ስኬት

…በዳዊት አብርሃም…

“ስኬት” የሚለውን ቃል የማይወድ ሰው ያለ አይመስልም:: በተለይ ራእይ ያላቸው ወጣቶች ስኬታማ መሆንን አጥብቀው ስለሚፈልጉ ብዙ ይጨነቃሉ፡፡ ወደ ስኬት የሚያመሩ መንገዶችን ይጠቁማሉ የተባሉ መጻሕፍትን ያነባሉ፡፡ ብዙ ጊዜም ታላላቆችንና ባለሙያዎችን ስለዚሁ ጉዳይ ምክር ይጠይቃሉ፡፡ እርስ በርስ ይወያያሉ፡፡ ብቻቸውን ሲሆኑም ከራሳቸው ጋር የሚመክሩት ጉዳይ ቢኖር እንዴት ስኬታማ መሆን እንደሚችሉ ነው፡፡ በርግጥ ስኬት ለማንኛውም ሰው ወሳኝ መሆኑ ግልጽ ስለሆነ ወጣቶች ያን ያክል አጥብቀው ቢፈልጉት የሚያስገርም አይሆንም፡፡ አሳዛኙ ነገር ብዙ ጊዜ ወደ ስኬት ያደርሳሉ ተብለው በአንዳንድ ዓለማውያን አማካሪዎች የሚነገሩ አሳቦች በትክክል ስኬታማ ማድረግ መቻላቸው አስተማማኝ አለመሆኑና ዘዴዎቹ ወጥነት የሚጎድላቸው እንዲሁም በጣም ብዙና አንዳንዴም የሚቃረኑ መሆናቸው ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ደግሞ የትኛውን ዘዴ መጠቀም እንደሚሻል ማወቅ ብቻ ፈታኝ ይሆናል፡፡

Read more

መስቀልና ስሙ

…በመ/ር ማዕበል ፈጠነ…

     ታሪክ እንደሚነግረን በቀደመው ዘመን ለመስቀልና ለማርያም ስግደት አይገባም የሚሉ ባዕዳን ተነሥተው ነበር፡፡ ለዚህም ብዙ ሊቃውንት ብዙ ድርሰት ደርሰዋል፡፡ ከቅዱስ መጽሐፍ እየጠቀሱ በመንፈስ ቅዱስ እየተመሩ መልስ ሰጥተዋል፡፡ በዚህ ዘመን ከተደረሱት ድርሳናት አንዱ መጽሐፈ ምሥጢር ነው፡፡ መጽሐፉ የተነሣበት አላማ ደግሞ የድንግል ማርያምን ክብርና የመስቀልን ክብር ከፍ አድርጎ መተንተን እንደሆነ መጽሐፉ ያስረዳል፡፡ በመጽሐፉ ዙሪያ ጥናትና ምርምር ያደረጉ ሊቃውንትም በዚህ ይስማማሉ፡፡

Read more

ታቦት በሐዲስ ኪዳን

…በመ/ር ማዕበል ፈጠነ…

  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግን ታቦተ እግዚአብሔር የሌላትን ቤተ ክርስቲያን ቤተ ክርስቲያን ናት›› ብላ አትቀበልም፡፡ በራሷ ሥርዐት እንኳ ታቦት የሌለውን ይቅርና ቤተ ክርስቲያን ተብሎ ተሠርቶ በሊቀ ጳጳስ ጸሎት በቅብዐ ሜሮን ካልከበረ ሕንፃውን ብቻ ቤተ ክርስቲያን ብላ አትቀበለውም፡፡ ለዚህም ‹‹ቤተ ክርስቲያን እንተ አልባቲ ጳጳስ ምሥያጥ ይእቲ፤ ጳጳስ የሌላት ስብሐተ እግዚአብሔር የማይደረስባት ቤተ ክርስቲያን ብትኖር ገበያ እንጂ ቤተ ክርስቲያን ተብላ አትጠራም›› ስትል በቀኖናዋ ታስተምራለች፡፡ ታቦት ያስፈልጋል ብላ የምታስተምረውም በብሉይ ኪዳን የጌታችን በሐዲስ ኪዳን የቅዱስ ጳውሎስን ትምህርት ያለ መቆነጻጸል ተቀብላ ነው፡፡ (ፍት መን  አን 1)

     እንዲያም ሆኖ ምእመናን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መሆናቸውን ረስታ፣ ዘንግታ፣ ስታና ተሳስታ አይደለም፡፡ ይልቁንም ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹አኮኑ ንህነ ቤቱ ለእግዚአብሔር ሕያው፤ እኛ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አይደለንምን›› የሚለውን ቃል ተቀብላ በትሩፋታቸው የደከሙትን ሩጫቸውን የጨረሱትን ሃይማኖታቸውን የጠበቁትን እግዚአብሔር የጽድቅ አክሊል የሰጣቸውን አክብራ በስማቸው ታቦት አስቀርጻ ‹‹ቅዱሳን አበው›› ብላ ታከብራቸዋለች፡፡ እነዚህ በአፀደ ሥጋ ሳሉ አምላካችን ‹‹ወዳጆቼ›› ብሎ  የጠራቸው ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ›› ብሎ የገለጻቸው ንጹሓን ናቸው፡፡

Read more

ታቦት በቅዱስ ጳውሎስ አንደበት

…በመ/ር ማዕበል ፈጠነ…

ታቦት ከእግዚብሔር ለእሥራኤል ዘሥጋ የተሰጠ ስመ አምላክ የተጻፈበት ሰው በእግዚአብሔር ትእዛዝ ውስጥ መሆኑን የሚያመለክት ምሥጢራዊ ሀብት ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ለእስራኤል ዘሥጋ የሰጠውን ታቦት ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ በሐዲስ ኪዳን ጠቅሶ ሲያስተምርበት እንመለከታለን፡፡ እንደሚታወቀው ቅዱስ ጳውሎስ  ዓለምን በሚያስተምርበት መዋዕለ ስብከቱ  ታቦትን ከጣዖት  ለይተው ያላወቁ  ጥሬ ደቀ መዛሙርት ነበሩ፡፡ ይኸውም በቅዱስ ጳውሎስ አነጋገር ታውቋል፡፡ ያም ማለት ‹‹ለመሆኑ  ታቦተ እግዚአብሔርን  ከጣዖት ጋር አንድ የሚያደርግ ማን ነው›› ብሎ ታቦትን ከጣዖት ለይቶ ማስተማሩ  ነው፡፡  ይህን ሊል የቻለው ቅድመ ኦሪት የነበሩ እስራኤል ዘሥጋ  በከነዓናውያን ፍቅረ ጣዖት እየተሳቡ ወደቤተ ጣዖት ይገሠግሡ ነበር፡፡ ያን እንዲተዉ ጌታ በሙሴ እጅ ታቦትን ሰጣቸው፡፡

Read more

ታቦት ምንድን ነው?

…በመ/ር ማዕበል ፈጠነ…

ሕገ እግዚአብሔር በወረቀት ላይ መጻፍ ሲጀምር በብዙ ቁጥር የሚቆጠሩ ምሥጢራት በእግዚአብሔር አንደበት ለሊቀ ነቢያት ሙሴ ተነግረዋል፡፡ ነቢዩ ሙሴ ከእግዚአብሔር ጋር ቃል በቃል ከተነጋገረባቸው አንዱ ምሥጢር ደግሞ ‹‹እንደ ቀደመው የድንጋይ ጽላት ቅረፅ›› የሚለው ትእዛዝ ነው፡፡ ይህም ‹‹እግዚአብሔር ሙሴን አለው ‹‹ሁለት የድንጋይ ጽላት እንደ ፊተኛው አድርገህ ቅረፅ፤ ወደእኔም ወደ ተራራው ውጣ በሰበርሃቸው በፊተኞቹ ጽላቶች የነበሩትን ቃላት እጽፍባቸዋለሁ›› ይላል፡፡ ዘጸ. 34÷1-2

  ከመጽሐፍ ቅዱሱ ንባብ ውስጥ በማያሻማ መልኩ እንደ ተመለከትነው ሙሴ በቀደሙት ጽላት ፋንታ ሌላ ጽላት እንዲቀርፅ ትእዛዝ ተሰጥቶታል፡፡  ዝቅ ብሎም  ‹‹ወወቀረ ሙሴ ክልኤተ ጽላተ ከመ ቀዳምያት፤ ሙሴም ሁለት ጽላት እንደ ቀደመው አድርጎ ቀረፀ፤ ሲል ይደመድመዋል፡፡ ዘጸ. 34÷4

Read more

በፍቅር መኖር

…በመ/ር ኃይለ ሚካኤል ብርሃኑ…

በክርስቲያናዊ ሕይወት ለመኖር የወሰነ ሰው ሰውን ሁሉ ሊወድ ይገባል፡፡ ፍቅር ሲባል ፍትወታዊ የጾታ ፍቅር ሳይሆን ሁሉንም ሰው ሳይለያዩ መውደድ ነው፡፡ ለዚህ ነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሕግጋት ሁሉ ፍቅርን ያስበለጠው፡፡ (ዮሐ. 15፥12) ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን ሲጠቅስ በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ  ናስ ወይም እንደሚንሿሿ ጸናጽል ሆኛለሁ፤ ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና ዕውቀትን  ሁሉ ባውቅ ተራሮችንም እስካፈርስ ድረስ እምነት ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ፤ ድሆችን ልመግብ ያለኝን ሁሉ ባካፍል ሥጋዬንም ለእሳት መቃጠል፤ አሳልፌ ብሰጥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም፡፡ ፍቅር ይታገሣል፤ ቸርነትም ያደርጋል፤ ፍቅር አይቀናም፤ ፍቅር አይመካም፤ አይታበይም፤ የማይገባውን አያደርግም…(1ኛ ቆሮ. 13፥1) በማለት አስረድቷል፡፡

Read more

“እግዚአብሔርን ፈልጉት፥ ትጸናላችሁም፤ ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ።”

፩ኛ ዜና መዋዕል ፲፮፥፲፩ 

በዲያቆን በረከት አዝመራው

እግዚአብሔርን መፈለግ እና ወደ እርሱ ሰው ሁሉ መቅረብ ይገባዋል? ወይስ ጥቂቶች ብቻ የሚጣጣሩበት ሕይወት ነው ብለን እንደፈለግን መሆን ይቻለናል? በውኑ አእምሮ ያለው ፍጡር ያስገኘውን ፈጣሪውን ከመፈለግ፣ ከፈጣሪው ጋር ኅብረት ከመፍጠር እና የተፈጠረበትን ዓላማ ከመፈጸም የበለጠ ምን ታላቅ ተግባር አለው?

መልካም አባት ሁልጊዜ ለልጁ ጥሩ ነገርን እንደሚያስብ እና እንደሚያደርግ የታወቀ ነው። በዚህም ምክንያት “ጤነኛ” ልጅ ሁሉ አባቱን ይወዳል:: ካለማወቅ እና ከድካም የተነሳ አንዳንድ ጊዜ ቢሳሳትም በአብዛኛው ግን የአባቱን ትእዛዝ ይጠብቃል:: ታዲያ እግዚአብሔር “ከልብ ለሚፈልጉኝ ሁሉ እገኛለሁ፤ ከምድራውያን ወላጆች ጋር የማልነጻጸር መልካም አባት ነኝ፤ ለሚወዱኝ ዓይን ያላየው፣ ጆሮ ያልሰማው፣ በሰው ልብ ያልታሰበ ታላቅ ሥጦታን እሰጣለሁ” (፪ኛ ዜና መዋዕል ፲፭፥፪፣ ማቴ. ፯፥፲፩፣ ፩ኛ ቆሮ. ፪፥፱) እያለ ዘወትር እየተጣራ፤ ሰዎች ወደ እርሱ በሙሉ ልብ ለመቅረብ ፈቃዳችን የሚደክመው እና ዳተኛ የምንሆነው ለምንድን  ነው? Read more

ሕይወትን በማስተዋልና በዓላማ ስለመምራት

ዲያቆን መዝገቡ ዘወርቅ

“ስለዚህ እኔ ያለ አሳብ እንደሚሮጥ ሁሉ እንዲሁ አልሮጥም፤ ነፋስን እንደሚጎስም ሁሉ እንዲሁ አልጋደልም፡፡” (1ኛ ቆሮ. 9፥26)

በማስተዋልና በዓላማ የሚመራ፣ ወደ አንድ አቅጣጫ የተሰበሰበ ኑሮ (Focused Life) የሰውን ልጅ በሥጋም በነፍስም ስኬታማ የሚያደርግ እና በተፈጥሮአችን የተሰጠንን አቅም ተግባራዊ ለማድረግ የሚረዳን የኑሮ መሥመር ነው፡፡ በዚህ ጽሑፍ ሕይወታችንን እግዚአብሔር ወደሚደሰትበት መልካም አቅጣጫ ለመምራት የሚጠቅሙንን መንገዶች ለመዘርዘር እንሞክራለን፡፡ Read more

ጥቂት ስለ ነጻነት

በዲያቆን በረከት አዝመራው

ከጥቂት ወራት በፊት ነው፤ በተሳፈርኩበት ታክሲ ውስጥ በአለባበሳቸውም ሆነ በአነጋገራቸው ወጣ ያሉ ሦስት ወጣቶች አብረው ተሳፍረዋል። እነዚህ ወጣቶች ድምጻቸውን ለቀቅ አድርገው አብዛኛውን ተሳፋሪ የሚረብሽና አንገት የሚያስደፋ ንግግር ይነጋገራሉ።ድምጻቸው ከፍ ከማለቱ የተነሳ በታክሲው ውስጥ ያለው ሰው ሳይፈልግም ቢሆን እነርሱን ከመስማት ውጭ ሌላ ምንም አማራጭ አልነበረውም። Read more