መናፍቃን የሚስቱባቸውና የሚያስቱባቸው መንገዶች (ክፍል አንድ)

ዳዊት አብርሃም

ነገረ ድኅነትን (የመዳን ትምህርትን) በተሳሳተ መንገድ የሚያስቡና ስሕተት የሆነን ትምህርት ከማስተማር አልፈው ትክክል የሆነውን የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ የሚቃወሙ ወገኖች እዚህ አቋም ላይ ሊደርሡ የቻሉበት በርካታ ምክንያቶች ቢኖሩም ከብዙዎቹ ምክንያቶች መካከል ጥቂቶቹን በመለየት ቀለል ያለውን መንገድ መርጠን ለማየት እንሞክራለን፡፡ የስሕተቶቹ መነሻ በመጠኑ ሲዳሰስ የሚከተለውን ይመስላል፡፡

  1. በአንዲት ነጠላ ጥቅስ ላይ መመሥረት

 

በማንኛውም የትምህርት መስክ አንድ አቋም ላይ ለመድረስ በቂ የሆነ መረጃ መያዝ እንደሚያስፈልግ የጥናትና ምርምር ሕግ ግድ ይላል፡፡ ዓለማዊ ወይም ምድራዊ ነገር ይህን ያህል ጥንቃቄ የሚያስፈልገው ከሆነ ሰማያዊው የነገረ መለኮት ዕውቀት ደግሞ የቱን ያህል ጥንቃቄ፣ የቱንስ ያህል ትዕግሥት ይሻ ይሆን? በተለይ የሰው ልጆችን ዘለዓለማዊ ሕይወትና ዘለዓለማዊ ጥፋት በቀላሉና በችኮላ፣ በተወሰኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ላይ ብቻ በመመሥረት ለማወቅና እውነቱ ይህ ብቻ ነው ብሎ ለመደምደም መሞከር ከባድ ስሕተት ላይ መጣሉ አይቀርም፡፡ ብዙዎቹ መናፍቃን ግን በጥቂት ጥቅሶች ላይ ከመመሥረት አልፈው በሁለትና በሦስት ጥቅሶች ላይ ብቻ ተመሥርተው ይደመድማሉ፡፡ ይህ ብቻ አይደለም፤ በጣም በሚገርም ኹኔታ በአንዲት ነጠላ ጥቅስ ላይ ብቻ ተመሥርተው ትልቅ ነገር መለኮታዊ ግንብ ለመገንባት ይጥራሉ፤ ወይም የተገነባውን ታላቅ ግንብ ለመናድ ይሞክራሉ፡፡ አንዳንዶች አንዲትን ቃል መዘው በመያዝ መዳን በጌታ ነው ሲሉ ይደመጣሉ፤ ቀጥለውም ቅዱሳን ለመዳን ምንም ሚና ሊኖራቸው አይገባም በማለት ይደመድማሉ፡፡

Read more

ማዘንና መጸለይ (ከባለፈው የቀጠለ)

በዲ/ን ታደለ ሲሳይ

  1. የቤተ ክርስቲያን ሰላም በጠፋ ጊዜ

ክርስቶስ በደሙ ዋጅቶ የመሠረታት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለድኅነታችን መንገድ፣ ለህልውናችን ዋስትና፣ ለሰማያዊ ቤታችን ደግሞ ተስፋ ናት፡፡ ይህንን መንገድ፣ ዋስትናና ተስፋ የምናገኘውና ተጠቃሚም የምንሆነው የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰላም ሲጠበቅ፣ መንጋዎቿ ፈጣሪያቸው በፈቀደላቸው መስክ ብቻ መሠማራት ሲችሉ፣ እረኞቹ ከመንጋው ባለቤት ከኢየሱስ ክርሰቶስ የተቀበሏቸውን በጎች ከቀበሮና ከሌሎች አውሬዎች መጠበቅ ሲችሉ ነው፡፡ ይህ የሚሆነው ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ሰላም ተጠብቆ ሲቀጥል ብቻ ነው፡፡

Read more

ማዘንና መጸለይ

በዲ/ን ታደለ ሲሳይ

የሰው ልጅ በመጀመሪያ ሲፈጠር ዓለምን ከፈጣሪ በታች እየመራ፣ ፍጡራን ሁሉ ይገዙለት ዘንድ ነበር፡፡ አዳም በተፈጠረ ጊዜም ጣርና ሐዘን፣ መከራና ስቃይ አልነበረበትም፤ ይልቁንም በድሎትና በደስታ ይኖር ነበር እንጂ፡፡ ይሁን እንጂ አድርግ የተባለውን ብቻ ማድረግ ሲኖርበት አትብላ የተባለውን ዕፀ በለስ በመብላቱ የሞት ሞት አገኘው፡፡ አዳምና ሔዋን ስቃይና እንግልት፣ ፈተና፣ ሐዘንና መከራ ደረሰባቸው፡፡ ከዚያ በኋላ ያለው የሰው ልጅ ኑሮው በችግርና በድሎት፣ በስደትና በመረጋጋት፣ በሐዘንና በደስታ፣ በማሸነፍና በመሸነፍ፣ በመርታትና በመረታት መካከል ሆነ፡፡ የሰው ልጅ ሕይወትም መውደቅና መነሣት፣ ማግኘትና ማጣት፣ መከፋትና መደሰት፣ ማዘንና መረጋጋት ልማዱ ሆነ፡፡

Read more

በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን (ገላ. 5÷1)

በዲ/ን ታደለ ፈንታው

በኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያናዊ አስተምህሮ ያሉት ምርጫ ሁለት ናቸው፡፡ እነርሱም የቅዱስ ጋብቻ ሕይወትና የምንኩስና ሕይወት ነው፡፡ የቅዱስ ጋብቻ ሕይወት ደግሞ የእጮኝነት ጊዜያት አሉት፡፡ አንድ ወደ ጋብቻ ለመምጣት የወሰነ ወይም የወሰነች ወጣት ሦስት ነገሮችን እንዲያሟላ (እንድታሟላ) ይመከራል፡፡ እነዚህም

  1. መንፈሳዊ ብስለት

መንፈሳዊ ብስለት እንዲህ ከሚለው የእግዚአብሔር ቃል ጋር ይስማማል፡ ፡ “ጎበዞች ሆይ ክፉውን አሸንፋችኋልና እጽፍላችኋለሁ” (1ዮሐ.2፥13) ተብሎ ስለተጻፈ ክፉ የሆነውን ወይም ኀጢአት የሆነውን ነገር ጽድቅ ከሆነው ለይቶ ማወቅ፣ ክፋት፣ ማስወገድና መልካም በሆነው በጽድቅ መንገድ መመላለስ ነው፡፡

Read more

በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን (ገላ. 5÷1)

በዲ/ን ታደለ ፈንታው

ይህ መልእክት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች በጻፈው መልእክቱ በምዕራፍ አምስት ቁጥር አንድ ላይ የተቀመጠ ኀይለ ቃል ነው፡፡ የገላትያ ሰዎች አስቀድመው እግዚአብሔርን ያወቁ፣ ክፉ ከሆነው ከዚህ ዓለም የሥጋ ዐሳብ ያመለጡ፣ በሃይማኖት የሚኖሩ፣ ከክፋት የራቁ፣ መልካም የሆነውን ነገር ፈትነው የተቀበሉ፣ ለማፍረስ ያይደለ ለማነጽ የተጠሩ፣ ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ ደፋ ቀና የሚሉ፣ ሌትና ቀን በቤተ መቅደሱ በጸሎት ሁሉ የሚተጉ ክርስቲያኖች ነበሩ፡፡ አስቀድመው በተጠሩበት መጠራት መመላለስ ሲያቅታቸው ከመንፈሳዊው ነገር ይልቅ ትኩረታቸው ጉጉታቸውና አላማቸው ሥጋዊ ነገር ላይ ሲያርፍ ትውክልታቸው እግዚአብሔር መሆኑ ቀርቶ ምድራዊ ነገር ሲሆን የሚፈሩት ነፍስንና ሥጋን አንድ አድርጎ በገሀነም የሚቀጣውን እግዚአብሔርን ሳይሆን ጊዜ የሰጣቸውን ወገኖች ሆኖ ቢያገኛቸው እንዲህ የሚል መልእክት ጻፈላቸው፡፡ ‹‹በክርስቶስ እናንተን ከጠራች ከእርሱ ወደልዩ ወንጌል እንዲህ ፈጥናችሁ እንዳለፋችሁ እደነቃለሁ እርሱ  ግን ሌላ አይደለም የሚያናውጧችሁ የክርስቶስን ወንጌል ሊያጣምሙ የሚወዱ አንዳንድ ወገኖች አሉ እንጂ›› (ገላ.1፥6) በማለት ይጽፍላቸዋል፡፡ ክርስቲያኖችን ሁል ጊዜ በሚያባብል ቃል መቅረብ አስፈላጊ አይደለም፡፡ Read more

ጠንካራ ማንነት

…በዳዊት አብርሃም…

በዓለም ስትኖር ብዙ ሓላፊነቶችን ለመወጣት አለብህ። በዓለም መኖር ዓለማዊ መሆን አይደለም። ከኀጢአት ርቆ ዓላማን በማሳካት ምድራዊና መንፈሳዊ ሕይወትን አስተባብሮ መኖር ነው እንጂ። አንድ ሰው ጠንካራ ማንነትን ገንብቷል የሚባለው ምድራዊውንና ሰማያዊውን ዓለም አስታርቆ መኖር ሲችል ነው። በመሆኑም ጠንካራ ማንነትን ለመገንባት የሚከተሉትን አድርግ።

Read more

ከእግዚብሔር ጋር መሆን

…በዳዊት አብርሃም…

አንድ ክርስቲያን ከሁሉ አስቀድሞ ከእግዚአብሔር ጋር ለመሆን ማቀድ ይኖርበታል፡፡ ይህም የተሳካ መንፈሳዊ ሕይወት እንዲኖረው ያስችለዋል፡፡ የተሳካ መንፈሳዊ ሕይወት ደግሞ ለስኬታማ ምድራዊ ሕይወት መሠረት ነው፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን ነጥቦች በመመልከት ለመተግበር መጣር ያስፈልጋል፡፡

  1. ጸሎት

“ወደፈተና እንዳትገቡ ተግታችሁ ጸልዩ፡፡” ተብለን በተመከርነው መሠረት በግል፣ በቤተሰብና በማኅበር በያንዳንዷ ሥራችን መጀመሪያና መጨረሻ እንዲሁም በማዕድ ስንቀመጥ ልንጸልይ ይገባል፡፡ ጸሎት ከእግዚአብሔርም ጋር የምንሆንበት ዋነኛው መንገድ ነው፡፡ እግዚብሔርም ከእኛ ጋር የሚንሆንበት ዋነኛው መንገድ ነው፡፡ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ደግሞ ሁሉም ነገር ይከናወንልናልና፡፡ ሌላው ቀርቶ እግዚአብሔር ከርሱ ጋር መሆኑን ማሳብና ማመን የቻለ ሰው ይህን በማሰቡ ብቻ ከፍርሐት ነፃ ይሆናል፡፡ ሰላማዊ መንፈስም ይኖረዋል፡፡

Read more

ስኬት

…በዳዊት አብርሃም…

“ስኬት” የሚለውን ቃል የማይወድ ሰው ያለ አይመስልም:: በተለይ ራእይ ያላቸው ወጣቶች ስኬታማ መሆንን አጥብቀው ስለሚፈልጉ ብዙ ይጨነቃሉ፡፡ ወደ ስኬት የሚያመሩ መንገዶችን ይጠቁማሉ የተባሉ መጻሕፍትን ያነባሉ፡፡ ብዙ ጊዜም ታላላቆችንና ባለሙያዎችን ስለዚሁ ጉዳይ ምክር ይጠይቃሉ፡፡ እርስ በርስ ይወያያሉ፡፡ ብቻቸውን ሲሆኑም ከራሳቸው ጋር የሚመክሩት ጉዳይ ቢኖር እንዴት ስኬታማ መሆን እንደሚችሉ ነው፡፡ በርግጥ ስኬት ለማንኛውም ሰው ወሳኝ መሆኑ ግልጽ ስለሆነ ወጣቶች ያን ያክል አጥብቀው ቢፈልጉት የሚያስገርም አይሆንም፡፡ አሳዛኙ ነገር ብዙ ጊዜ ወደ ስኬት ያደርሳሉ ተብለው በአንዳንድ ዓለማውያን አማካሪዎች የሚነገሩ አሳቦች በትክክል ስኬታማ ማድረግ መቻላቸው አስተማማኝ አለመሆኑና ዘዴዎቹ ወጥነት የሚጎድላቸው እንዲሁም በጣም ብዙና አንዳንዴም የሚቃረኑ መሆናቸው ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ደግሞ የትኛውን ዘዴ መጠቀም እንደሚሻል ማወቅ ብቻ ፈታኝ ይሆናል፡፡

Read more

መስቀልና ስሙ

…በመ/ር ማዕበል ፈጠነ…

     ታሪክ እንደሚነግረን በቀደመው ዘመን ለመስቀልና ለማርያም ስግደት አይገባም የሚሉ ባዕዳን ተነሥተው ነበር፡፡ ለዚህም ብዙ ሊቃውንት ብዙ ድርሰት ደርሰዋል፡፡ ከቅዱስ መጽሐፍ እየጠቀሱ በመንፈስ ቅዱስ እየተመሩ መልስ ሰጥተዋል፡፡ በዚህ ዘመን ከተደረሱት ድርሳናት አንዱ መጽሐፈ ምሥጢር ነው፡፡ መጽሐፉ የተነሣበት አላማ ደግሞ የድንግል ማርያምን ክብርና የመስቀልን ክብር ከፍ አድርጎ መተንተን እንደሆነ መጽሐፉ ያስረዳል፡፡ በመጽሐፉ ዙሪያ ጥናትና ምርምር ያደረጉ ሊቃውንትም በዚህ ይስማማሉ፡፡

Read more

ታቦት በሐዲስ ኪዳን

…በመ/ር ማዕበል ፈጠነ…

  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግን ታቦተ እግዚአብሔር የሌላትን ቤተ ክርስቲያን ቤተ ክርስቲያን ናት›› ብላ አትቀበልም፡፡ በራሷ ሥርዐት እንኳ ታቦት የሌለውን ይቅርና ቤተ ክርስቲያን ተብሎ ተሠርቶ በሊቀ ጳጳስ ጸሎት በቅብዐ ሜሮን ካልከበረ ሕንፃውን ብቻ ቤተ ክርስቲያን ብላ አትቀበለውም፡፡ ለዚህም ‹‹ቤተ ክርስቲያን እንተ አልባቲ ጳጳስ ምሥያጥ ይእቲ፤ ጳጳስ የሌላት ስብሐተ እግዚአብሔር የማይደረስባት ቤተ ክርስቲያን ብትኖር ገበያ እንጂ ቤተ ክርስቲያን ተብላ አትጠራም›› ስትል በቀኖናዋ ታስተምራለች፡፡ ታቦት ያስፈልጋል ብላ የምታስተምረውም በብሉይ ኪዳን የጌታችን በሐዲስ ኪዳን የቅዱስ ጳውሎስን ትምህርት ያለ መቆነጻጸል ተቀብላ ነው፡፡ (ፍት መን  አን 1)

     እንዲያም ሆኖ ምእመናን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መሆናቸውን ረስታ፣ ዘንግታ፣ ስታና ተሳስታ አይደለም፡፡ ይልቁንም ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹አኮኑ ንህነ ቤቱ ለእግዚአብሔር ሕያው፤ እኛ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አይደለንምን›› የሚለውን ቃል ተቀብላ በትሩፋታቸው የደከሙትን ሩጫቸውን የጨረሱትን ሃይማኖታቸውን የጠበቁትን እግዚአብሔር የጽድቅ አክሊል የሰጣቸውን አክብራ በስማቸው ታቦት አስቀርጻ ‹‹ቅዱሳን አበው›› ብላ ታከብራቸዋለች፡፡ እነዚህ በአፀደ ሥጋ ሳሉ አምላካችን ‹‹ወዳጆቼ›› ብሎ  የጠራቸው ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ›› ብሎ የገለጻቸው ንጹሓን ናቸው፡፡

Read more