sami.02.07

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በጸሎተ ምኅላ ተጀመረ

ጥቅምት 11 ቀን 2007ዓ.ም.

መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

በዓመት ሁለት ጊዜ የሚደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ዛሬ ጥቅምት 11ቀን 2007ዓ.ም. ከቀኑ ዐሥር ሰዓት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በጸሎተ ምኅላ ተጀመረ፡፡

 

       sami.02.07

የጥቅምት 2007 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ  ከጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ የሚካሔድ ሲሆን በዚህ ጉበኤ ሐዋርያት  እኛና መንፈስ ቅዱስ   ወስነናል እያሉ ለቤተክርስቲያን የሚጠቅም ውሳኔ ይወስኑ እንደነበር፤ የሐዋርያት አምላክና መምህር ኢየሱስ ክርስቶስ ረድቷቸው፣ በርደተ መንፈስ ቅዱስ ወቅት   ከሐዋርያት ያልተለየች እመቤታችን  ሳትለያቸው  ለቤተ ክርስቲያን የሚጠቅም ውሳኔዎችን ያስተላልፋሉ ብለን እንጠብቃለን፡፡