መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
በዓለ ትንሣኤ ወዕርገታ ለቅድስት ድንግል ማርያም
ከዚህ ዓለም ውጣ ውረድና ድካም በ፷፬ ዓመቷ በጥር ፳፩ ቀን በ፵፱ ዓ.ም ያረፈችው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትንሣኤዋም ሆነ ዕርገቷ በክብር የተፈጸመ እንደመሆኑ እኛም ልጆቿ ይህችን የተባረከች ቀን እናከብራለን፡፡
ትዕግሥተኛዋ እናት ቅድስት እንባመሪና
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? የጾምን ወቅት እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? አባቶቻችን ሊቃውንት ስለ ጾም እንዲህ ይላሉ፤ ጾም ማለት ከምግብና ከውኃ መከልከል ብቻ ሳይሆን ከክፉ ሥራም መታቀብ (መከልከል) ነው፤ ጾም የጽድቅ በር ናት፣ ጾም ለመልካም ነገር የምታነሣሣን ናት፤ ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ስንጾም ከጸሎትና ከስግደት ጋር፣ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በማስቀደስ ፣ታዛዦች በመሆን የጾሙን ጊዜ ልናሳልፍ ይገባል፡፡ መልካም!
ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ ታሪክ የቅድስት እንባመሪናን ነው፡፡
ሙሻ ዘር
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፉት ክፍሎች ዘመድ ሙሻ ዘርን እና ባዕድ ሙሻ ዘርን ሰዋስውን ከሰዋስው ሳቢን ከተሳቢ እያናበቡ ዘጠኝ አገባባትን ሲያወጡ አይተናል። ከዚያ ቀጥለን ደግሞ ዛሬ የመጨረሻውን ክፍል እናያለን። መልካም ቆይታ!
በዓለ ደብረ ታቦር
በተከበረች በነሐሴ ፲፫ በታቦር ተራራ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ዕለት በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ”በዓለ ደብረ ታቦር‘ ተብሎ ይከበራል፡፡
ፅንሰታ ለማርያም
ለዓለም ሁሉ የድኅነት መገኛ የሆነች ክብርት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተፀነሰችበት ዕለት ነሐሴ ሰባት የተባረከች እንደመሆና መላው ክርስቲያን በዓሏን ሊያከብር ይገባል፤ የመፀነሷ ነገርም እንዲህ ነው፡፡…
ማርኩሽ በለኝ!
አንተን ይዛ በተሰደደችው
በርሃ አቋርጣ ግብጽ በገባችው
በድንግል እናትህ በአምስቱ ኀዘኗ
ማርኩሽ በለኝ ስለ ቃል ኪዳኗ!
ጾመ ፍልሰታ
አምላክን የወለደች እመቤታችን ድንግል ማርያም ከዕረፍቷ በኋላ ከእርሳቸው ስለመለየቷ ሐዋርያት ፈጽሞ እያዘኑ ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ተገለጠላቸው፤ እርሷን በሥጋ ያዩ ዘንድ እንዳላቸውም ተስፋ ሰጣቸው፡፡
ወንጌላዊ ዮሐንስም እስያ በሚባል አገር እያስተማረ ሳለ በነሐሴ ወር ዐሥራ ስድተኛ ቀን ተድላ ደስታ ወደአለባት ገነት በመንፈስ ቅዱስ ተነጠቀ፡፡ የክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን የእመቤታችን ማርያም ሥጋዋ ካለበት ከዕፀ ሕይወት ዘንድ ተቀምጦ አየው፡፡ የንጽሕት እናቱንም ሥጋ ታወጣ ዘንድ ምድርን እንዲጠሩዋት ሰባቱን የመላእክት አለቆች አዘዛቸው፤ እነርሱም ”የንጽሕት እናቱን ሥጋ ታወጪ ዘንድ እግዚአብሔር አዞሻል‘ አሏት፡፡ያን ጊዜም ከዕፀ ሕይወት በታች ካለ መቃብር የእመቤታችን ማርያም ሥጋዋ ወጣ፡፡…
ሙሻ ዘር
የተወደዳችሁ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ ‹‹እርባ ቅምር›› በሚል ርእስ የሁለተኛውን ክፍል ይዘንላችሁ ቀርበን ነበር፡፡ በዚህ ሳምንት ደግሞ ለሰጠናችሁ መልመጃ ምላሽና ስለ ‹‹ሙሻ ዘር›› እናስተምራችኋለን፤ በጥሞና ተከታተሉን!
ዐሥሩ ማዕረጋት
የምድርን መከራ፣ ችግርና ሥቃይ አልፎ በእምነት ጽናትና በመልካም ምግባር ለሚኖር ሰው የቅድስና ሕይወት እጅግ ጣፋጭ ናት፡፡ በጠቧቧ መንገድ በእውነት በመጓዝ ፍቅር፣ ሰላምንና የመንፈስ እርካታን በማጣጣም ጥዑመ ነፍሰ ምግብን እየተመገበ የመንፈስን ፍሬ ለመብላት በሚያበቃው በክርስትና ሕይወትም ይኖራል፡፡ መስቀልን የጦር መሣሪያ ወንጌልን ጋሻ መከታ አድርጎ ጠላት ዲያብሎስን ድል የነሣ እንደ እነ አቡነ ተክለሃይማኖት ዓይነት ጻድቅ ደግሞ በቅድስና ማዕረግ ወደ መንግሥተ ሰማያት ይጓዛል፡፡
በርግጥም በቅድስና ሕይወት ሁሉም ተመሳሳይ ችሎታና ትጋት ሊኖረው አይችልም፤ እግዚአብሔር በሰጠው መክሊት ግን አትርፎ በከበረ ሞት ወደ ፈጣሪው መሄድ ይቻለው ዘንድ የአምላካች ቅዱስ ፈቃድ ነው፡፡ ሰው በመንፈሳዊ ብርታት ፈታናውን ሁሉ ማለፍ ከቻለ ለተለያዩ ክብር እንደሚበቃ ቅዱሳት መጻሕፍት ምሥክሮች ናቸው፡፡ ቅዱሳን በገድልና በትሩፋት ብዛት የሚያገኟቸው ዐሥር ማዕረጋት አሉ፡፡ ‹ጽማዌ፣ ልባዌ፣ ጣዕመ ዝማሬ፣ አንብዕ (አንብዐ ንስሓ)፣ ኩነኔ፣ ፍቅር፣ ሑሰት፣ ንጻሬ መላእክት፣ ተሰጥሞ እና ከዊነ እሳት› የሚል ስያሜም አላቸው፡፡ የንጽሐ ሥጋ፣ የንጽሐ ነፍስና የንጽሐ ልቡና ማዕረጋት በመባል ደግሞ በሦስት ክፍሎች ይከፈላሉ፡፡
ቅድስት መስቀል ክብራ
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? ወርኃ ክረምቱ እንዴት ነው? መቼም ዝናቡና ቅዝቃዜው እንደፈለግን እንዳንጫወት አድርጎናልና ከቦታ ቦታ ለመንቀሳቀስም አያመችም፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ቤት ውስጥ እንደምንቆይ ይታወቃል፡፡ ታዲያ ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም መጻሕፍትን ማንበብ፣ ለቀጣዩ ዓመት የትምህርት ጊዜ የሚረዱንን ጥናቶች በማድረግ ልንዘጋጅ ያስፈልጋል፤ ጊዜያችንን በአግባቡ በቁም ነገር ላይ ማዋል አለብን! ደግሞም በጉጉት የምንጠብቃት ጾመ ፍልሰታም እየደረሰች ነው!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለዛሬ ያዘጋጀንላችሁ የቅድስት መስቀል ክብራን ታሪክ ነው፡፡