5)

ለክህነቱ እጣን ተሰጠው። ክህነቱም የአበውን እና የሌዋውያንን ክህነት የምትፈጽም የዘለዓለም ሰማያዊት ሥራው ናት። እነሆ የአብ ሊቀ ካህናት እርሱ የሰውን ባሕርይ ከራሱ ጋር አስማማ። ራሱ ካህን፣ ራሱ መስዋዕት፣ ራሱ ተቀባይ ሆኖ የፈጸማት የክህነት ሥራው የዘለዓለም ድኅነትን አስገኘች።

ለሞቱ ከርቤ ቀረበለት። እነሆ እግዚአብሔር ሰው የሆነበት ዋናው ምክንያት በሞቱ ሞትን ድል ለመንሣት ነውና በልደቱ ሞቱ ተሰበከ። ከርቤ ለሞቱ ሲቀርብለት የማይሞተው እርሱ ለሰው ልጆች ሲል የሚሞት ሥጋን እንደለበሰ ታወቀ።

የአሕዛብ ነገሥታት ወርቅ ገበሩለት፤ ምእመናን ደግሞ ጽሩይ፣ ንጹሕ፣ ሰማያዊ የሆነ ልቦናን እና እምነትን ለእርሱ እናቀርባለን። (1ኛ ጴጥ.1፥6) ሰብዐ ሰገል እርሱ የፈጠረውን ወርቅ ገበሩለት፤ እኛም በርሱ ጸጋና ሥራ ያገኘነውን ንጹሕና ሰማያዊ እምነታችንን እናቀርብለታለን።(ይሁ.3)

ነገሥታቱ ዕጣን ገበሩለት፤ ምእመናን ደግሞ ቂም በቀል የሌለበትን፣ ከመልካም እና ንጹሕ ልብ የሚወጣ የምስጋና ጸሎት እናቀርባለን፤ “ጸሎቴን በፊትህ እንደ ዕጣን ተቀበልልኝ፥ እጅ መንሣቴንም እንደ ሠርክ መስዋዕት ትሁን።” እንዳለ ንጉሥ ዳዊት።(መዝ.140፥2)

ስለሰው ልጆች ፍቅር ሲል ለሚቀበለው ሞት ከርቤ ገበሩለት፤ ምእመናን ደግሞ ለእግዚአብሔርና ለሰው ልጆች ያለንን ፍቅር ለእርሱ እናቀርባለን። ነገሥታቱ እርሱ ከፈጠረው ከርቤ ወስደው እጅ መንሻ አቀረቡ፤ ምእመናን ደግሞ ከእርሱ ከተማርነው፣ ከመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ከተቀበልነው ፍቅር መልሰን ለእርሱ እናቀርባለን። “እርሱ ስለኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቷልና በዚህ ፍቅርን አውቀናል፤ እኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን ልንሰጥ ይገባናል(1ኛ ዮሐ.3፥16)።” ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክብር አሜን!!

 

 

30

እረኝነት እንደ አፍርሃት ሶርያዊ አስተምህሮ

ታኅሣሥ 24/2004 ዓ.ም

ትርጉም

በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ

መግቢያ

አፍርሃት ያዕቆብ ዘንጽቢን እና “የፋርሱ ጠቢብ” በሚሉ ስያሜዎቹ የሚታወቅ አባት ሲሆን በዐራተኛው ክፍለ ዘመን መግቢያ ላይ የተነሣ ሶርያዊ ተጠቃሽ  ጸሐፊ ነው፡፡ በእርሱ ዘመን ማኅልየ ማኅልይ ዘሶርያና የቶማስ ሥራ የሚባሉት ሥራዎች እንደሚታወቁ ይታመናል፡፡ ስለአፍራሃት የሕይወት ታሪክ ብዙ የሚታወቅ ነገር ባይኖርም አንዳንድ ጥንታዊ ታሪክ ጸሐፊያን አፍራሃት በአሁኑዋ ኢራቅ ትገኝ በነበረችው ማር ማታያ ተብላ በምትታወቀው ገዳም ሊቀ ጳጳስ እንደነበረ ጽፈው ይገኛሉ፡፡ ይህ ግን ተቀባይነት የለው፡፡ አፍራሃት ሃያ ሦስት ድርሳናትን የጻፈ ሲሆን እነርሱም የተለያዩ ርእሶች ያሉዋቸው ናቸው፡፡ እርሱ ከጻፈባቸው ድርሰቶች መካከል ስለእምነት ፣ ስለፍቅር፣ ስለጾም ፣ ስለጸሎት፣ በዘመኑ ስለነበረው የቃልኪዳን ልጆችና ልጃገረዶች፣ ስለትሕትና ጽፎአል፡፡ አፍርሃት ከቅዱስ ኤፍሬም ጋር ለሶርያ ሥነ ጽሑፍ ፋና ወጊ የሆነ ጸሐፊ ነው፡፡  እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በእረኝነት ላይ የፃፈውን እንመለከታለን፡፡

እረኞች የሕይወት ምግብን ይሰጡ ዘንድ በመንጋው ላይ የተሾሙ አለቆች ናቸው፡፡ መንጋውን የሚጠብቅና ስለእነርሱ የሚደክም እረኛ እርሱ መንጋውን ለሚያፈቅረውና ራሱን ስለመንጎቹ ለሰጠው መልካም እረኛ እውነተኛ ደቀመዝሙር ነው፡፡ ነገር ግን መንጋውን ከጥፋት የማይመልስ እርሱ ለመንጋው ግድ የሌለው ምንደኛ ነው፡፡

እናንተ እረኞች ሆይ በጥንት ጊዜ የነበሩትን ቅዱሳን እረኞችን ምሰሉአቸው፡፡ ያዕቆብ የላባን በጎች ያሰማራ፣ በትጋትና በድካም ይጠብቅ30 ነበር፡፡ በዚህም ከአምላኩ ዘንድ ዋጋ አግኝቶበታል፡፡ አንድ ወቅት ያዕቆብ ለላባ  “ሃያ ዓመት ሙሉ ከአንተ ጋር ነበርሁ በጎችህና ፍየሎችህ አልጨነገፉም የመንጎችህንም ጠቦቶች አልበላሁም አውሬ የሰበረውን አላመጣሁልህም ነበር፤ እኔ ስለ እርሱ እከፍልህ ነበርሁ፤ በቀንም በሌሊትም የተሰረቀውን ከእጄ ትሻው ነበር፡፡ የቀን ሀሩር የሌሊት ቁር ይበላኝ ነበር ፤ እንቅልፍ ከዐይኔ ጠፋ”(ዘፍ.፴፩፥፴፰-፴፱)ብሎት ነበር፡፡  እናንተ እረኞች ይህን እረኛ ለመንጎቹ ምን ያህል እንዲጠነቀቅ  አስተዋላችሁን? በሌሊት እንኳ እነርሱን ለመጠበቅ በትጋት ያለእንቅልፍ የሚተጋ እነርሱንም ለመመገብ በቀን  የሚደክም  እውነተኛ እረኛ ነበር፡፡

ዮሴፍና የእርሱ ወንድሞች ሁሉ እረኞች ነበሩ፤ ሙሴ የበጎች እረኛ ነበር፤ ዳዊትም እንዲሁ እረኛ ነበር፡፡ አሞጽም ላሞችን ያግድ ነበር፡፡ እነዚህ ሁሉ መንጎቻቸውን በመለመለመ መስክ ማሰማራት የሚያውቁ እረኞች ናቸው፡፡ ወዳጄ ሆይ  እግዚአብሔር እነዚህን እረኞች አስቀድመው በጎችን በኋላም ሰዎችን እንዲጠብቁ ስለምን እንዳደረጋቸው ተረዳህን? መልሱ ግልጽ ነው፤ መንጎቻቸውን እንዴት መጠበቅና ስለእነርሱ ሲሉ ምን ያህል መድከም እንዳለባቸው ሊያስተምራቸው በመፈልጉ ነበር፡፡ ይህንን የእረኝነት ሓላፊነት ከተማሩ በኋላ ለእረኝነት ተቀቡ፡፡ ያዕቆብ የላባን በጎች በብዙ ድካምና ትጋት ጠበቀ፤ በለመለመ መስክም አሰማራ፡፡ ከዛም ልጆቹን በአግባቡ ወደ መምራት ተመለሰ፣ የእረኝነት ሙያንም ለልጆቹ አስተማረ፡፡ ዮሴፍ በጎችን ከወንድሞቹ ጋር በመሆን  ይጠብቅ ነበር፡፡ ስለዚህም በግብጽ እጅግ ብዙ ሕዝብን ይመራና ልክ እንደ መልካም እረኛ ያሰማራ ዘንድ ተሾመ፡፡ ሙሴ የአማቱን በጎች ይጠብቅ ነበር፡፡

 

በመቀጠል ወገኖቹን ይመራ ዘንድ ተመረጠ፡፡ እርሱም እንደ መልካም እረኛ ሕዝቡን በለመለመ መስክ አሰማራ፡፡ ሕዝቡ የጥጃ ምስልን ሠርቶ እግዚአብሔር አምላክን በማሳዘናቸው ምክንያት ሊያጠፋቸው ቆርጦ ሳለ ሙሴ ስለሕዝቦቹ ተገብቶ እግዚአብሔር አምላክ ይቅር እንዲላቸው ዘንድ “አሁን ይህን ኃጢአታቸውን ይቅር በላቸው፤ ያለዚያ ግን ከጻፍከው መጽሐፍህ እባክህ እኔን ደምስሰኝ” (ዘጸአ.፴፪፥፴፪) ብሎ ጸለየ፣ እግዚአብሔር አምላኩን ተለማመነው፡፡ በመንጎቹ ፈንታ ነፍሱን የሚሰጥ እርሱ እጅግ መልካም እረኛ ነው፡፡ ስለሚመራው ሕዝብ ነፍሱን የሚሰጥ እርሱ ትክከለኛ መሪ ነው፡፡ እርሱ ስለመንጎቹ ደጀን ሆኖ የሚጠብቅና የሚመግብ ርኅሩኅ አባት ሊስኝ የሚገባው፡፡ መንጋውን እንዴት ማሰማራት እንደሚችል የሚያውቀው አስተዋዩ እረኛ ሙሴ እጁን ጭኖ መንፈሱን ላሳደረበት ለመንፈስ ልጁ ለኢያሱ ወለደ ነዌ፣ የእግዚአብሔርን መንጋ እንዲያሰማራ የእስራኤልንም ሠራዊት እንዲመራ የእረኝትን ሙያ አስተምሮት ነበር፡፡ እርሱ ጠላቶቹን ሁሉ ድል በመንሳትና ሀገራቸውንም በመውረስ፣ የመሰማሪያ መስክ በመስጠትና ምድሪቱንም ያርፉባትና ለበጎቻቸውም ማሰማሪያ ያገኙ ዘንድ አድርጎ አካፈላቸው፡፡

 

እንዲሁ ንጉሥ ዳዊት የአባቱን በጎች ይጠብቅ ነበር፡፡ ከዚህም ነው ሕዝቡን ይመራ ዘንድ የተቀባው፡፡ እርሱ ከልቡ ሕዝቡን ወደ አንድነት መራ፤ በእጁም ጥበብ መንጋውን አሰማራ፡፡ ዳዊት መንጎቹን ወደ መቁጠር በመጣ ጊዜ በእነርሱ ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ነደደ፤ ሕዝቡም እግዘአብሔር ባመጣው ቸነፈር ምክንያት ማለቅ ጀመረ፡፡ ዳዊት ግን በመንጎቹ ምትክ እርሱና ቤቱ ላይ ቅጣቱ እንዲፈጸም ጠየቀ፡፡ በጸሎቱ ስለእነርሱም “ጌታ ሆይ እኔ በድያለሁ፤ ጠማማም ሥራ አድርጌአለሁ፤ እነዚህ በጎች ግን እነርሱ ምን አደረጉ፤ እጅህ በእኔና በአባቴ ቤት ላይ አንድትሆን እለምንሃለሁ፡፡”(፪ሳሙ.፳፬፥፲፯)ብሎ እግዚአብሔር አምላክን አጥብቆ ተማጸነ፡፡ ነገር ግን ስለመንጎቻቸው ግድ ስለሌላቸው እረኞች፣ ለእነዚያ እራሳቸውን ብቻ ስለሚያሰማሩ እረኞች ነቢዩ እንዲህ ይወቅሳቸዋል “መንጎቼን የምታጠፉና የምትበትኑ እናንተ እረኞች ሆይ የጌታን ቃል ስሙ እግዚአብሔር እንዲህ ብሎአል፡፡ እረኛ መንጎቹን እንዲጎበኝ አንዲሁ እረኞችን የምጎበኝበት ጊዜ ይመጣልና ወዮላችሁ፡፡  በዚያን ጊዜ በጎቼን ከእጃችሁ እፈልጋቸዋለሁ፡፡

 

እናንተ ሰነፍ እረኞች ሆይ ከበጎቼ ፀጉር ለበሳችሁ፡፡ ከሰባውም ተመገባችሁ በጎቼን ግን አላሰማራችሁም፣ የታመመውን አላዳናችሁም፣ የተሰበረውን አልጠገናችሁም፣ የደከመውን አላበረታችሁም የጠፋውንና የባዘነውን አልፈለጋችሁም፣ ብርቱውንና የሰባውን አሰማራችሁ ነገር ግን እነርሱን በግፍ አጠፋችኋቸው፡፡ እናንተ የሰባውን ገፋችሁ በላችሁ፣ ከእግራችሁ ሥር ያለውን ረገጣችሁ፡፡ እናንተ ከጥሩ ውኃ ትጠጣላችሁ ከእናንተ የተረፈውን ውኃ ግን በእግራችሁ ታደፈርሳላችሁ፡፡ የእኔ በጎች እናንተ ባጠፋችሁት መስክ ታሰማሯቸዋላችሁ፡፡ በእግራችሁም ያደፈረሳችሁትንም ውኃ ታጠጧቸኋላችሁ” ይላል፡፡ (ዘካ. ፲፩፥፲፭-፲፯)  እነዚህ እረኞች ስስት የሠለጠነባቸው፣ የማያስተውሉ እረኞች እና ባለሙያተኞች ናቸው፡፡ እነዚህ መንጎቻቸውን አይመግቡም ወይም አይጠብቁም ወይም ለተኩሎች አሳልፈው የሚሰጡ ጨካኝ እረኞች ናችው፡፡ ነገር ግን የእረኞች አለቃ ይመጣል፤ መንጎቹንም በየስማቸው ይጠራል፤ ይጎበኛቸዋል፤ ስለመንጎቹም ደኅንነት ይመረምራል፡፡ የበጎቹንም እረኞች ከፊቱ ያቆማቸዋል፤ እንደ በደላቸውም መጠን ይከፍላቸዋል፤ እንደሥራቸውም መጠን ይመልስባቸዋል፡፡

መንጎቻቸውን በመልካም ላሰማሩ እረኞች ግን የእረኞች አለቃ ደስ ያሰኛቸዋል፤ ዘለዓለማዊ ሕይወትንና ዕረፍትን ይሰጣቸዋል፡፡ አንተ የማታስተውል ሰነፍ እረኛ ሆይ ሰለመተላለፍህ ቀኝ ክንድህንና ቀኝ ዐይንህን ታጠፋታለህ፡፡ ምክንያቱም ስለበጎቼ የሚሞተው ይሙት፤ የሚጠፋውም ይጥፋ ቅሬታም ካለው ሥጋውን እቀራመተዋለሁ የምትል ሆነሃልና፡፡ ስለዚህም ቀኝ ዐይንህን አጠፋዋለሁ ቀኝ እጅህንም ልምሾ አደርገዋለሁ፡፡ መማለጃን የሚጠብቁትን ዐይኖችህ ይጠፋሉ፤ በጽድቅ የማይፍርደውም እጆችህም የማይጠቅሙ ልሙሾዎች ይሆናሉ፡፡  ብታስተውለው እንደ አንተ በመስኩ ላይ የተሰማሩት በጎቼ የሰዎች ልጆች ናቸው፡፡ እኔ ግን ያንተ ጌታ የሆነኩ አምላክህ ነኝ፡፡ እነሆ በዛ ጊዜ መንጎቼን በለመለመ መስክ በመልካም አሰማራቸዋለሁ፡፡ “መልካም እረኞ ነፍሱን ስለበጎቼ አሳልፎ ይሰጣል፡፡” እንዲሁም “ወደዚህ የማመጣቸው ሌሎች በጎች አሉኝ፡፡ እናም አንድ መንጋ ይሆናሉ፡፡” አንድም እረኛ ይኖራቸዋል፡፡ አባቴ ስለሚያፈቅረኝ ስለበጎቼ ራሴን አሳልፌ እሰጣለሁ፡፡” እንዲሁም “እኔ በር ነኝ ሁሉም በእኔ በርነት ይገባል በእኔም ምክንያት በሕይወት ይኖራል ፡፡ እናም ይወጣል ይገባል ይወጣል ይላል ጌታ፡፡…”

yeledete 2

የልደት ምንባብ ከአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ

ታኅሣሥ 24/2004 ዓ.ም

ይህ ጽሑፍ  ከአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ “መጽሐፈ ምሥጢር”  ምዕራፍ 6 ላይ “የልደት ምንባብ” ከሚለው የተወሰደ ነው፡፡

{gallery count=1 width=350 height=300 counter=1 links=0 alignment=center animation=3000}ledet04{/gallery}

“… እግዚአብሔርም ሳሙኤልን “ልዩ ቅብዓት ይዘህ ወደ ቤተልሔም ሒድና ወደ ዕሤይ ቤት ግባ ከልጆቹ እኔ የመረጥኩትን አሳይሃለሁ” አለው፡፡ ሳሙኤልም ወደ ቤተልሔም ደረሰ ከዕሤይ አጥር ግቢ ገብቶ “ልጆችህን አምጣቸው” አለው፡፡ እርሱም ኤልያብን አምጥቶ ለእግዚአብሔር ሹመት የሚገባ ይህ ነው አለ፡፡ እግዚአብሔርም የመረጥኩት ይህን አይደለም አለው፡፡

ዳግመኛ ሳሙኤል አሚናዳብን አስመጥቶ፣ በእግዚአብሔር ፊትም አቆመው፡፡ እግዚአብሔር “ይህንንም አልመረጥኩትም አለ፡፡ ዕሤይ ስድስቱን ልጆቹን አቀረበለት፡፡  በሳሙኤል ፊትም የእግዚአብሔር ምርጫ በእነርሱ ላይ አልሠመረም፤ ሳሙኤል ዕሤይን “የቀረ ሌላ ልጅ አለህን?” አለው፡፡ እርሱም፡- “ታናሹ ገና ቀርቶአል፣ እነሆም በጎችን ይጠብቃል” አለ፡፡ ሳሙኤልም “በፍጥነት ልከህ አስመጣው” አለው፡፡ ዳዊትን አምጥተው በሳሙኤል ፊት አቆሙት፤ እግዚአብሔር ሳሙኤልን “ያልኩህ ይህ ነውና ተነሥተህ ቅባው” አለ፡፡ (1ሳሙ.16፡1-13)

yeledete 2

በሌላም ቃል “አገልጋዬ ዳዊትን አገኘሁት፤ ልዩ ዘይትንም ቀባሁት ኀይሌ ትረዳዋለች፣ ሥልጣኔም ታጸናዋለችና ጠላት በእርሱ ላይ አይሠለጥንበትም፣ የዓመፅ ልጆችም መከራ ማምጣትን አይደግሙም፣ ጠላቶቹንም ከፊቱ አጠፋለሁ፣ የሚጠሉትን አዋርዳቸዋለሁ፣ ይቅርታዬና ቸርነቴ ከእርሱ ጋር ነው በስሜም ሥልጣኑ ከፍ ከፍ ይላል፤ ግዛቱንም ከጽንፍ እስከ ጽንፍ አደርግለታለሁ፤ ሥልጣኑም ከዳር እስከ ዳር ይሆናል እርሱም አባቴ ይለኛል እኔም ልጄ እለዋለሁ፤ በዐራቱ ማእዘን ከነገሡት ነገሥታት ይልቅ ታላቅ ንጉሥ አደርገዋለሁ፡፡  (መዝ.88፡20-27) በሌላ ቃልም እኔ ለዳዊት ሥልጣንን እሰጣለሁ ለቀባሁት መብራትን አዘጋጃለሁ፤ ጠላቶቹንም የኀፍረት ማቅን አለብሳቸዋለሁ፤ በእርሱ ቅድስናዬ ያፈራል፡፡” (መዝ.131፡17-18) በሌላም ቃል “ቀብቶ ላነገሠው ምሕረትን ያደርግለታል፤ ለዳዊትና ለዘሩ እስከ ዘላለም ድረስ ያደርጋል” ይላል፡፡

ኢሳይያስም “ከዕሤይ ሥር በትር ትወጣለች፣ ከግንዱም አበባ ይወጣል፡፡ በእርሱም  የእግዚአብሔር መንፈስ ያርፍበታል” አለ፡፡(ኢሳ.11፡1) እነሆ የእግዚአብሔር በረከት ወደ ዳዊት ቤት አለፈች፡፡ የዘይት ቀንድ በራሱ ላይ ፈላ፡፡ የመንግሥትም በትር ከቤቱ በቀለች፡፡ ከዘሩ እግዚአብሔር የመድኀኒታችንን ሥልጣን አስነሥቶአልና ዳግመኛ ወደ ገሊላ ነገሥታት አውራጃዎችም አልገባም፡፡ የሄሮድስን ሴት ልጅ አልመረጣትም፡፡ ከታላላቅ የይሁዳ ነገሥታት ይልቅ የድሆችን ሴት ልጅ መረጠ እንጂ እግዚአብሔር ፈጣሪ ሲሆን በሴት ማኅፀን አደረ፡፡ ደም ግባቷን ወድዶ ባፈቀራት ጊዜ በጽርሐ አርያም እናት ትሆነው ዘንድ ወደ ሰማይ አላወጣትም፡፡ እርሱ ራሱ ወርዶ በጠራቢው በዮሴፍ ቤት አደረ /ሰው ሆነ/ እንጂ፡፡ በዚያ ትፀንሰው ዘንድ ወደ ኪሩቤል ሠረገላ ላይ አላወጣትም፡፡ ናዝሬት ገሊላ በምትባል አገር ሳለች ራሱ በማኅፀኗ አደረ እንጂ፡፡ በጌትነቱ ሰው በሆነ ጊዜ አላሰፋትም፡፡ ገብርኤልን “በሆዷ ዘጠኝ ወር ትሸከመኝ ዘንድ ድንግልን ወደዚህ አምጣት” አላለውም፡፡

እርሱ ትሕትናዋን ተሳትፎ ከገብርኤል ጋር ወርዶ ወደ ድኻይቱ ቤት ገባ፡፡ መልአኩ “መንፈስ ቅዱስ ወዳንቺ ይመጣል” ባላት ጊዜ የአምላክBeserate እናት ለመሆን በመንፈስ ቅዱስ መውረድ ከበረች፡፡ “የልዑል ኀይልም ይጋርድሻል” ብሎ በደገመ ጊዜ በሰማያዊ አባቱ ሥልጣን ወልድን ለመፅነስ በቃች፡፡ “ከአንቺ የሚወለደው የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል” አላት፡፡ ያን ጊዜ ከእርሷ የሚወለደው የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ያንን ተረዳች፡፡ እርሷም ወልድ ከአባቱ ጋር ወዳለበት ወደ ጽርሐ አርያም ኅሊናዋን አወጣች /አሳረገች/፡፡ እርሱም ራሱን ዝቅ አድርጎ በትሐትና ከሰማየ ሰማያት ወርዶ በማኅፀኗ ተፀነሰ፡፡ ዳግመኛ ድንግል መልአኩን “እንደ ቃልህ ይደረግልኝ” አለችው፡፡(ሉቃ.1፡26-32) ያን ጊዜ አካላዊ ቃል ከእርሷ በተዋሕዶ ሰው ሆነ፡፡ አይታው እንዳትደነግጥ ተመልክታው እንዳትፈራ  ኪሩቤልን ከእርሱ ጋር አላመጣም፡፡ በወዲያኛው ዓለም በአባቱ ሥልጣን እንዳለ በዚህ ዓለም ለቅዱሳን ተልእኮ የሚጠቅም ምድራዊ ሕግን ሠራ፤ የማይታይ የማይመረመር ኀይል በዚህ ዓለም እርሱ ብቻውን በእናቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ማኅፀን ህልው ሆነ፤ በወዲያኛውም ዓለም የማይዳሰስ መለኮት ከሚዳሰስ ሥጋ ጋር በዚህ አለ፡፡

yeledeteበወዲያኛው ዓለም የእግዚአብሔርን መንበር የተሸከሙ ኪሩቤል አሉ፡፡ በወዲህኛውም ዓለም ሥጋ የተገኘባቸው ዐራቱ ባሕርያት አሉ፡፡ ወልድ በወዲያኛው ዓለም  አባት ያለ እናት በዚህ እናት ያለ ምድራዊ አባት አለው፡፡ በወዲያኛው ዓለም ቅዱስ ገብርኤል በፍርሃት ይቆማል፡፡ በዚህኛው ዓለም ቅዱስ ገብርኤል በደስታ ያበሥራል፡፡ በዚያ በጽርሐ አርያም ከአብ የማይታይና የሚደነቅ የልደት ክብር አለው፡፡ በወዲያኛው ዓለም ሰማያውያን ካህናት በወርቅ ጽንሐሕ የዕጣን መዓዛ ያቀርቡለታል፡፡ በዚህኛው ዓለም ከሰብአ ሰገል ወርቅ፣ ዕጣን፣ ከርቤ ይቀርብለታል፡፡

በወዲያኛው ዓለም ከግርማው የተነሣ ሱራፌልና ኪሩቤል ይንቀጠቀጣሉ፡፡ በዚህኛው ዓለም ድንግል ማርያም ትታቀፈዋለች፣ ሰሎሜም ትላላከዋለች፡፡ ከዚያ በፊቱ የመባርቅት ብልጭልጭታ ከፊቱ ይወጣል የእሳት ነበልባልም ከአዳራሹ ቅጥር ይወጣል፡፡ በዚህ አህያና ላም በእስትንፋሳቸው ያሟሙቁታል፡፡

በዚያ የእሳት መንበር በዚህ የድንጋይ ዋሻ አለ፡፡ በወዲያኛው የተሠራ የሰማይ ጠፈር (ዘፀ.24፡10) በዚህ የላሞች ማደሪያ /ማረፊያው/ ሆነ፡፡ በዚያ ትጉሃን መላእክት የሚገናኙበት ኢየሩሳሌም ሰማያዊት፤ በዚህኛው የእረኞች ማደሪያ የሆነች ዋሻ አለች፡፡ ዘመኑ የማይታወቅ ተብሎ በዳንኤል የተነገረለት ብሉየ መዋዕል አምላክ በወዲህኛው ዓለም የዕድሜው ቁጥር በሰው መጠን የሆነ አረጋዊ ዮሴፍ አለ፡፡ በጽርሐ አርያም ፀንሳው ቢሆን ኖሮ ክብርና ልዕልና ለብቻዋ በሆነ ነበር፡፡ እኛም በእርሷ ክብር ክብርን ባላገኘን ነበር፡፡ በሰማያት የሚደረገውን ምሥጢር ምን እናውቃለን? በአርያም ያለውን ስውር ነገር በምን እናየው ነበር?

በኪሩቤል ሠረገላ ላይ እንዳለ ብትወልደው ኖሮ በእቅፍ መያዙን ማን ባየ ነበር፤ አካሉንስ ማን በዳሰሰው ነበር በምድር ላይ ባይመላለስ ኖሮ የጥምቀቱን ምልክት ማን ባየ ነበር፤ የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት ብሎ አብ ለማን በመሰከረ ነበር፤ መንፈስ ቅዱስስ በነጭ ርግብ አምሳል በማን ራስ ላይ በወረደ ነበር፤ የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት ባይገለጽ ኖሮ በማን ስም እንጠመቅ ነበር? ስለዚህ ደቀ መዛሙርቱን “ሒዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቋቸው” አላቸው፡፡ (ማቴ.28፡19) አብ ማን ነው? ወልድስ ማን ነው? መንፈስ ቅዱስ ማን ነው? እንዳይሉ በዮርዳኖስ ወንዝ የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት ተገለጠ፤ በሰው ልጅ አምሳል ባይጎለምስ፣በሰው ልጅ አምሳል ባይታይ እኛን ስለማዳን ማን መከራን በተቀበለ ነበር? እነሆ! የሰው ልጅ ከሰማይ መላእክት ይልቅ ከበረ፤ እግዚአብሔር ከሴት ተወልዷልና፡፡ ስለዚህ ነገር ጳውሎስ “የአብርሃምን ዘር ይዞአል እንጂ የያዘው የመላእክትን አይደለም” አለ፡፡(ዕብ.2፡16)

አሁንም የፎጢኖስን ተግሳፅ ፈጽመን የአምላክን ልጅ ሰው መሆን በዓል እናድርግ፡፡ ለተሸከመችው ማኅፀን ምስጋና እናቅርብ፡፡ ላቀፉት ጉልበቶች እንስገድ፤ ላሳደጉት ጡቶች እንዘምር፤ የዳሰሱትን እጆች እናመስግን፤ ለሳሙት ከንፈሮች እናሸብሽብ ከእረኞች ጋር እናመስግን፤ ከሰብአ ሰገል ጋር እጅ መንሻ እናቅርብ፡፡ እንደ ዮሴፍ እናድንቅ፤ እንደ ሰሎሜም እንላላክ፡፡ በተኛበት በረት እንስገድ፤ በተጠቀለለበት በረት እንበርከክ፡፡ ሰውን ለወደደ ለእግዚአብሔር በላይ በሰማይ ክብር ምስጋና፣ ሰላምም በምድር ይሁን እንበል፡፡ እግዚአብሔር ምስጋና ይግባውና ሰው ሆነ የሰው ልጅም የእግዚአብሔር እናት ሆነች፡፡ ለእርሱ ክብር ምስጋና ለእርሷም የክብር ስግደት ለዘለዓለም ይሁን፡፡ አሜን፡፡

ቤተ ክርስቲያንን ያቃለላት፣ የወልድን መለኮት የለየ፣ የሃይማኖትን ገመድ የቆረጣት የገሞራ ሐረግ የፎጢኖስ ተግሳጽ ተፈጸመ፡፡ …Aba Georgise ze gasecha ጊዮርጊስ የቤተ ክርስቲያን ካህናት ትምህርት ልጅ፣ የሃይማኖትን መንገድ የወደደ ይህን ተናገረው፡፡ ድንግል ተቀዳሚ ተከታይ ከሌለው ከበኲር ልጇ ዘንድ ኀጢአቱን ታስተሰርይለት ዘንድ፣ በዚህ ዓለም ከመከራ ታድነው ዘንድ በሚመጣው ዓለም ወደ ቤቷ ታስገባው ዘንድ፣ ከሚደነቅ የሕይወት ማዕድ ታበላው ዘንድ፣ ከምሥጢር ወይን ታጠጣው ዘንድ፣ ለዘወትር መከራን እንዳያይ ከመከራ ደጃፍ ታርቀው ዘንድ ለምኑለት፡፡ ይህን መጽሐፍ ሥነ ምግባሯ በተከበረበት፣ የክብሯ ገናናነት በታየበት በመታሰቢያዋ ዕለት ታኅሣሥ 29 ቀን እንዲነበብ አዘዘ፡፡ ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

“ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ”

ታኅሣሥ  22/2004 ዓ.ም
በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ

 

በዛሬው ቀን ዓለም ለመዳን የቅድስት ድንግል ማርያምን ይሁንታን የፈለገበት ቀን ነበር፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ከምንም በላይ የሰውን ነጻ ፈቃድ ስለሚያከብር መልአኩን ቅዱስ ገብርኤልን ወደ ቅድስት ድንግል ማርያም ሲልከው ፈቃዱዋን ይጠይቃት ዘንድ ነበር፡፡ ይህ ማለት ምን ማለት መሰላችሁ “እነሆ በደጅህ ቆሜ አንኳኳለሁ ማንም ድምፄን ቢሰማ ደጁንም ቢከፍትልኝ ወደ እርሱ እገባለሁ ከእርሱም ጋር እራት እበላለሁ እርሱም ከእኔ ጋር ይበላል”(ራእ.3፡20) እንዳለው ዓይነት ነው፡፡ ነገር ግን በይዘቱ የቅድስት እናታችን  ይሁንታ በጣም የተለየ ነው፡፡ ስለዚህም የዓለም መዳን በእርሱዋ ይሁንታ ላይ ነውና እግዚአብሔር በመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በኩል የቅድስት ድንግል ማርያምን ፈቃድ ጠየቀ፡፡ ለእርሱዋም በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል አንደበት እግዚአብሔር ቃል ለሰው ልጆች መዳን ከእርሱዋ ተፀንሶ ለመወለድ ፈቃዱ እንደሆነ፣ እርሱዋንም የዘለዓለም እናቱና የሰው ልጆችን ፍጹም የመውደዱ ምልክት ሊያደርጋት እንደወደደ አበሰራት፡፡ ቅድስት እናታችንም ፍጹም ትወደውና ታመልከው የነበረው እግዚአብሔር ከእርሱዋ ተወልዶ ዓለምን ለማዳን መፍቀዱን ስትሰማ በፍጹም ደስታ ተሞልታ ግሩም በሆነ ትሕትና “ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ” “እንደቃልህ ይደረግልኝ” በማለት ዓለምን እፎይ አሰኘቻት፡፡ እስከዛች ጊዜ ድረስ ዓለም በጭንቀት ተውጣ የእርሱዋን መልስ በጉጉት ትጠባበቅ ነበር፡፡

የቅድስት እናታችን የይሁንታ ቃል በተሰማ ጊዜ በሲኦል ያሉ ቅዱሳት ነፍሳት በደስታ ቦረቁ፡፡ በአካለ ሥጋ የነበሩ ነቢያትና ቅዱሳን እንደ እምቦሳ በደስታ ዘለሉ፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልም በደስታ ተውጦ ለመላእክት ጉባኤ “በቅድስት ድንግል ማርያም የይሁንታ ቃል ምክንያት ዓለም ዳነች” ብሎ የምስራች አላቸው፡፡ ነቢዩ ሕዝቅኤል “… በዙፋኑም አምሳያ ላይ እንደ ሰው መልክ አምሳያ ነበረ” (ሕዝ.1፡26) ብሎ እንደገለጠው እግዚአብሔር አምላክ ለመላእክት በሰው ምሳሌ ተገልጦ ይታያቸው ነበር እንጂ እርሱን ገጽ በገጽ ለመመልከት አልበቁም ነበር፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ገብርኤል የፀንሰቱን ነገር ለመላእክት በነገራቸው ጊዜ ፈጣሪያቸው እግዚአብሔር ቃል ሰው በመሆን በአካል ሊያዩት እንደተቃረቡ ተረድተው ከዚህ በፊት ተሰምቶ የማያውቅ ታላቅ የሆነ የደስታ ዝማሬ ዘመሩ፡፡ በዚያን ጊዜ  ቅዱሳን መላእክት ደስታቸው ድርብ ነበር፡፡ የመጀመሪያው ደስታቸው የሰው ልጆች መዳን ሲሆን ሁለተኛው ግን አምላካቸውን በጠባብ ደረት በአጭር ቁመት ተወስኖ ለማየት በመብቃታቸው ነበር፡፡ “ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ሥምረቱ ለሰብእ!!!