መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የ6 ወር የሥራ አመራር ስብሰባ ውሳኔዎችን አስመልክቶ ከማኅበሩ የሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት የተሰጠ መግለጫ
በማኅበራችን ማኅበረ ቅዱሳን ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ያደረገው የ6ወሩ የሥራ አመራር ስብሰባ ወሳኔዎችን አስመልቶ ከማኅበሩ ሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት የተሰጠ መግለጫ። ሙሉ መግለጫውን እዚህ በመጫን መመልከት ይቻላል፡፡
አስደናቂው ሞት
ክብረ ድንግል ማርያም
እግዚአብሔር ዘላለማዊ ኃይሉንና አምላክነቱን ለዓለም ከገለጸበት ታላቅ ሥራ መካከል በእመቤታችን በቅድስት ድንግል
ማርያም የገለጸው ድንቅ ሥራው በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ቀዳሚውን ሥፍራ ይይዛል፡፡ ይህንን ሁኔታ ድንግል ማርያም “ብርቱ የሆነ እርሱ ታላቅ ሥራን በእኔ አድርጓል ስለዚህም ምክንያት ፍጥረት ሁሉ ያመሰግኑኛል” ሉቃ.፩፥፵፱/1፥9/ በማለት ገለጸችው፡፡ ቅድሰት ኤልሳቤጥም የጌታዬ እናት” አለቻት /ሉቃ.፩፥፵፫/1፥43/ “መልአኩ ቅዲስ ገብርኤል ከሴቶች መካከል ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ” /ሉቃ.፩፥፳፰/1፥28/ አላት፡፡ ቅዱስ ዳዊት ልጄ ይላታል መዝ.፵፬፥፱/44፥9/ ሰሎሞን እኅቴ ይላታል /መኃ.፭፥፩/5፥1/ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስም እናት ሆና ተሰጠችው /ዮሐ.፲፱፥፳፮/19፥26/ ይህንን ድንቅ ሥራ ውስንና ደካማ የሆነ አእምሮ ሊገነዘበው ከሚችለው በላይ ነው፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን ላይ የተሠሩ የሐሰት ሰነዶችን አስመልክቶ ከማኅበሩ ሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት የተሰጠ መግለጫ፡፡
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ዕድገትና ልማት የማይፈልጉ አፅራረ ቤተ ክርስቲያን የማኅበሩን መልካም ስም በማጥፋት አገልግሎቱን ለማሰናከል በየጊዜው ይጥራሉ፡፡ በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የማኅበሩን ስም ለማጥፋት አመች ነው ብለው ያሰቡትን የሐሰት ሰነድ የማዘጋጀት ተግባራቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ ከዚህ በፊት በስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ የግንቦት ወር ልዩ ዕትም “የማኅበረ ቅዱሳን የ25 ዓመት ዕቅድ” ብለው ያዘጋጁትን የሐሰት ሰነድ አስመልክተን እንደገለጽነው ሁሉ አሁንም ሁለት የሐሰት ደብዳቤዎች በማኅበሩ የመቀሌ ማዕከል ስም ተዘጋጅተው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ት/ቤቶች ማ/መምሪያ መካነ ድር ተለቅቀዋል፡፡
የክብረ ገዳማት የቀጥታ ዘገባ
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። እንደምን ዋላችሁ ውድ ምእመናን አሁን የክብረ ገዳማትን የቀጥታ ዘገባ ለማቅረብ እንሞክራለን። 9:23 በዝናብ ምክንያት ዘግየት ብሎ የጀመረው ይህ መርሐ ግብር በጠቅላይ ቤተ ክህነት እየተደረገ ይገኛል። አዳራሹ ሞልቶ ምእመኑ ቆሞ በሚታይበት ሁኔታ በዚህ አመት ሙሉ ፕሮፌሰርነት ያገኙት ፕርፕፌሰር ሽፈራው በቀለ የጥናት ጽሁፋቸውን እያቀረቡ ይገኛሉ። “የገዳማት ደጀሠላሞች ዋጋ እንደሌላቸው ታስቦ […]
ለሑዳዱ አዝመራ ተዋሕዶ ስትጣራ የቀጥታ ዘገባ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ማኅበሩ ለሚያደርገው የስብከተ ወንጌል አገልግሎት የበኩላችንን ድርሻ እንወጣ፣ ሰለ አንዲት ነብስ መዳን የሰማይ መላእትም ምን ያህን እንደሚደሰቱ እናስተውል። ሐዋርያትም ደማቸውን ያፈሰሱባት አጥንታቸውን የከሰከሱባት አገልግሎት እርስዋ ናትና። ከአሁን በህዋላ ወር በገባ በሁለተኛው ሳምንት ዘወትር ረቡዕ ስለ ስብከተ ወንጌል የምንነጋገርበት መርሐ ግብር ይኖራል። “ለወደፊቱ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን ጠብቀው ከንቀሳቀሱ ማኅበራትና ሰ/ት/ቤቶች ጋር እንሠራለን ይህም ችግሮቻችንን ያቃልልሉናል ብለን እናስባለን” ቀሲስ ታደሰ ጌታሁን የትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዋና ክፍል አስተባባሪ የገንዘብ ችግር፣ የሰው ኃይልና የቁሳቁስ ችግሮች አገልግሎታችን እንዳይሰፋ እያደረጉት ነው” “ማኅበሩ በአንድ ጊዜ በአራቱም አቅጣጫ ሐዋርያዊ ጉዞ ማካሄድ ይችላል። […]
ክብረ ገዳማት በፆመ ፍልሰታ መጀመሪያ
ሦስት አራተኛው መሬት
እንግዳ ተቀባዩ አባ ቢሾይ(ለሕፃናት)
ሐምሌ23፣2003 ዓ.ም
አዜብ ገብሩ
ክብረ ገዳማት( ነሐሴ 1/2003 ዓ.ም
መሠልጠን ማለት ግን ምን ማለት ነው?!
ሥልጣኔ ሲተነተን አንድ ገጽታ፣ አንድ መልክ፣ አንድ ወጥ ሳይሆን ብዙ መልኮች፣ ብዙ ገጽታዎች እንዳሉት ማጤን ይገባል፡፡
ሥልጣኔ የሰው ልጅ አካባቢውን ለኑሮ እንዲስማማው፣ እንዲመቸው ለማድረግና ለሕይወቱ የተመቻቸ ሥፍራ ለማድረግ የዕለት ተዕለት ተግባር ውስጥ ቀስ በቀስ የተከሰተ ነው፡፡ በዚህ ረገድ ሥልጣኔ ጥንትም የነበረ፣ ዛሬም ያለ፣ ለወደፊትም የሚኖር የሰው ልጅ የተፈጥሮ እንቅስቃሴ ነው፡፡ ሆኖም ግን ስለ ሥልጣኔ ብይን ሲሰጥ፣ ስለ መግለጫው ሲነገር፣ ስለ ጥቅሙ ሲዘመር፣ ስለ ግቡ /መዳረሻው/ ሲታተት፤ ሥልጣኔ ከቁሳዊ ነገር መሟላትና ከሥጋዊ ድሎትና ምቾት ጋር ብቻ ሲያያዝ ይስተዋላል፡፡ ለዚህም ይመስላል የሥልጣኔን ክስተት በዓይን በሚታዩ፣ አብረቅራቂና ሜካኒካዊ በሆኑ ነገሮች ብቻ እንድናይ ከታች ጀምሮ በትምህርት ቤት እንድንማረው የሆነው፡፡ በሚዲያ ዘወትር እንድንሰማው የተደረገው፡፡ከበደ ሚካኤል ስለ ሥልጣኔ ምንነት ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፡፡