megelecha

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጠ

መስከረም 12 ቀን 2005 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በቤተ ክርስቲያኒቱ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መስከረም 11 ቀን 2004 ዓ. ም. መግለጫ ሰጠ፡፡ መግለጫውን የሰጡት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሓላፊ የሆኑት እስክንድር ገብረ ክርስቶስ ሲሆኑ በመግለጫቸውም “በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥና ዙሪያ ተሸሽገው የተዛባ መረጃን በማቀበል የሽግግር ወቅት ሂደቱን ሰላማዊ በሆነ መልኩ እንዳይራመድ የሚጥሩ ወገኖች ሁሉ ከዚህ አፍራሽ እንቅስቃሴያቸው እንዲታቀቡ እያሳሰብን ይህ ባይሆን ግን የሽግግር ሂደቱን ሰላማዊ ለማድረግ ሲባል ቤተ ክርስቲያኒቱ ሕጋዊ እርምጃዎቸን ለመውስድ የምትገደድ መሆኑን አጥብቃ ለማሳሰብ ትወዳለች፡፡” ብለዋል፡፡

 

6ኛውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ምርጫን በሚመለከት ጥቅምት በሚካሔደው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የሚወሰን መሆኑንና ሕዘበ ክርስቲያኑ የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔና የቤተ ክርስቲኒቱን ድምጽ ብቻ መከታታል እንደሚገባው በመግለጫቸው አመልክተዋል፡፡

 

በተያያዘ ዜና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ክቡር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በጠቅላይ ሚኒስትርነት፤ ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት  መመረጣቸውን በማስመልከት ለኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት መልእክት ማስተላለፏን ከሕዝብ ግንኙነት መምሪያው የወጣው መረጃ ያመለክታል፡፡

 

megelecha