የይሁዳ ሰላምታ የቀሪ ሒሳብ ማስተካከያ ነው

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይሁዳን ከሐዋርያት እንደ አንዱ የመረጠበት ምስጢር እጅግ ጥልቅ ነው፡፡ ይህን ባናውቅ፣ ታሪኩ ባይጻፍና መምህራኑም በየጊዜው ባይነግሩን ኖሮ ዛሬ ብዙዎቻችን እንጨነቅ እንታወክም ነበር፡፡ እርሱን እንድናስታውሰው ያደረገን ደግሞ «ሃይማኖተ አበው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማኅበር» ያቀረበው ተደጋጋሚ ጥያቄ ነበር፤ በቤተ ክርስቲያኒቱ ፈቃድ ተሰጥቶት የመንቀሳቀስ ጥያቄ፡፡ ጉዳዩን በቀጥታ ከማየታችን በፊት ግን ጌታችን ይሁዳን ሐዋርያ አድርጎ በመምረጡ ካስተማረን ትምህርት እንነሣ፡፡
በትውፊት እንደሚታወቀው ይሁዳ ሳያውቀውም ቢሆን አባቱን ገድሎ እናቱን አግብቶ ይኖርበት ከነበረው ሕይወት የመጣ ሰው ነው፡፡ ጌታችን ንስሐውን ተቀብሎ እርሱን ከሐዋርያት እናቱንም ከቅዱሳት አንስት ደመራቸው፡፡ ጌታ አምላክ ነውና የይሁዳን ምንነት ብቻ ሳይሆን ወደፊት ርሱንም እንደሚሸጠው እያወቀ ለምን ሐዋርያው አደረገው) ልንል እንችላለን፡፡ ቢያንስ የሚከተሉትን ነገሮች እንድንማር ነው፡፡

ጌታ ለሚመለሱት ሁሉ እውነተኛ መሐሪ ነው፡፡ በተመለ ሰበት ጊዜ ፈጽሞ ይቅር ብሎ ወደ ማኅበረ ሐዋርያት ማም ጣቱ ፍጹም ፍቅሩንና ለተልእኮ የሚመርጠውም ሰው ተነሳሒ መሆኑን ያሳየናል፡፡ ጌታችን ድንግላዊ ዮሐንስን ብቻ አልመረጠም፤ ይህ እንግዲህ የሐዲስ ኪዳኗ ቤተ ክርስቲያን እውነተኛ ተነሳሕያን ለቅድስና የሚያበቃ የጽድቅ በር መክ ፈቷን የሚያውጅ ነበር፡፡ በዚህም የጌታችንን ፍጹም ይቅር ታና የምርጫውን ፍጹምነት እንማርበታለን፡፡

ከዚሁ ጋር ተያይዞም ጌታችን ምንም አምላክ በመሆኑ የነገውን የይሁዳን ድርጊት ቢያውቅም ገና ባልበደለው በደል ግን ቀድሞ አልገፋውም፡፡ በዛሬ ማንነቱ ብቻ የተቀበለውን ሰው ክብሩንም ሓሳሩንም የሚወስነው ዛሬውኑ በሠራው ሥራ መሆኑን ለማስተማር ነው፡፡ የዚህ ተጨማሪ ጉዳይ ደግሞ ክፉን ሰው ምክንያት ማሳጣት የሚገባ መሆኑንም ለመናገር ነው፡፡
 
ይሁዳን በመዋዕለ ስብከቱ ከክብር ሳያሳንስ፣ መዓርግ በመስጠት ያኖረው በኋላ ሹመት አጉድሎብኝ ነው እንዳይ ለውም ጭምር ነበር፡፡ በዐሥራት ላይ ሾሞ፤ የገንዘብ ፍላጐቱንም እንደተመኘ ይወጣለት ዘንድ ነጻ ፈቃድን ሰጥቶ ስርቆቱን ታግሶታል፡፡ ጌታ ዐሥራቱን በሌላ ሐዋርያ እጅ ቢያደርገው እንዲጠበቅ እያወቀ ለይሁዳ የሰጠው ጾሩ ቢቀልለት ብሎ ብቻ ሳይሆን ምክንያትም ሊያሳጣው ነውና፡፡ ይህም ከሆነ በኋላ ሲሰርቅ በፍጹም ታግሦታል፡፡ ስለዚህም ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ቤተ ክርስቲያን ዘክርስቶስ እንደ ይሁዳ ሙዳየ ምጽዋት የሚገለብጡትን እንደ ይሁዳ ታግሣቸው ትኖራለች፡፡ የይሁዳን የሌብነት ደረጃ ከፍተኛ መሆኑን ያየነው ደግሞ በጸሎተ ሐሙስ ዕለት ማታ እጁን ከወጭቱ መስደዱን ጌታ ገልጦ በመናገሩ ነው፡፡ «የለመደ ልማድ ከማድ ያሰርቃል» እንደሚሉት እንኳን ለሌላ ከመጣው ለራሱም ከተሰጠው የሚሰርቅ ምን ያህል ቢከፋ ይሆን) ዛሬም እንደ ይሁዳ ውሳጤ ውሳጢት /ቅድስተ ቅዱሳን/ ገብተው ለእነርሱ ብቻ የተፈቀ ደው ምስጢር ላይ እጃቸውን ያለአግባብ የሚጭኑኮ መጻሕፍቱንና ንዋያቱን የሚሰርቁ ሲያጋጥሙ ቤተ ክርስቲያን ብታዝንም የማትታወከው ነገሩን ቀድማ ከይሁዳ ሕይወት ስለ ተረዳችው ነው፡፡ ከላይ የጠቀስናቸውን ሁሉ ብዙ ጊዜ ሰምተናቸው ይሆናል፡፡ ችግሮቹም በየጊዜው የሚገጥሙን ስለሆነ አሁን አሁን አያስደንቁንም፡፡

ትልቁና ዋናው ጉዳይ ይልቁንም ለዛሬው ጉዳይችን የሚቀ ርበው ይሁዳ በመጨረሻው ሰዓት የፈጸመው ድርጊት ነው፡፡ ይሁዳ ተጠቃሚ ስለነበር ከሐዋርያት ጋር ጌታን እየተከተለ ይቆይ እንጂ ልቡ እንደ ጸሐፍት ፈሪሳውያን ነበር፡፡ ይህም የታወቀው ሠላሳ ብር የጐደለበት በመሰለውና ማንነቱ በተነገ ረው ጊዜ ወደ እነርሱ በማምራቱ ነበር፡፡ ጌታም ራሱ ይሁዳ ባለበት ስለይሁዳ የተናገረው በአካል ከሐዋርያት ጋር ቢሆንም በምግባርና በአመለካከት ከእነ ሀና እና ቀያፋ ጋር በመሆኑ ነበር፡፡ በይሁዳ ሕሊና ያለው ግን አሁንም ሌላ ብልጠት ነበር፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ራሱን የተሻለ አሳቢ አድርጎ ስለወሰደ ከሐዋርያት ተደብቆ ከፈሪሳውያን ገንዘብ ተቀብሎ ጌታን አሳልፎ ከሰጠ በኋላ ጌታ በተአምራት ሲሰወርለት ገንዘቡንም አግኝቶ ከሐዋርያትም ጋር ሆኖ ለመኖር ነበር፡፡ ይህ ባልተሳካለት ጊዜ /ጌታ ራሱን አሳልፎ በሰጠ ጊዜ/ ደግሞ ፈጥኖ የታነቀው ሲኦል ገብቼ ካገኘኝም ትቶኝ አይወጣም ብሎ ጽድቁንም በብልጠትና በቀመር ሊፈጽም ነበር፡፡ ሁሉም ግን አልተሳካም፡፡ ድኅነትን በየዋሕነትና በእውነተኛ ንስሐ እንጂ በብልጠትና በቀመር ሊያገኙት አይቻልምና፡፡

ይሁዳ ከማርያም ባለሽቱዋ ቀረብኝ ያለውን ገንዘብ ለማግኘት የተጠቀመበት ስልት «ሰላምታ» ነበር፡፡ ነገሩን ከሊቃነ ካህናቱ ጋር ከጨረሰ በኋላ እርሱ «ሰላም» ብሎ ሊሰጥ በዚህም እነርሱ ጌታን ይይዛሉ፤ ለእርሱ ደግሞ እንደመሰለው በስውር ገንዘቡን ተቀብሎ ከጌታም ጋር ሊኖር ነበር፡፡ የዚህ ነገር ፍጻሜው ታላቅ ጥፋት መሆኑን ብናውቅም ነገር ግን ቤተ ክርስቲያን ይህን ስልት እየተጠቀሙ ደሟን የሚያፈስሱ ጠላቶቿ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ከቤተ ክርስቲያን እንደማይጠፉ እውነተኛውን ትምህ ርት ትቶልን አለፈ፡፡

በዕሥራ ምእቱ መጨረሻ በ«ሃይማኖተ አበው የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማኅበር» ስም የሚወጡት የሚወርዱት «ውስጠ ዘ» ዎች ጥያቄም ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡ እንደ ይሁዳ ቤተ ክርስቲያን ነበሩ፤ እንደ እርሱ ኮረጆአቸውን ይዘው ከዓለም አቀፍ የፕሮቴስታንት ተቋማት የሚፈልጉትን ሰበሰቡ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ግን እንደ ይሁዳ አቅርባ ሾመቻቸው፡፡ ከአንድም ሁለት ጊዜ ጥያቄያቸውን ተቀብላ ፈቃድ ሰጥታ ቢሮ ከፍታ ሰየመቻቸው፡፡ እነርሱ ግን ከግብራቸው አልተመለሱምና ማኅ በሩ በይፋ ተዘጋ፡፡ ደግነቱ ይሁዳ ገንዘቡን ለራሱ በተመኘ ጊዜ ሐዋርያትን ጨምሮ ለማሳመጽ «ይህ ሽቶ ተሽጦ ለድሆች ያልተሰጠ ለምንድን ነው?» በሚል ደስ በሚያሰኝ ቃል ቅስቀ ሳውን ቢያደርግም ከሐዋርያት የተከተለው አለመኖሩ ነው፡፡ ሃይማኖተ አበውም ከጥንቶቹ ቀናዕያንና ንጹሐን አባላቱ እር ሱን የተከተለው የለም፡፡ እነርሱ እንደ ሐዋርያት በታማኝነት አገልግሎታቸውን ቀጥለዋልና፡፡ ይሁን እንጂ በመካከለኛ ዕድሜ ከነበሩ ወጣት ዘማርያን መካከል ለሙሉ ወንጌል፣ ለሬማና ለመሳሰሉት የገበራቸው ወንድሞቻችንና እኅቶቻችን የሚዘነጉ አይደሉም፤ አሁንም የሚያሳዝኑን ሆነው ቀርተዋልና፡፡

ይህ ሁሉ ሳያንሰው አሁንም በተድበሰበሰ መንገድ እንደገና ፈቃድ ይሰጠኝ፤ ቢሮ ልክፈት የሚለው ጥያቄውን አቅርቧል፡፡ ይህ ጥያቄ ጥንት ማኅበሩን መሥርተው በቅን መንገድ ቤተ ክርስቲያንን አገልግለው፤ የማኅበሩ አመራር ማኅበሩን ወደ ተሳሳተ አቅጣጫ ሲወሰደውም እነርሱ በቤተ ክርስቲያናቸው ጸንተው ከቀጠሉትና አሁንም እያገለገሉ ካሉት እውተኛ ልጆቿ ቀርቦ ቢሆን ኖሮ ምን ያህል ያስደሰት ነበር፡፡ ስለዚህም እነዚህን አካላቱን ለስምና ለዝና ብቻ የሚፈልጋቸውና የተደበቀ ጅምር ዓላማውን /ፕሮቴስታንት የማድረግ ግቡን/ ይዞ ሲንቀሳ ቀስ የኖረው የማኅበሩ አመራር ግልጽ ባልሆነ ሁኔታ በሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ በኩልና ራሱም አድበስብሶ ያለ ማንም ሰው ፊርማ ያቀረበው ጥያቄ ዝም ተብሎ የሚታለፍ አይደለም፡፡

ማእምረ ኅቡአት ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰወረውን ዓላማ የሚ ገልጥበት ጊዜው ሩቅ ባይሆንም እንዲህ ያለው ቀረቤታ ከይ ሁዳ ሰላምታ ተለይቶ የሚታይ ሊሆንም አይችልም፡፡ ይሁዳ ጌታችንን ሰላም ያለው በአይሁድ ለማስያዝና ቀረብኝ ያለውን ገንዘብ ለማግኘት እንደነበረው ሁሉ የዚህ ጥያቄ ዓላማም ያው ቀሪ ሒሳቤን ላወራርድ የማለት ይመስላል፡፡ ለእርሱ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን የዚህን «ሰላምታ» ትርጉም ነገሮናል፤ መልእክቱንም አስተምሮናል፡፡ ምክንያቱም ጌታ ይሁዳን ንስሐም ሲገባ ያውቀዋል፤ ሊያታልለውም ሲመጣ ያውቀዋል፡፡ ይሁዳ አጥፍቶ ነው የወጣው፤ ስለዚህ ሲመለስ ንስሐ ይጠበቅበት ነበር፡፡ የእርሱ መልስ ግን ቀሪ ሒሳብ የማወራረድ ስለነበር ለንስሐ ፈቃደኛ አልነበረም፡፡ ስለዚህም በሰላምታው ሸንግሎ ቀሪ ሒሳቡን ለመውሰድ የመጨረሻ ዕድሉን ተጠቀመ፡፡

የ«ሃይማኖተ አበው» መሪዎችም እውነተኞች ቢሆኑ ኖሮ ማኅበር እንደመሆኑ መጠን ያጠፉትን ጥፋት ራሳቸው ዘርዝረው አቅርበው፤ ለዚያ የዳረጋቸውን ምክንያቱን ለይተው ቤተ ክርስቲያንን ለበደሉበት ይቅርታ ጠይቀው አጥፍተዋቸው ለቀሩት ልጆቿ እውነተኛ ንስሐ ገብተው ቢመለሱ እንዴት ባማረባቸው ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ቢቻል ሌላ ሃይማኖት የገቡትን ለመመለስና ለንስሐ ለማብቃት ቢጥሩ በይፋ ስሕተታቸውን ገልጸው ጥፋታቸውን ነግረው ቢመለሱ ኑሮ አሁንም ያለው አገልግሎት እንኳን ለእነርሱ ሌላም ቢፈጠር የሚጋብዝ ነበር፡፡ ይህን ግን አላደረጉትም፡፡ ሊያደርጉት ሲጥሩም አይታዩም፡፡ ይልቁንም ውስጥ ለውስጥና በድብቅ እንደገና የጨለማ ሥራ፤ የይሁዳ ሸንጐ፡፡ ለሃይማኖተ አበው አመራርና ደጋፊዎቹም ሁልጊዜም ቤተ ክርስቲያን አልገባት /አልበራላት/ ብሎ እንጂ እነርሱማ አይሳሳቱማ፡፡ «እግዚአብሔር ሰማዩን ጠቅልሎ ሸሸ» እንዳለ ሰይጣን፤ «እኔ ወረድኩ» ማለትንማ አይሞክራትማ፡፡ እንዲህ ካለማ እውነት ሊወጣው ነው፡፡ አሁንም ግን ለትክክለኛው መንገድ ጊዜው አልመሸም፤ ልቡ ካለ፡፡
 
ካለበለዚያ ግን ጥያቄው ከይሁዳ ሰላምታ ፍጻሜውም ከእርሱ ፍጻሜ አያልፍም፡፡ ለዚህ ጉዳይ የቀድሞ እውነተኞቹ አባላት ዛሬም እንደ ጥንቱ ሓላፊነት አለባችሁ፡፡ በጎውን ዓላማ ማጥፋትና መንገዱን ማሳታቸው ሳያንሳቸው ጥፋታቸውን በስማችሁ ለማሳት መምጣታቸውን መግለጥ ያለባችሁ እናንተ ናችሁና፡፡ የቤተ ክርስቲያናችን አባቶችም ጌታቸውን በመመሰል ይሁዳን እንደ አመጣጡ እንደሚመልሱት የታመነው ነው፡፡ ንስሐ ሲገባ ይቀበሉታል፤ አሳልፎ ሊሰጥ ሲመጣማ ጌታችን እንደጠየቀው «ለምን ነገር መጣህ)» ብለው ይጠይቁታል እንጂ ዝም አይሉትም፡፡ ስለዚህም ተጠየቅ፤ ለምን ነገር መጣህ) አብረውህስ ያሉት እነማን ናቸው? ሾተሉና ዱላውስ የማን ነው?