የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ስብሰባ ተጠናቀቀ

በግንቦቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ የቤተክርስቲያኒቱን አስተዳደራዊና የልማት ሥራዎች እንዲያከናውን የተመረጠውንና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብ ከት የተነሳውን ችግር ለመፍታት የተጠራው አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ተጠናቀቀ፡፡

ከቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በተሰጠውና ቅዱስ ፓትርያርኩ ባነበቡት መግለጫ እንደተመለከተው፤ በቤተ ክርስቲያኒቱ የሚታየውን የአፈጻጸም ችግር እንዲከታተል በግንቦቱ የርከበ ካህናት ጉባኤ የተሰየመው የሥራ አስ ፈጻሚ ኮሚቴ ከተሰየመበት መደበኛ ተግባሩ ጋር በቤተክርስቲያኒቱ የልማት ዘርፍ ላይ ውጤቶች ለማጠናከር የገቢ ምንጭ የሚያስገኙትን ፕሮጀክቶች ለመፍጠር የሚያስችለውን ረቂቅ አላዘጋጀም ይላል፡፡
ውስጥ ደንቡን አዘጋጅቶ ወደ ሥራ ከመግባቱ በፊት በተፈጠረው ሰው ሠራሽ ችግር ምክንያት የቤተክርስቲያኒቱን ማዕከላዊ አስተዳደር ለትችት የዳረገ ውዘግብ ተፈጠሮ እንደነበር ቅዱስ ፓትርያርኩ ያነበቡት መግለጫ አስታውሶ፤ ቅዱስ ሲኖዶስ የችግሩን መነሻ ከምንጩ በመመርመር ሁሉ ንም በየሥራ ዘርፉ ማስተናገድ የሚያስችል ውሳኔ ማሳለፉንም መግለጫው አመልክቷል፡፡
በቅዱስ ¬ትርያርኩ የተነበበው መግለጫ እንደሚያመለክተው፤ በአም ስተኛው ¬ትርያርክ አሥራ ሰባተኛ ዓመት በዓለ ሲመት አከባበር ማግስት ጀምሮ በተካሄደው ስብሰባ የሚከተሉትን ውሳኔዎች ማሳለፉን አስተውቋል፡፡

አንደኛ ታግዶ የነበረው የቅዱስ ሲኖዶስ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እግዱ ተነስቶ ሊመራበት የሚያስችለውን ውስጠ ደንብ ከሚመድቡለት ባለሙ ያዎች ጋር በመሆን አዘጋጅቶ እን ዲያቀርብ፤ የሚያዘጋጀውን የመተዳ ደርያ ደንብ እስከሚያቀርብ ድረስም ከቤተክርስቲያኒቱ የአመራር አካላት ጋር እየተመካከረ እንዲሠራ መወሰኑን በቅዱስነታቸው የተነበበው መግለጫ ያመለክታል፡፡
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተ ዳደር ችግር በተመለከተ ምልዓተ ጉባኤው በረጋ መንፈስ በነቃ አእ ምሮ ሊተኮርበት የሚገባ ታላቅ ሀገረ ስብከት መሆኑን በመገንዘብ ለውዝግቡ መነሻ የሆነውን የፋይናንስና የመልካም አስተዳደር እጦት ችግር አጣርቶ ለጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የሚያቀርብ ገለልተኛ ኮሚቴ እንዲቋቋም ጉባኤው መስማመቱንም መግለጫው ጠቁሟል፡፡

ቀደም ሲል በቅዱስ ¬ትርያርኩ እገዳ ተጥሎባቸው የነበሩት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የብፁዕ ወቅዱስ ¬ትርያርኩ ረዳት ጳጳስ አቡነ ሳሙኤል እገዳ እስከ ጥቅምት 2002 ሲኖዶስ ስብሰባ እን ዲቆይና እንዲታይ፤ እስከዚያው ድረ ስም ሀገረ ስብከቱ ቅዱስ ሲኖዶስ በሾመው ሥራ አስኪያጅ እየተመ ራና እየተዳደረ እንዲቆይ መወሰኑን ከመግለጫው ለመረዳት ተችሏል፡፡
በመግለጫው ላይ እንደተመለከተው፤ ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተክርስተያኒቱን አጣዳፊ ተግባር ለማከናወን ከተሰየመ በት ሐምሌ 6 ቀን 2001 ዓ.ም ጀምሮ በሀገር ውስጥና በውጭ አህጉር እንዲሁም በተለያዩ ጋዜጦችና መጽሔቶች ሲነገር የሰነበተው፤ ከቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔዎች ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌለው፤ ከእውነት የራቀ ዘይቤ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም ሲልም መግለጫው አስረድቷል፡፡

በቅዱስ ¬ትርያርኩ የተነበበው መግለጫ በመጨረሻ እንዳመለከተው፤ ቅዱስ ሲኖዶስ በየጊዘው ከሚያስተላልፋቸው መልእክቶች መካከል ሰላምና መረጋ ጋት የመጀመሪያውን አጀንዳ ይዘው ይገኛሉ በማለት ጠቁሞ፤ እግዚአብሔርን ማመስገን፣ ቤተክርስቲያንና ወገንን ማገልገል፣ ሀገርን ማልማት የሚቻለው ፍቅር፣ አንድነትና ሰላም ሲኖር ብቻ ነው ይላል፡፡

በመሆኑም ከራሳችን ከእያንዳን ዳችን ከቤተሰባችን ቅዱስ ሲኖዶስ ጀምሮ ሁሉም ኅብረተሰብ በሰላም የተመሠረተ ሕልውና እንዲኖረው በቅዱስ ¬ትርያርኩ የተነበበው መግለጫ ያመለክታል፡፡

በሌላ ዜና የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ብፁዓን አባቶች ማንነታቸው ባልታ ወቁ ግለሰቦች ሐምሌ 8 ቀን 2001 ዓ.ም ምሽት በመንበረ ¬ትርያርክ ጽ/ቤት ግቢ በሚገኘው መኖሪያቸው የመደብደብ ሙከራ እንደደረሰባቸው ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል፣ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ገልጸዋል፡፡

እንደ ብፁዓን አባቶች ገለጻ ማግሥቱ ለመሰብሰብ እየተዘጋጁ፣ ጸሎት እያደረሱ ሳለ ሌሊት ማንነታ ቸው ያልታወቁ ሰዎች ቤታቸውን በኃይል በመደብደብ በር እንዲከፍቱ ላቸውና የሚያወያዩአቸው ነገር እንዳለ ሲገልጹላቸው ማንነታቸውን ስለማያውቁ እንደማይከፍቱ ምሽትም በመሆኑ ማንነታቸውን የማያውቋቸውን ሰዎች ለማነጋገር ፈቃደኛ እንዳልሆኑ በመግለጽ እንደመለሷቸው አስተያየታቸውን የሰጡን አባቶች አስረድተዋል፡፡

ዓላማቸው ያልተሳካላቸው ማንነታቸው ያልታወቁት ግለሰቦች ቅዱስ ¬ትርያርኩ ባልተገኙበት ወቅት ቅዱስ ሲኖዶሱን በሰብሳቢነት ይመሩ የነበሩትን የብፁዕ አቡነ ቄርሎስን በር ሰብረው በመግባት ጭምር ጉዳት ለማድረስ እንደሞከሩ ብፁዓን አባ ቶች ጠቁመው፤ የአንዳንዶቹን በር በኃይል በመምታትና በማስጠንቀቅ «ጠብቅ እናሳይሐለን» የሚሉ ዛቻዎች በመሰንዘር ያስፈራሩ እንደነበረም ገልጸዋል፡፡

ጉዳት ለማድረስ የመጡት ግለሰ ቦች በመጀመሪያ የብፁዓን አባቶችን በር ሲያንኳኩ «ፖሊሶች ነን ክፈቱ» ይሉ እንደነበርና የብፁዓን አባቶቹ ቤት የደበደቡበት ሰዓት ተመሳሳይ እንደነበር አስተያየት ከሰጡን አባቶች ለመረዳት ችለናል፡፡

ምዕመናን በተከሰተው ነገር ሳይደና ገጡ ሁሉን ማድረግ ወደሚችለው አምላክ ይጸልዩ ያሉት ብፁዓን አባ ቶች፤ መንግሥት ጉዳዩን በጥልቅና በትኩረት በመከታተል ጥበቃ እንዲ ያደርግና የቤተክርስቲያንን ችግር እንዲፈታ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በጠቅላይ ቤተክህነት የጥበቃ ሓላፊውን በአባቶች ላይ የደረሰውን የድበደባ ሙከራ አስመልክተን ያደረግነው ሙከራ አጥጋቢ ምላሽ ባለመገኘቱ አልተሳካም፡፡

በጉዳዩ ላይ ቤታቸው የተደበደበ ባቸውን የቅዱስ ሲኖዶስ አባላትና ቤተሰቦቻውን አነጋግረናል ከዚህ እን ደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡ ብፁዕ አቡነ ዮናስ የአፋር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናቸው፡፡ ብፁዕ ነታቸው ሌሊት በቅጽረ ቤተ ክህነት ስለተፈጠረው ጉዳይ ጠይቀናቸው ምላሻቸው የሚከተለው ነበር፡፡

ሐምሌ 8 ቀን የነበረው ስብሰባ በጣም ጥሩ ስብሰባ ነበር፡፡ የመንግሥት ባለ ሥልጣናት በተገኙበት እየተነጋገርን አንድ ሁለቱ ችግር ተቃሎ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የብፁዕ አቡነ ሳሙኤልን ጉዳይ ለማነጋገር እሳቸው ስላልነበሩ ነገ እሳቸው ባሉበት እንነጋገራለን፡፡ ብለን ነው በሰላም የወጣነው፡፡ ከዚያ በኋላ በሰላም ወደ ቤታችን ገባን፡፡

ሌሊት የአባቶች ቤት ተመቷል፤ የአቡነ ቄርሎስ ግን በጣም የበዛ ነበር መዝጊያውም ተሰብሯል፡፡ ይህን ዐይቻለሁ፤ በውስጡም በውጭውም «የ¬ሊስ ያለህ፣ የመንግሥት ያለህ» ድረሱልኝ በእንደዚህ ቁጥር ቤት ያለን እየተደበደብን ነው ብዬ ስጮህ ገለል ብለው ሔዱ፤ እንጂ ወደ መኝታ ቤቱ ሊገቡ ትንሽ ነበር የቀረው ብለው ነግረውኛል፡፡ በማለት የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡

ዲ/ን ተክለ ወልድ የብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ረዳት ነው፡፡ ጉዳዩን አስመልክቶ የሚለው አለ፡፡ «ዋናውን በር ገንጥለው ገብተዋል፡፡ ቀጥለው የመኝታ ክፍሉን በር ለመስበር ሲታገሉ ብፁዕ ነታቸው ውስጥ ሆነው ስልክ መደወላቸውን ሲሰሙ ትተው ሔዱ፡፡ ማዕድ ቤት ገብተው ያሉትን ዕቃዎች ሁሉ ፈትሸዋል፣ መሳቢያዎች ሁሉ ተከፋፍ ተው ተበርብረዋል፡፡ ብፁዕነታቸው አሁን ደህና ናቸው፡፡ አጋጣሚ አንዲት ነርስ እኅታችን ጤንነታቸውን እየተከተለች የሕክምና ርዳታ ታደርግላቸው ትከታተላቸው ስለነበር እሷ የሳሎኑ በር ሲሰበር መኝታ ቤቱን ቆልፋ ለሕይወታቸው መትረፍ ምክንያት እንደሆነችም ይገልጻል፡፡

የጉራጌ ከንባታና ሀዲያ እና ሲልጤ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ምን ይላሉ?

«ነገሩ ያሳዝናል ግን እግዚአብሔር ይመስገን ደህና ነን፡፡ ለሁሉም የኛ አለቃ፣ ንጉሥ፣ ባለሥልጣን፣ እግዚአብሔር ነው፡፡ ስለዚህ ለእግዚአብሔር ከመንገርና ከመስጠት ሌላ የምንለው የለም፡፡ የቤተ ክርስቲያን ሕግ ሕገ ቅዱስ ሲኖዶስ ይከበር ነው ያልነው፡፡ ሌላ ያልነው ነገር የለም፡፡

በአሁኑ ሰዓት በእውነቱ ቤተክርስቲያን የጠበቀችውን ያህል አልተጓዘችም ብለናል፡፡ አባቶችም ሲታገዱ በሲኖዶሱ ሕግ፣ ሲኖዶሱ ያግድ፣ ከሲኖዶሱ ጋር ይሥሩ፣ እንርዳዎት፣ እናገልግልዎት፣ እናግዝዎት ነው ያልነው እኛ ሌላ ነገር ያልነው ነገር የለም፡፡ እኛ በየሀገረ ስብከታችን እያገለገልን እየተሯሯጥን ነው፡፡
ባለሥልጣናት ባለፈው ዓርብ መጥተው የቅዱስ ሲኖዶስን፣ የቤተክርስቲያንን ቃለ አዋዲ አክብራችሁ፣ ተደማመጡ፣ ቤተክርስቲያኒቱ እንኳን ለራሷ ለአፍሪካም መሆን የም ችል ናት አሉን፡፡

ሕዝቡም ተበጥብጧል፣ ተጨንቋል እባካችሁ ሰላም አውርዱ፣ መንግሥት ሓላፊነት አለበት፡፡ አመራርና አካሔድ ልንነግራችሁ ነው የመጣነው፡፡ ከተበጣበጠ መንግሥት ጣልቃ ይገባል፣ ሓላፊነት አለበት፡፡ እናንተ አባቶች ናችሁ፤ የምትመክሩንና የምትረዱን እንጂ እኛ እናንተ ውስጥ ጣልቃ መግባት አንችልም፡፡ የራሳችሁን ችግር በራሳችሁ አክብሩ፤ የሐምሌ 5 ቀን በዓልን በሰላም አክብሩ፤ የራሳችሁ በዓል ነው ብለው ጥሩ መመሪያ ሰጡን ተወያዩ አሉን፡፡ እንደገና ተሰባሰብን ሐምሌ 7 ቀን ሰላም ይኖራል ብለን፡፡ ነገር ግን የባሰ ነበር ጉዳዩ፡፡

አሁን ደግሞ እየታየ ያለው ደስ የማይል ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን አምላክ ይፍረደን፤ እሱ እንደፈቀደ ይሁን፣ ቅዱስ አባታችንን ለመንቀፍ አይደለም፣ እሳቸውን ለማዋረድ አይደለም እናከብራቸዋለን፡፡ እኛ ያልነው ሕግ አክብረው ያስከብሩን፣ በሕግ ይምሩን ነው የምንለው፡፡

እኛ መሠረታችን እግዚአብሔር ነው፡፡ ጠባቂያችን እግዚአብሔር ነው፡፡ ቀጥሎ ደግሞ መንግሥት ነው፡፡ በመንግሥት ተስፋ አንቆርጥም፡፡ የማጣራት ሥራ ሠርቶ መግለጥ አለበት፡፡

ሁሉንም የሚያውቀው ጌታ እግዚአብሔር ነው፡፡ ለሁሉም ጽዋው ይሞላል፤ ዋጋውን ይከፍላልና ብዙ ችግሮች ደርሰዋል፣ እየደረሱም ናቸው፡፡ ግን አባቶች ለሞትም ቢሆን የተዘጋጀን ነን፡፡

የበር መስበር አይደለም፣ ማስፈራራት አይደለም ለቤተ ክርስቲያን ካስፈለገ እንሞታለን፤ የቀደሙትም ሞተውላታል፡፡ አሁንም ቢሆን አባቶች ወደ ኋላ አንልም፡፡ ቤተ ክርስቲያን ሁል ጊዜ በፈተና እየተፈተነች ነው ዘመናትን የተሻገረችው ከፈተና ወጥታ አታውቅም፡፡

አሁንም ቢሆን ሲኖዶሱ የተወያየው፣ እርሳቸው ስብሰባውን እንዲመሩ፣ አስተዳደራዊ ሥራውን ሌሎች እንዲሠሩ ሁልጊዜ የምንነጋገረው፣ ለመንግሥትም እያሳሰብን ያለነው ይሄን ነው፡፡

እሳቸው በአባትነታቸው፣ በሊቀ መንበርነታቸው ጉባኤውን ይምሩ፤ ሲኖዶሱ ግን በሲኖዶሱ ሕግ መሠረት ተወያይቶ ይወስን የሚል ሐሳብ ለብዙ ዓመታት ስናነሣ ቆይተናል፡፡ ስለልማት፣ ስለ ሃይማኖት ተጨቃጭቀን አናውቅም፡፡ አሁን ሰለቸን ብዙዎች አባቶች፣ ደከማቸው፤ በጣም ያሳዝናል፡፡

በዋናነት ኃይለኛ ክርክርና ጭቅጭቁ ሕገ ቤተ ክርስቲያን ይከበር ነው፡፡ መልካም አስተዳደር እንዲሰፍን ነው፣ በጀት በሥነ ሥርዓት እንዲመራ ነው፡፡ ሥራ አስፈጻሚውንም ቅዱስ ሲኖዶስ ሲመድበው ሥራ እንዲሠራ ነው፡፡ ኮሚቴው ቅዱስነትዎ በጥርጣሬ ሊያዩት አይገባም፡፡ ኮሚቴው እርስዎን የሚረዳና የሚያግዝ ነው ያልነው፡፡

በቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ላይ በአብዛኛው አባቶች አንድን ዓይነት መንፈስ ነበራቸው፡፡ የሃሳብ ግጭቶች ይኖራሉ፣ እያንዳንዱ የራሱ የሆነ አመለካከት ይኖረዋል ግን በአብዛኛው ሲኖዶሱ ደግሞ አንድ ዐይነት መንፈስ የሚታይበት ነው፡፡

በመጨረሻ የማስተላልፈው ቤተ ክርስቲያን በመርከብ ትመሰላለች፡፡ በባሕር ላይ ያለች መርከብ አውሎ ንፋስ ሊያንገላታት ይችላል፡፡ ስለዚህ ሐዋርያትን እናስታውስ፡፡ አውሎ ንፋስ የተሳፈሩበትን መርከብ ሲያናውጠው ክርስቶስም አብሮ ነበር፡፡ ክርስቶስ ያለባት መርከብ ዐውሎ እንደተነሣባት ነው፤ ሁሉም ሐዋርያት «አድነን» ነው ያሉት፤ ወደ እሱ ነው የጮሁት መጨረሻ ላይ ነፋሱን የገሰጸው እሱ ነው፡፡ አሁንም የቤተ ክር ስቲያን አምላክ ይህንን ማዕበል ፀጥ ያደርገዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ ጾም ጸሎት ያስፈልጋልና፡፡ ምእመናን ወደ እግዚ አብሔር እንዲጮሁ ነው የማሳስበው፡፡ በዚህ ምክንያት እንዳይሸማቀቁ እንዳ ይደናገጡ ሃይማኖታቸውን ብቻ ይጠብቁ፡፡ በማለት አባታዊ ጥሪያቸውን በእንባም ጭምር አስተላልፈዋል፡፡

አቡነ ፋኑኤል የሲዳማ፣ የጌድዮ፣ የአማሮ፣ የቡርጂ ዞኖችና ልዩ ወረዳ ዎች አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናቸው፡፡ ጥቃት ባይደርስባቸውም ሙከራ ተደርጎባቸው እንደ ነበር ሰማንና የደረሰባቸውን እንዲያብራሩልን ጠየቅናቸው ቃላቸውን እነሆ «እኔ ዘንድ የተፈጠረው ችግር ሐምሌ 9 ቀን ከምሽቱ 4፡30 ላይ ነው፡፡ ማንነታቸውን የማላውቅ ሰዎች ወደ መኖሪያዬ በመኪና መጡ፡፡ በኃይል የቤቴን መዝጊያ ደበደቡ፡፡ ጠባቂዎችን ተጠንቀቁ፤ በር አትክፈቱ አልኩ በዚያ ሰዓት እንግዳ እንደማይመጣ አውቃለሁ፡፡

ውጭም ያሉ ልጆችም በመስኮት አንኳኩተው ምንድን ነው አሉኝ፤ ዝም በሉ አልኳቸው፡፡ በጣም አንኳኩ በጣም ጠንከር አለ፡፡ በዚህ መሐከል ለቤተ ሰብና ለፖሊስ እንዲደወል አደረግሁ፡፡ 10 ደቂቃ ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ ተመልሰው በመኪናቸው ሄዱ ወዲያው ቤተሰብም ፖሊስም መጣ፡፡ ነዕለታዊ ሪፖርት ፖሊስ ጣቢያ ሄጄ አስመዘገብኩ፡፡

ድርጊቱ የተፈጸመው እኔ ላይ ብቻ መስሎኝ ነበር፣ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሌሊት ስደውል እዚያም የባሰ እንደነበር ሰማሁ፡፡ እኔ የምኖረው ቃሊቲ ገብርኤል አካባቢ ነው፡፡ ይህ ሁሉ የመጣው በቅዱስ ሲኖዶሱ ሽኩቻ ነው፡፡

መቼም እኛ ሌላ ተቃዋሚ ወይም ጠላት የለንም፡፡ ምን ተፈልጐ ለምን እንደተፈጸመ አይገባኝም፡፡ በወቅቱ ስብሰባው የተካሄደው ለግማሽ ቀን ነው፡፡ ለሥራ አስፈጻሚ ተብሎ የተመረጠው ኮሚቴ እገዳው ተነሥቶለታል፡፡ ሌላው የብፁዕ አቡነ ሳሙኤል ጉዳይ ነው እሱን ነገ እናየዋለን ነበር ያልነው፡፡ ስብሰባ ውም ቁጣ የተሞላበት አልነበረም፡፡ የተረጋጋና በሰከነ መንፈስ የተካሄደ ነበር፡፡ በማለት ጥቃቱ በተፈጸመበት ዋዜማም ቢሆን ለዚህ ድርጊት የሚያ ነሣሣ ምንም ዓይነት ምክንያት እንዳ ልነበር ገልጸዋል፡፡

ሕገ ሲኖዶስን አስመልክተው በርግጥ ቅዱስነታቸው ተቀባይነት የሌለው ሐሳብ አቅርበው ነበር፡፡ መሻሻል አለበት፣ ብዙ ነገር ጐድሎታል ይሉም ነበር ምን እንደሚጨምሩ፣ የትኛው አንቀጽ እንደሆነ የሚሻሻለው ባይገልጹም በድፍኑ ግን ቅሬታ እንዳላቸው ይገልጹ ነበር፡፡

በስብሰባው ወደ 6 አጀንዳ ቀርቧል እስካሁን የታየው ገና አንዷ ብቻ ነው፡፡ አሁን የተፈለገው ጠቅላላ ነገሮቹ እንዳይታዩ ሊሆን ይችላል ብዬ እገምታለሁ፡፡

በመጨረሻ የማስተላልፈው መልእክት ይሄ ፈተና ነው፤ በእኛ ላይ የመጣ ማዕበል ፈተና ነው ሁሉም በሃይማኖቱ ጸንቶ ቤተ ክርስቲያኒቱንም እኛንም ያስበን ሁላችንም በያለንበት እንጸልይ በሃይማኖት እንጽና ነው የምለው፡፡ እኛ ሁል ጊዜ ሕይወታችን ከወንጌል አገልግሎት ጋር የተያያዘ ነው፡፡ አሁንም የምናደርገው ይህንኑ ነው፡፡ ቀጣዩም ሕይወታችን በወንጌል ማገልገል ነው፡፡

የቤተ ክርስቲያንን አስተዳደራዊ ጉዳይ በተመለከተ ለውጥ ያስፈልጋል፡፡ ለውጥም ስለሚያስፈልግ ነው ይሄ ሁሉ የተከሰተው፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን በሁለንተናዋ በልማቱም በወንጌል አገልግሎቱም ወደኋላ ቀርተናል ማለት ይቻላል፡፡

የቤተ ክርስቲያናችን ችግር ከኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰወረ አይደለም፡፡ አሁን በሲኖዶስ ደረጃ ጐልቶ ወጣ፤ እንጂ ሕዝብ ተነጋግሮበት ያበቃለት ጉዳይ ነው፡፡ ስለዚህ ሁላችንም በሃይማኖት በጸሎት ጸንተን መኖር ይገባ ናል፡፡ በተፈጠረው ሁኔታም ሳንደናገጥ ሳንሸበር ባለንበት ጸንተን የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕልውና የሚቀጥልበትን መንገድ ማሰብ ያስፈልገናል በማለት መልእክታቸውን ያጠቃልላሉ፡፡

ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የቅዱስ ሲኖዶስ ጸሐፊና የዋግ ህምራ ሊቀ ጳጳስ ስለጉዳዩ በጥልቅ ሐዘን ይናገራሉ፡፡ይህ ነገር ይበጃል) ምእመኑ በጭን ቀት ላይ ነው ያለው የኛን ድምፅ መስማት ይፈልጋል፡፡ እኔ በሁኔታው ተረብሼ ሳልተኛ ነው ያደርኩት በቃ አሞኛል፡፡ አሁን ይህን የማስብበት የተረጋጋ አእምሮ የለኝም፤ ብለዋል፡፡
የቦረናና ጉጂ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስም ከዛቻና ስድብ ባያልፍም የጥቃቱ ሰለባ ነበሩና የሚናገሩት አላቸው፡፡«እግዚአብሔር በቸርነቱ በደላችንን ሳይመለከት አትርፎናል፡፡ ቤታችን በምሽት ባልታወቁ ግለሰቦች ተደበደበ በግምት ከምሽቱ አራት ሰዓት አካባቢ ይሆናል፡፡ የመጡት ሰዎች በሩን በኃይል ደበደቡ ክፈት አሉኝ፡፡ አልከፍትም አልኳቸው «አይ ልናማክሮት ነው አንዳንድ ነገሮችን ልናዋዮት ነው በሩን ክፈቱ አሉኝ» ሰዓቱ አልፏል እኔ አልከፍትም አልኳቸው «¬ሊሶች ነን» አሉኝ ፖሊሶችም ብትሆኑ በዚህ ሰዓት ሕጉ አይደለም፤ የሰውን በር ማስከፈት ስለዚህ አልከፍትም አልኳቸው፡፡ ክፈት እያሉ በሩን በኃይል መደብደብ ጀመሩ፡፡ እኔም በውሳኔዬ ጸናሁ፤ እነሱም ድብደባውን አጠነከሩ፣ በኋላ የውስጥ በር ዘግቼ ስልክ ወደ ፖሊስና ቤተሰብ ደወልኩ፡፡ ከዛም በኋላ ብዙ ሰዓት ይሆናል በሩን የቀጠቀጡት እኔ እንደውም ሰብረው የገቡ መስለውኝ ነበር፡፡ ሌላ ክፍል ውስጥ ቆልፌ ተቀምጬ ሳለ እግዚአብሔር መለሳቸው፡፡ የሔዱ ሲመስለኝ ቀጥሎ የሌላ አባት ቤት ሲደበደብ ሰማሁኝ፤ የማንን ቤት ነው የደበደቡት እያልኩ ነበር፡፡

ከኔ ቤት ቀጥሎ ያለውን ቢመስለ ኝም የሳቸው ቤት አልተነካም፣ ነገር ግን ብዙ ቤት ነው የተደበደበው በአጠቃላይ የጳጳሳቱ ቤት ነው የተደበደበው ግን እኛ በቸርነቱ ተርፈናል፡፡

ምክንያት ይሆናል የምለው ምናልባት በሲኖዶስ ስብሰባ ላይ በሰጠነው ሐሳብ ይሆናል ብዬ አስባለሁ፡፡ እንግዲህ ከዚህ ሌላ ምን ሊሆን ይችላል ሌላ የተጣላነው ሰው የለንም ያው መነሻው በስብሰባው ላይ ሕገ ሲኖዶስ ይከበር ማለታችን ይመስለኛል፡፡

የቤተ ክህነት ግቢ ጥበቃ አለው፡፡ ድርጊቱ ሲፈጸም ለዘበኞች ደወልኩ እንመጣለን ይላሉ እንጂ አንዳች እርዳታ አላገኘሁም፡፡ ለወደፊቱ መንግሥት ጥበቃ ካላደረገልን እንግዲህ ለሕይወታችን በጣም የሚያሰጋ ጉዳይ ነው፡፡ ብዙ ጥረው መጨረሻ ሳይሳካ በመቅረቱ ነው እየተሳደቡ የሔዱት፡፡ ታገኛታለህ ቆይ እያሉ ነው ሲዝቱብኝ የነበረው፡፡

ማንም የደረሰልን የለም፣ እግዚአብሔር ግን ረድቶናል፡፡ ፖሊሱ መጣ ተባለ ነገር ግን ወደ ውስጥ መግባት የቻለ አይመስለኝም፤ መብራትም አልነበረም፡፡ በወቅቱ ያው ጨለማን ተገን አድርገው ነው፤ ለድብደባ የተሰማሩት አጥቂዎቹ፤ እንግዲህ የነገን ባናውቅም ለአሁን ተርፈናል፡፡

እኛ ለእግዚአብሔር አመልክተናል፡፡ መንግሥትም ጥበቃ እንዲያደርግልን ነው ጥሪያችንን አቅርበናል፡፡ ይህ ችግር በስብሰባው ላይ በተፈጠረ ያለመግባባት የመጣ ነው፡፡ ምክንያቱም በአቋማችን በጸናነው አባቶች ላይ ብቻ ተለይቶ ነው ድብደባው የተፈጸመው፡፡ ቤተ ክርስቲያኗ ትከበር፣ አስተዳደሯ ይከበር፣ ሙስና ይጥፋ ሁሉም ነገር በቤተ ክርስቲያን ሕግ ይሁን በማለታችን ዛቻና የበር ድብደባ ተፈጽሞብናል፡፡

የትናንት /ሐምሌ 8 ቀን 2001 ዓ.ም/ የስብሰባ ውሏ ችን የሰባቱን ሊቃነ ጳጳሳት እግድን ስለማንሣት ነበር የተወያየነው፡፡ ከዛ በኋላ በሌላ አጀንዳ ለዛሬ /ለሐምሌ 9/ ልነነጋገርና የመንግሥት አካላት እንዲገኙ ልን ተነጋግረን ነው የተለያየነው፡፡
የቤተ ክርስቲያን መዋቅርና አስተዳደራዊ መሠረቷ ሕገ ሲኖዶስ ነው፡፡

ያባቶች ሐሳብ አንድ ነው፡፡ ሁኔታዎች ላይ መስማማት እንጂ የመለያየት ነገር የለም፤ የሁሉም ዓላማና ራእይ አንድ ነው፡፡ ሐሳባቸው ዓላማቸው አስተዳደር ይስተካከል ሕገ ቤተ ክርስ ቲያኑ ይከበር ነው የተለያየ አይደለም፡፡ በመሠረታዊ ጉዳዩ የሁሉም አባቶች አቋም አንድ ዓይነት ነው፡፡ ለምሳሌ ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ቤት እንደገናም በ¬ትርያርኩ መሪነት የተሰበሰቡ አሉ ይባላል፡፡ እንግዲህ ¬ትርያርኩም ጋር ሄደው ቢሰበሰቡ ሐሳባቸው አንድ ነው፡፡ እርስዎ ፊት የተወያየነውን ነገር በሲኖዶሱ ፊት እንስማማበታለን /እንፈራረምበታለን/ ነው ያሉት እንጂ በሐሳብ መከፋፈል የለም፡፡

በተፈጠረው ነገር ምእመናን እን ደተረበሹ እናውቃለን፡፡ ምእመናን የተበላሸ ነገር በአንዴ ሊስተካከል አይችልም፤ ያለ እምነት ውጤት አይ ገኝምና አሁንም በትዕግሥት እግዚኦታቸውን ይቀጥሉ፡፡ ምእመናንን የሚረብሽ ነገር የለም፡፡ ሁሉም ምእ መን በጸሎት ሆኖ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን ከፈተና እንዲታደ ጋት በጸሎት እንዲጠይቅ ነው፡፡ በጸሎት እንዲያስቡን ያስፈልጋል፡፡ እግዚአብሔርን በጸሎታቸው እንዲ ጠይቁልን ነው የሚያስፈልገው፡፡» በማለት ነበር ስለሁኔታው የገለጹት፡፡
ጥቃቱን የፈጸመው ቡድን ሆን ብሎ ብፁዓን አበውን የሚያሳድድ በመሆኑ ለብፁዓን አበው ጥበቃ እንዲ ደረግላቸውና ወንጀለኞቹም ለፍርድ እንዲቀርቡ ምእመናን እየጠየቁ ነው፡፡
ብፁዓን አበው ምእመናን በጾምና በጸሎት እንዲተጉ ደጋግመው የጠየቁት ሲሆን በሃይማኖት ጸንተው የእግዚአብሔርን ፍርድ እንዲጠጣበቁ አሳስበዋል፡፡

 
 
 

ወስብሐት ለእግዚአብሔር