• እንኳን በደኅና መጡ !

 “ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና ለወልደ ዳዊት…” (ቅዱስ ያሬድ)

በቀሲስ ኃይለሚካኤል ብርሃኑ ሆሣዕና  በዕብራይስጥ  ሆሼዕናህ የሚል ሲሆን  ትርጒሙም “አቤቱ አሁን አድን” ማለት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት ዐቢይ ጾም ስምንት ሳምንታ አሉት፡፡ ሳምንታቱም የየራሳቸው ስያሜ አላቸው፡፡ ለማስታወስ ይረዳን ዘንድ ስንቃኛቸውም የመጀመሪያው ሳምንት ዘወረደ፣ ሁለተኛው ሳምንት ቅድስት፣ ሦስተኛው ሳምንት ምኲራብ፣ አራተኛው ሳምንት መጻጉዕ፣ አምስተኛው ሳምንት ደብረ ዘይት፣ ስድስተኛው ሳምንት ገብር ኄር፣ ሰባተኛው […]

“…ኒቆዲሞስ የተባለ አንድ ሰው ነበረ ”(ዮሐ.፫፥፩)

 በቀሲስ ኃይለሚካኤል ብርሃኑ የዐቢይ ጾም ሰባተኛው ሳምንት ኒቆዲሞስ ይባላል፡፡ ይህም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሌሊት ወደ እርሱ እየመጣ ይማር ለነበረው  ኒቆዲሞስ ለተባለ ፈሪሳዊ ሰው የዳግም ልደትን ምሥጢር (ምሥጢረ ጥምቀትን) ያስተማረበት በመሆኑ ኒቆዲሞስ ተብሏል፡፡ ኒቆዲሞስ በሕይወት ዘመኑ ቅንናና መልካም ሰው እንደነበር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በቀን ለመገናኘት ሁኔታው ባይፈቅድለትም በሌሊት እየመጣ የሕይወት ቃል በመማር ያልገባውንም በመጠየቅ ያሳየው […]

የኒቆዲሞስ መንፈሳዊ ዕድገት

ኤልያስ ገ/ሥላሴ አሐቲ፣ ቅድስት፣ ኵላዊት እና ሐዋርያዊት የሆነችው ቤተክርስቲያናችን እኛ ምእመኖቿ በዓለም ሐሳብ ድል እንዳንነሣ፣ ይልቅስ ፍትወታትን ሁሉ ድል አድርገን ራሳችንን ገዝተን (ተቈጣጥረን) በውስጣችን ፈቃደ እግዚአብሔርን አንግሠን ምድራዊውን ሳይሆን ሰማያዊውን እያሰብን እንድንኖር በዓመቱ ውስጥ በተለያዩ ወራት የሚጾሙ አጽዋማትን ሠርታልናለች፡፡ ከነዚህ አጽዋማት ውስጥ አንዱና ዋነኛው ደግሞ አሁን በዚህ ወቅት እየጾምነው ያለነው ዐቢይ ጾም ነው፡፡ ዐቢይ ጾም […]

ማስታወቂያ

Nothing Found

Sorry, no posts matched your criteria

መልእክትዎን ይላኩልን