መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ቃለ ዓዋዲ
ጥቅምት 13 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ኅሩይ ባየ
ማእከሉ ጠቅላላ ጉባኤውን ሊያካሂድ ነው
ጥቅምት 12 ቀን 2005 ዓ.ም. በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ጠቅላላ ጉባኤውን የፊታችን ቅዳሜና እሑድ እንደሚያካሂድ የማእከሉ ዋና ጸሐፊ አቶ ካሳሁን ኀይሌ አስታወቁ፡፡ ቅዳሜ ጥቅምት 17 ቀን 2005 ዓ.ም ከሰዓት በፊት በሚኖረው የመክፈቻ መርሐ ግብር ላይ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስን ጨምሮ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ፣ የሀገረ […]
700 ምእመናን ወደ እናት ቤተ ክርስቲያናቸው ተመለሱ
ጥቅምት 12 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ
በቄለም ወለጋ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሐዲስ ለማ በየነ አማካኝነት፥ ለ31ኛው ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አጠቃላይ መንፈሳዊ የሰበካ ጉባኤ የቀረበው ሪፖርት፤ ለ28 ዓመታት ያህል በሰዩ ወረዳ ሹሻ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያንና በአጥቢያው የሚገኙ ምእመናን ከእናት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናቸው በመለየት የቆዩትን ሁለት ቀንደኛ የተሐድሶ መናፍቃን መሪዎች ተውግዘው መለየታቸውን አመለከተ፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ቢያደርገው የምንላቸው ነጥቦች
ጥቅምት 12 ቀን 2005 ዓ.ም.
ቅዱስ ሲኖዶስ ኤጲስ ቆጶሳት የያዘውን፣ የታወቀ ሕጋዊ መንበር፣ ታሪካዊና ሕጋዊ መሠረት እንዲኖረው ሆኖ የተደራጀውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምልዐተ ጉባኤ ነው፡፡ ይህ ምልዐተ ጉባኤ ለአንዲቷ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አንድነትና ልዕልና እጅግ አስፈላጊና አንድ ነው፡፡
አስፈላጊነቱም የሚመነጨውና የሚረጋገጠው በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ፣ የመንበረ ሐዋርያት ወራሽ በመሆኑና ውሳኔዎች ሁሉ ይግባኝ የሌለባቸው ከመሆኑ ላይ ነው፡፡ ሐዋርያት ከክርስቶስ፤ ሐዋርያነ አበውና ሊቃውንት ከሐዋርያት፣ እኛም ከእነዚህ ሁሉ የወረስናቸውን መሠረተ እምነት፣ ሥርዐተ አምልኮና ትውፊት የሚጠብቅና የሚያስጠብቅ ዐቃቤ ሃይማኖት ነው፡፡
ቤተ ክርስቲያንን ማገልግል አክራሪነት አይደለም !
መጽሔተ ተልዕኮን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
ማኅበረ ቅዱሳን በምድረ ከብድ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አንድነት ገዳም ያስገነባቸው ፕሮጀክቶች ተመረቁ፡፡
ጥቅምት 8 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
2ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጥናት መጽሔት ተመረቀ
ጥቅምት 8 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ማኅበሩ በሬድዮ ማሰራጫው ላይ የአየር ሞገድ ለውጥ አደረገ፡፡
ጥቅምት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ በማኅበረ ቅዱሳን ኅትመትና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ የሬድዮና ቴሌቪዥን ዝግጅት ክፍል ዘወትር አርብ ከምሽቱ 3፡30 እስከ 4፡30 ያሰራጭ የነበረውን ትምህርታዊ የሬድዮ ዝግጅት የአየር ሞገድ ለውጥ በማድረግ በ19 ሜትር ባንድ 15335 ኪሎ ኸርዝ አጭር ሞገድ አማካኝነት በተሻለ ጥራት ከጥቅምት 9/2005 ዓ.ም. ጀምሮ ማስደመጥ እንደሚጀምር በማኅበረ ቅዱሳን የሬድዮና ቴሌቭዥን ፕሮግራም […]
ከሰባት ሺህ በላይ በሌላ እምነት የነበሩ ሰዎች ተጠመቁ
ጥቅምት 8 ቀን 2005 ዓ.ም. በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ በደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ባሳለፍነው የ2004 ዓ.ም. ቁጥራቸው ሰባት ሺህ አንድ መቶ አርባ አንድ ሰዎች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ሃይማኖት በመቀበል መጠመቃቸውን የሀገረ ስብከቱ ሪፓርት አመለከተ፡፡ የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ትጉሀን ወንድወሰን ገ/ሥላሌ ለ31ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ ባቀረቡት ሪፓርት የሕግ […]
የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የከሰዓት በኋላ ውሎ
ጥቅምት 6 ቀን 2005 ዓ.ም. በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ 31ኛው የመንበረ ፓትርያርክ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ከዛሬው የከሰዓት በኋላ መርሐ ግብሩ ላይ የትግራይ ማእከላዊ ዞን፣ /የአክሱም/፣ የሲዳሞ፣ የሰሜን ጎንደር፣ የምሥራቅ ሐረርጌ፣ የጅማ ዞን፣ የመቀሌ ዞን፣ የኢሊባቡር፣ የድሬዳዋ፣ የጋሞ ጎፋ፣ የሰሜን ወሎ፣ የባሌ፣ የደቡብ ጎንደር የምሥራቅ ወለጋ፣ የአርሲ፣ የትግራይ ምሥራቅ ዞን /የአዲግራት/፣ አህጉረ ስብከቶች የበጀት ዓመቱን ሪፓርታቸውን […]