የጥምቀት በዓል አከባበር በጃን ሜዳ

 ጥር 11 ቀን 2006 ዓ.ም

የከተራ በዓል ጥር 10 ቀን 2006 ዓ.ም. በጃሜዳ ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በድምቀት ተከብሮ የዋለ ሲሆን፤ ምሽቱን ደግሞ በስብከተ ወንጌልና በዝማሬ ቀጥሎ በሥርዓተ ቅዳሴ ተፈጽሟል፡፡ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ የጥምቀተ ባሕር ቦታዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ የከተራ በዓል በድምቀት ተከብሯል፡፡

ጥር 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ከሌሊቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ልዩ ልዩ መርሐ ግብሮች እየተካሔዱ ሲሆን፤ ጃን ሜዳ የሚካሔደው ሥነሥርዓት ቅዱስነታቸውና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በጸሎተ ወንጌል ተጀምሮ የጥምቀት መርሐ ግብሩ ይቀጥላል፡፡ የእለቱ ተረኛ የሆነው የወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ዝማሬ የበዓሉ አካል እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡