መናፍቃን የሚስቱባቸውና የሚያስቱባቸው መንገዶች (አራተኛ ክፍል)

በዳዊት አብርሃም

ጥቅሱን ካጠቃላዩ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነገረ መለኮት (Biblical Theology) አንጻር ለማየት አለመቻል

 ትክክለኛ ትምህርተ መለኮት ጥቅሶችን በዘፈቀደ መደርደር አይደለም፡፡ የተደረደሩት ጥቅሶች ከጥንት ከሐዋርያት ጀምሮ በመጣ አመክንዮ ተያይዘው ትርጉም የሚያስገኙበት ዘዴ አለ፡፡ ይህም ትውፊት ይባላል፡፡ ትውፊት የሌላቸው አብያተ ክርስቲያናት የሉም፡፡ ትውፊትን የሚያጥላሉት ፕሮቴስታንቶች እንኳ ከአውሮፓ የተሐድሶ አባቶች ከነማርቲን ሉተር የሚነሣ የአስትምህሮ ቅብብሎሽ አላቸው፡፡ ምንም አስተምህሯቸውን በጣም የሚለውጡ ክስተቶች እየተፈጠሩ ከነርሱ መካከል ወግ አጥባቂዎች የሆኑት እስኪደነግጡ ቢደርሱም መለዋወጥን የሚፈቅድ ሥርዓት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ የራሳቸው ትውፊት ነው፡፡

Read more

መናፍቃን የሚስቱባቸውና የሚያስቱባቸው መንገዶች (ሦስተኛ ክፍል)

…በዳዊት አብርሃም…

ጥቅሱን ከዳራው መነጠል

መጽሐፍ ቅዱስ ምንም በመንፈስ ቅዱስ አነሳሽነት የተጻፈ ቢሆንም የተጻፈው ግን በሰዎች ነው፡፡ የተጻፈውም ለሰዎች ነው፤ የተጻፈበት ቋንቋ፣ ቦታና የተወሰነ ጊዜ አለ፡፡ ስለዚህ የአጻጻፉን ባህል፣ በዘመኑ የነበረውን ኹኔታ፣ መጽሐፉ የተጻፈበትን ዓላማ በማወቅና በዚያም ውስጥ የጥቅሱን ትክክለኛ መልእክት በመረዳት መጥቀስ እንጂ እንደመሰለ አንሥቶ መጥቀስ ስሕተት ላይ ይጥላል፡፡

Read more

መናፍቃን የሚስቱባቸውና የሚያስቱባቸው መንገዶች (ክፍል ሁለት)

በዳዊት አብርሃም

  1. ጥቅሱን ከዓውዱ ነጥሎ መጥቀስ

አንድን ጥቅስ በተሟላ መልኩ በትክክል ጠቅሶ ድምዳሜ ላይ መድረስ ትክክል ባይሆን እንኳ የተሻለ ነገር አያጣውም፡፡ ስሕተቱን የከፋ፣ የስሕተት ስሕተት የሚያደርገው አንዲቷን ጥቅስ ቆንጽለው ሲጠቅሷት ነው፡፡ ብዙዎች መናፍቃን አንድን ጥቅስ አሟልተው ለመረዳት ጥቂት መስመሮችን ከፍ ብለው እንዲሁም ከጠቀሱት ጥቅስ ቀጥሎ ያሉትን ጥቂት ዐረፍተ ነገሮች ጨምረው ለመመልከት ቢሞክሩ ድምዳሜያቸውን ርግፍ አድርገው መተው ወይም የሚያሰሙትን ተቃውሞ ባልደገሙት ነበር፡፡

ይህንም በሚቀጥሉት ስለ ነገረ ድኅነት ከተጻፉት ጥቅሶች አንጻር እንመልከት፡፡ “ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፡፡” (ኤፌ2፡8-9) የዚህ ጥቅስ መልእክት በጣም ግልጽ ይመስላል፤ ጥቅሱ ‹ሥራ አያስፈልግም፣ እምነትና ጸጋ ብቻቸውን ለመዳን በቂ ናቸው› የሚል መልእክት የያዘ መስሎ ይታያል፡፡ ግን ሳንቸኩል አንድ ቁጥር ወረድ ብለን ንባባችንን ብንቀጥል እንዲህ የሚል እገኛለን፡፡ “እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።” (ኤፌ2፡10)

Read more

መናፍቃን የሚስቱባቸውና የሚያስቱባቸው መንገዶች (ክፍል አንድ)

ዳዊት አብርሃም

ነገረ ድኅነትን (የመዳን ትምህርትን) በተሳሳተ መንገድ የሚያስቡና ስሕተት የሆነን ትምህርት ከማስተማር አልፈው ትክክል የሆነውን የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ የሚቃወሙ ወገኖች እዚህ አቋም ላይ ሊደርሡ የቻሉበት በርካታ ምክንያቶች ቢኖሩም ከብዙዎቹ ምክንያቶች መካከል ጥቂቶቹን በመለየት ቀለል ያለውን መንገድ መርጠን ለማየት እንሞክራለን፡፡ የስሕተቶቹ መነሻ በመጠኑ ሲዳሰስ የሚከተለውን ይመስላል፡፡

  1. በአንዲት ነጠላ ጥቅስ ላይ መመሥረት

 

በማንኛውም የትምህርት መስክ አንድ አቋም ላይ ለመድረስ በቂ የሆነ መረጃ መያዝ እንደሚያስፈልግ የጥናትና ምርምር ሕግ ግድ ይላል፡፡ ዓለማዊ ወይም ምድራዊ ነገር ይህን ያህል ጥንቃቄ የሚያስፈልገው ከሆነ ሰማያዊው የነገረ መለኮት ዕውቀት ደግሞ የቱን ያህል ጥንቃቄ፣ የቱንስ ያህል ትዕግሥት ይሻ ይሆን? በተለይ የሰው ልጆችን ዘለዓለማዊ ሕይወትና ዘለዓለማዊ ጥፋት በቀላሉና በችኮላ፣ በተወሰኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ላይ ብቻ በመመሥረት ለማወቅና እውነቱ ይህ ብቻ ነው ብሎ ለመደምደም መሞከር ከባድ ስሕተት ላይ መጣሉ አይቀርም፡፡ ብዙዎቹ መናፍቃን ግን በጥቂት ጥቅሶች ላይ ከመመሥረት አልፈው በሁለትና በሦስት ጥቅሶች ላይ ብቻ ተመሥርተው ይደመድማሉ፡፡ ይህ ብቻ አይደለም፤ በጣም በሚገርም ኹኔታ በአንዲት ነጠላ ጥቅስ ላይ ብቻ ተመሥርተው ትልቅ ነገር መለኮታዊ ግንብ ለመገንባት ይጥራሉ፤ ወይም የተገነባውን ታላቅ ግንብ ለመናድ ይሞክራሉ፡፡ አንዳንዶች አንዲትን ቃል መዘው በመያዝ መዳን በጌታ ነው ሲሉ ይደመጣሉ፤ ቀጥለውም ቅዱሳን ለመዳን ምንም ሚና ሊኖራቸው አይገባም በማለት ይደመድማሉ፡፡

Read more

ማዘንና መጸለይ (ከባለፈው የቀጠለ)

በዲ/ን ታደለ ሲሳይ

  1. የቤተ ክርስቲያን ሰላም በጠፋ ጊዜ

ክርስቶስ በደሙ ዋጅቶ የመሠረታት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለድኅነታችን መንገድ፣ ለህልውናችን ዋስትና፣ ለሰማያዊ ቤታችን ደግሞ ተስፋ ናት፡፡ ይህንን መንገድ፣ ዋስትናና ተስፋ የምናገኘውና ተጠቃሚም የምንሆነው የኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰላም ሲጠበቅ፣ መንጋዎቿ ፈጣሪያቸው በፈቀደላቸው መስክ ብቻ መሠማራት ሲችሉ፣ እረኞቹ ከመንጋው ባለቤት ከኢየሱስ ክርሰቶስ የተቀበሏቸውን በጎች ከቀበሮና ከሌሎች አውሬዎች መጠበቅ ሲችሉ ነው፡፡ ይህ የሚሆነው ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ሰላም ተጠብቆ ሲቀጥል ብቻ ነው፡፡

Read more

ማዘንና መጸለይ

በዲ/ን ታደለ ሲሳይ

የሰው ልጅ በመጀመሪያ ሲፈጠር ዓለምን ከፈጣሪ በታች እየመራ፣ ፍጡራን ሁሉ ይገዙለት ዘንድ ነበር፡፡ አዳም በተፈጠረ ጊዜም ጣርና ሐዘን፣ መከራና ስቃይ አልነበረበትም፤ ይልቁንም በድሎትና በደስታ ይኖር ነበር እንጂ፡፡ ይሁን እንጂ አድርግ የተባለውን ብቻ ማድረግ ሲኖርበት አትብላ የተባለውን ዕፀ በለስ በመብላቱ የሞት ሞት አገኘው፡፡ አዳምና ሔዋን ስቃይና እንግልት፣ ፈተና፣ ሐዘንና መከራ ደረሰባቸው፡፡ ከዚያ በኋላ ያለው የሰው ልጅ ኑሮው በችግርና በድሎት፣ በስደትና በመረጋጋት፣ በሐዘንና በደስታ፣ በማሸነፍና በመሸነፍ፣ በመርታትና በመረታት መካከል ሆነ፡፡ የሰው ልጅ ሕይወትም መውደቅና መነሣት፣ ማግኘትና ማጣት፣ መከፋትና መደሰት፣ ማዘንና መረጋጋት ልማዱ ሆነ፡፡

Read more

በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን (ገላ. 5÷1)

በዲ/ን ታደለ ፈንታው

በኦርቶዶክሳዊ ክርስቲያናዊ አስተምህሮ ያሉት ምርጫ ሁለት ናቸው፡፡ እነርሱም የቅዱስ ጋብቻ ሕይወትና የምንኩስና ሕይወት ነው፡፡ የቅዱስ ጋብቻ ሕይወት ደግሞ የእጮኝነት ጊዜያት አሉት፡፡ አንድ ወደ ጋብቻ ለመምጣት የወሰነ ወይም የወሰነች ወጣት ሦስት ነገሮችን እንዲያሟላ (እንድታሟላ) ይመከራል፡፡ እነዚህም

  1. መንፈሳዊ ብስለት

መንፈሳዊ ብስለት እንዲህ ከሚለው የእግዚአብሔር ቃል ጋር ይስማማል፡ ፡ “ጎበዞች ሆይ ክፉውን አሸንፋችኋልና እጽፍላችኋለሁ” (1ዮሐ.2፥13) ተብሎ ስለተጻፈ ክፉ የሆነውን ወይም ኀጢአት የሆነውን ነገር ጽድቅ ከሆነው ለይቶ ማወቅ፣ ክፋት፣ ማስወገድና መልካም በሆነው በጽድቅ መንገድ መመላለስ ነው፡፡

Read more

በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን (ገላ. 5÷1)

በዲ/ን ታደለ ፈንታው

ይህ መልእክት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች በጻፈው መልእክቱ በምዕራፍ አምስት ቁጥር አንድ ላይ የተቀመጠ ኀይለ ቃል ነው፡፡ የገላትያ ሰዎች አስቀድመው እግዚአብሔርን ያወቁ፣ ክፉ ከሆነው ከዚህ ዓለም የሥጋ ዐሳብ ያመለጡ፣ በሃይማኖት የሚኖሩ፣ ከክፋት የራቁ፣ መልካም የሆነውን ነገር ፈትነው የተቀበሉ፣ ለማፍረስ ያይደለ ለማነጽ የተጠሩ፣ ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ ደፋ ቀና የሚሉ፣ ሌትና ቀን በቤተ መቅደሱ በጸሎት ሁሉ የሚተጉ ክርስቲያኖች ነበሩ፡፡ አስቀድመው በተጠሩበት መጠራት መመላለስ ሲያቅታቸው ከመንፈሳዊው ነገር ይልቅ ትኩረታቸው ጉጉታቸውና አላማቸው ሥጋዊ ነገር ላይ ሲያርፍ ትውክልታቸው እግዚአብሔር መሆኑ ቀርቶ ምድራዊ ነገር ሲሆን የሚፈሩት ነፍስንና ሥጋን አንድ አድርጎ በገሀነም የሚቀጣውን እግዚአብሔርን ሳይሆን ጊዜ የሰጣቸውን ወገኖች ሆኖ ቢያገኛቸው እንዲህ የሚል መልእክት ጻፈላቸው፡፡ ‹‹በክርስቶስ እናንተን ከጠራች ከእርሱ ወደልዩ ወንጌል እንዲህ ፈጥናችሁ እንዳለፋችሁ እደነቃለሁ እርሱ  ግን ሌላ አይደለም የሚያናውጧችሁ የክርስቶስን ወንጌል ሊያጣምሙ የሚወዱ አንዳንድ ወገኖች አሉ እንጂ›› (ገላ.1፥6) በማለት ይጽፍላቸዋል፡፡ ክርስቲያኖችን ሁል ጊዜ በሚያባብል ቃል መቅረብ አስፈላጊ አይደለም፡፡ Read more

ጠንካራ ማንነት

…በዳዊት አብርሃም…

በዓለም ስትኖር ብዙ ሓላፊነቶችን ለመወጣት አለብህ። በዓለም መኖር ዓለማዊ መሆን አይደለም። ከኀጢአት ርቆ ዓላማን በማሳካት ምድራዊና መንፈሳዊ ሕይወትን አስተባብሮ መኖር ነው እንጂ። አንድ ሰው ጠንካራ ማንነትን ገንብቷል የሚባለው ምድራዊውንና ሰማያዊውን ዓለም አስታርቆ መኖር ሲችል ነው። በመሆኑም ጠንካራ ማንነትን ለመገንባት የሚከተሉትን አድርግ።

Read more

ከእግዚብሔር ጋር መሆን

…በዳዊት አብርሃም…

አንድ ክርስቲያን ከሁሉ አስቀድሞ ከእግዚአብሔር ጋር ለመሆን ማቀድ ይኖርበታል፡፡ ይህም የተሳካ መንፈሳዊ ሕይወት እንዲኖረው ያስችለዋል፡፡ የተሳካ መንፈሳዊ ሕይወት ደግሞ ለስኬታማ ምድራዊ ሕይወት መሠረት ነው፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን ነጥቦች በመመልከት ለመተግበር መጣር ያስፈልጋል፡፡

  1. ጸሎት

“ወደፈተና እንዳትገቡ ተግታችሁ ጸልዩ፡፡” ተብለን በተመከርነው መሠረት በግል፣ በቤተሰብና በማኅበር በያንዳንዷ ሥራችን መጀመሪያና መጨረሻ እንዲሁም በማዕድ ስንቀመጥ ልንጸልይ ይገባል፡፡ ጸሎት ከእግዚአብሔርም ጋር የምንሆንበት ዋነኛው መንገድ ነው፡፡ እግዚብሔርም ከእኛ ጋር የሚንሆንበት ዋነኛው መንገድ ነው፡፡ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ደግሞ ሁሉም ነገር ይከናወንልናልና፡፡ ሌላው ቀርቶ እግዚአብሔር ከርሱ ጋር መሆኑን ማሳብና ማመን የቻለ ሰው ይህን በማሰቡ ብቻ ከፍርሐት ነፃ ይሆናል፡፡ ሰላማዊ መንፈስም ይኖረዋል፡፡

Read more