መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
በዋልድባ ገዳምና በወልቃይት ስኳር ልማት ፕሮጀክት መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት አስመልክቶ ማኅበረ ቅዱሳን ያደረገው ጥናት ዘገባ
ግንቦት 10/2004 ዓ.ም. ካለፉት ሁለትና ሦስት ወራት ወዲህ ከዋልድባ ገዳም ጋር በተያያዘ በመንግሥትና በገዳሙ መካከል አለመግባባት ተከስቷል፡፡ አለመግባባቱም ብዙዎችን አነጋግሯል፣ አከራክሯል፡፡ ከጉዳዩ መግዘፍ የተነሣ በርካቶችን ሲያስጨንቅና ሲያሳስብ ቆይቷል፡፡ የበርካታ ኢትዮጵውያንን ትኩረት የሳበ ሀገራዊ ጉዳይም ሆኗል፡፡ አለመግባባቱን ለማወቅ ከመጓጓት አንጻርም፤ የጉዳዩን ምንጭና መፍትሔ ነጣጥሎ ማየት እስከ ሚከብድ ድረስ በሰው ልቡና ሲመላለስ ቆይቷል፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ […]
“ዝክረ ገብረ እግዚአብሔር” በሚል ርዕስ ጉባኤ ተካሄደ፡፡
ግንቦት 10/2004 ዓ.ም.
በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖአምላክ
የቅዱስ ያሬድ መታሰቢያ ዐውደ ርዕይ ተከፈተ
ግንቦት 8/2004 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ቅዱስ ያሬድ የተሠወረበትን መታሰቢያ ዓመት ምክንያት በማድረግ ከግንቦት 5-12 ቀን 2004 ዓ.ም. የሚቆይ ዐውደ ርዕይ አዲስ አበባ በሚገኘው ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን ተዘጋጀ፡፡ የቅዱስ ያሬድ 1500ኛ ዓመት የልደት በዓል በተለያዩ መንፈሳዊ መርሐ ግብሮች በደማቅ ሁኔታ በሚቀጥለው ዓመት ለማክበር የደብሩ አስተደደር የደብሩ ስብከተ ወንጌል ጽ/ቤት ሰበካ ጉባኤውና ሰንበት ትምህርት ቤቱ ተቀናጅተው እየሠሩ የሚገኙ ሲሆን ይህ አውደ ርዕይ የመርሐ ግብሩ አንድ አካል መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸዋል፡፡
የአሰቦት ገዳምን ለመርዳት ጉባኤ ሊካሄድ ነው፡፡
ግንቦት 8/2004 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የአሰቦት ደብረ ወገግ ቅድስት ሥላሴና አቡነ ሳሙኤል ገዳምን ለመርዳት ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሸ ሰኔ 3 ቀን 2004 ዓ.ም. ከቀኑ 7 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል፡፡ ከ800 ዓመታት በላይ እድሜ ያስቆጠረው ገዳም በፃድቁ አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ የተመሠረተ ሲሆን በቅርቡ የገዳሙ ደን ተቃጥሎ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት መሆኑ ይታወሳል፡፡
በሕገወጦች በጨለማ የተዘጋጀው ደብዳቤ ተበተነ፡፡
ግንቦት 7/2004 ዓ.ም.
ከጥቂት ቀናት በፊት ማኅበረ ቅዱሳን ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ማእከላዊ አስተዳደር ተገዥ ካለመሆን አልፎ የተቋሙን ሕልውና ወደ መፈታተን እንደ ደረሰ በማተት የሚከስ ደብዳቤ ለሕግ ተገዢ ባልሆኑ ግለሰቦች በጨለማ ተረቅቆ በመምሪያው ሓላፊ እንዲፈረም ተደርጎ ሊወጣ እንደ ነበር፤ ነገር ግን በመምሪያው ሓላፊው በቆሞስ መልአከ ጽዮን አባ ኅሩይ መታገዱን ገልጸን ነበር፡፡ ከዚያ በኋላ እስከ አሁን ምክንያቱ ግልጽ ባልሆነ ሁኔታ “ፍጹም ሕገ ወጥ ድርጊት በሕጋዊዋና በእውነተኛዋ ቤተ ክርስቲያን መፈጸም የለበትም፤ ይቁም” ያሉትን የመመሪያ ሓላፊ አስተዳደሩ ከቦታቸው አንሥቷል፡፡ በምትካቸውም ከግብረ አበሮቻቸው ጋር በመሆን ደብዳቤውን በወቅቱ በተገለጠው ሁኔታ በማርቀቅ፣ እንዲፈረምና እንዲሠራጭ የሞት ሽረት ትግል ሲያደርጉ ከነበሩት ግለሰቦች አንዱ የሆኑትን መምህር ዕንቊ ባሕርይ ተከሥተን ሾሟል፡፡
ቤተ ክርስቲያን በኦሮሚያ ክልል ስለምትገኝበት ሁኔታ ዐውደ ጥናት ተካሄደ
ግንቦት 7/2004 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የአባ ማሩ ተረት /ለሕፃናት/
ግንቦት 7/2004 ዓ.ም.
በልያ አበበ
እንደምን አላችሁ ልጆች! እግዚአብሔር ይመስገን ደኅና ነን እንደምትሉ አልጠራጠርም፡፡ ዛሬ የምነግራችሁ ተረት ስለ አንበሳ፣ ጥንቸልና አሳማ ነው እሺ በጣም ጥሩ ልጆች ተረቱን ልንገራችሁ? ግን እኮ ስለራሴ አላስተዋወኳችሁም፡፡ ስሜ አባ ማሩ ዘነበ ይባላል፡፡ ቁመቴ በጣም አጭር ነው፡፡ ፊቴ ደግሞ ልክ እንደ ብርቱካን ክብ ሆኖ ዓይኖቼ ትናንሽ ናቸው፡፡ ሁል ጊዜ የምለብሰው ነጭ ሱሪና ነጭ ሸሚዝ ነው፡፡ ከእጄ ነጭ ጭራ አይለይም፡፡ ለምን ነጭ ጭራ እንደምይዝ ታውቃላችሁ? በሰፈሬ የሚኖሩ እንደ እናንተ ያሉ ሕፃናት ወደ 12፡00 ሰዓት አካባቢ ፀሐይ ስትገባ ተሰብስበው ይመጡና “አባ ማሩ ዘነበ ተረት ይንገሩን?” እያሉ በዙሪያዬ ስብስብ ይላሉ፡፡ እኔም ልጆችን በጣም ስለምወዳቸው ትንሸን ወንበሬን ይዤ ከቤቴ እወጣና ከግቢያችን ካለው ሰፊ ሜዳ ቁጭ እላለሁ፡፡ ልጆችም በዙሪያዬ ይሰበሰባሉ እሳት እየሞቅን ተረቱን አጫውታቸዋለሁ ታዲያ ያን ጊዜ ትንኞች በአፌ ውስጥ እንዳይገቡ በነጩ ጭራዬ እከላከላቸዋለሁ፡፡ ስለራሴ ይኸን ያኽል ከነገርኳችሁ ወደ ተረቴ ልመለስ፡፡ ዝግጁ ናችሁ ልጆች? ጎበዞች፡፡
የደጉዋ እናት ልደት/ለሕፃናት/
ግንቦት 3/2004 ዓ.ም.
በኢየሩሳሌም አገር የሚኖሩ ኢያቄምና ሃና የተባሉ በጣም ደጋግ ሰዎች ነበሩ፡፡ ኢያቄምና ሃና ለእግዚአብሔር የታዘዘ በተቀደሰ ጋብቻ ውስጥ በብዙ ዘመናት አብረው ቢኖሩም በነዚያ ጊዜያት ወስጥ አንድ ልጅ እንኳ ስላልነበራቸው እጅግ ያዝኑ ነበር፡፡ ወደ ቤተ መቅደስ እየሄዱ እግዚአብሔር ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ አጥብቀው ይለምኑት ነበር፡፡
የመጻሕትና የድምጽ ወምስል የምረቃ መርሐ ግብር ተካሔደ
ግንቦት 3/2004 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
በማኅበረ ቅዱሳን የልማት ተቋማት አስተዳደር ያሳተማቸውን መጻሕፍትና የድምጽ ወምስል የምረቃ መርሐ ግብር ሚያዚያ 27 ቀን 2004 ዓ.ም. በብሔራዊ ሙዚየም ትልቁ አዳራሽ አስመረቀ፡፡ ከተመረቁት መጻሕፍትና የድምጽ ወምስል ሥራዎች መካከል ዐስሩ የትርጉምና ወጥ መጻሕፍት ሲሆኑ በቪሲዲ እና በሲዲ የተዘጋጁ የአማርኛና የሞሮምኛ ስብከቶች ዘጋቢ ፊልሞች፣ ትርጉም ፊልሞችና መዝሙራት ይገኙበታል፡፡
የጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ የአንድነት ኑሮ ማኅበር ሰባኪያነ ወንጌልን አስመረቀ
ግንቦት 3/2004 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጽርሐ ጽዮን ዘተዋሕዶ የአንድነት ኑሮ ማኅበር በ14ኛው ዙር ለ3 ወራት ያሰለጠናቸውን 47 ሰባኪያነ ወንጌልን ሚያዚያ 21 ቀን 2004 ዓ.ም. አስመረቀ፡፡ በማኅበሩ የተመሠረተው የቅዱስ ተክለ ሃይማኖት የስብከተ ወንጌል
ማሰልጠኛ ተቋም በ12 የትምህርት ዓይነቶች ከጥር 21 ቀን 2004 ዓ.ም. ጀምሮ ከ16 ሀገረ ስብከቶች በተለይም ከገጠሪቱ ኢትዮጵያ ተውጣጥተው የተመረጡና እያንዳንዳቸው ከሁለት እስከ ሦስት ቋንቋ መናገር የሚችሉ ሰባኪያነ ወንጌልን ቡራዩ አካባቢ በሚገኘው በተቋሙ ግቢ ውስጥ በደመቀ መንፈሳዊ መርሐ ግብር አስመርቋል፡፡ ከተመራቂ ደቀ መዛሙርት መካከል መነኮሳት፣ ካህናት፣ መሪጌቶች፣ ዲያቆናትና የሰንበት ትምህርት ቤቶች አባላት ያካተተ ሲሆን ‹‹ለቤተ ክርስቲያናችን እጣን፣ ጧፍና ንዋያተ ቅድሳት ብቻ ሳይሆን ሰውም እንስጥ›› የሚል መመሪያ ይዞ በመነሣት በተለይም በገጠሪቱ ኢትዮጵያ እየታየ ያለውን የመምህራን እጥረት ለመቅረፍ ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ አቶ ማናዬ አባተ የማኅበሩ መንፈሳዊ አገልግሎት መምሪያ ሓላፊ በሪፖርታቸው ገልጸዋል፡፡