meg 28 2006 01

ቅዱስ ፓትርያርኩ ጾመ ፍለሰታን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ

 ሐምሌ 28 ቀን 2006 ዓ.ም.

ዲ/ን ፍቃዱ ዓለሙ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት በየዓመቱ ከነሐሴ 1 እስከ 16 የሚጾመው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ጾም ዘንድሮም የፊታችን ሐሙስ ይጀምራል፡፡

meg 28 2006 01 ይህን አስመልክቶ በቅዱስ ፓትርያርኩ ልዩ ጽሕፈት ቤት በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅትብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ “የቅድስት ድንግል ማርያምን በዓለ ትንሣኤ ምክንያት አድርገን የምንጾመው ይህ ጾም ለሀገራችን፤ ለሕዝባችንና ለዓለሙ ሁሉ መዳንን፤ ምሕረትንና ይቅርታን ለማስገኘት ነው” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ቅዱስነታቸው፣ በጾሙ ወቅት ሁሉም ክርስቲያን የተራቡትን በማጉረስ፣ የታረዙትን በማልበስና የተቸገሩትን በመርዳት ጾሙን ለመጾም ከወዲሁ ቅድመ ዝግጅት ማድረግ እደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊትና ጥንታዊት እንደመሆኗ መጠን ከጥንት ጀምሮ ይህንን ክብረ ቅድስት ድንግል ማርያም ጠብቃ እስካሁን አቆይታለች፤ ለወደፊትም እስከ ዕለተ ምጽአት በዚሁ ትቀጥላለች ብለዋል፡፡ ጾመ ፍልሰታ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያን በአዋጅ ከሚጾሙ ሰባቱ አጽዋማት መካከል አንዱ ሲሆን ከሕጻናት ጀምሮ ሁሉም ሕዝበ ክርስቲያን በፍጹም ትጋት የሚጾሙት የበረከት ጾም ነው፡፡