የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ቃጠሎ መንሥኤ እየተጣራ ነው

ሐምሌ ቀን ፳፻፰ .

በዲያቆን ተመስገን ዘገየ

shema mareyam church

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት በስማዳ ወረዳ ቤተ ክህነት ሽሜ አዝማቾ ቀበሌ በምትገኘው በሽሜ ማርያም ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰው የእሳት ቃጠሎ መንሥኤ በወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት እየተጣራ እንደሚገኝ የወረዳ ቤተ ክህነቱ ሊቀ ካህን ቄስ ሞላ ጌጡ ተናገሩ፡፡

በቃጠሎው በሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ፣ በጥንታውያን የብራና መጻሕፍት፣ በመስቀሎች፣ በአልባሳትና በሌሎችም ንዋያተ ቅድሳት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን የወረዳ ቤተ ክህነቱ ሊቀ ካህን አስታውቀዋል፡፡

የቀበሌው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሲሳይ በየነ እንደ ተናገሩት የአካባቢው ሕዝበ ክርስቲያን እሳቱን ለማጥፋት ከፍተኛ ጥረት ቢያደርግም የእሳት ቃጠሎው የደረሰው በሌሊት በመኾኑ አዳጋውን ለመቀነስ የተደረገው ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

ሰኔ ፯ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም መንሥኤው ባልታወቀ ምክንያት በሽሜ ማርያም ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ላይ የእሳት ቃጠሎ አደጋ መድረሱ ይታወሳል፡፡ የቃጠሎው መንሥኤም በወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት እየተጣራ ይገኛል፡፡