መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የሰው ሰውነት ክፍሎች
ነሐሴ 23 ቀን 2005 ዓ.ም.
በመ/ርት ኖኀሚን ዋቅጅራ
ባለፈው ግእዝን ይማሩ አምዳችን ላይ የግእዝ ቁጥሮችን አጻጻፍና የንባብ ስያሜአቸውን ማቅረባችን የሚታወስ ነው፡፡ ዛሬ ደግሞ የሰውነት ክፍሎችን ማቅረባችንን እንቀጥላለን፡፡
የሰውነት ክፍሎች፣ ከአንገት በላይ የአካል ክፍሎች፣ /ክፍላተ አካላት ዘላዕለ ክሳድ/
የአንገት በላይ የአካል ክፍሎች ማለት ከእራስ ፀጉራችን ጀምሮ እስከ አንገታችን ድረስ ያሉትን የአካል ክፍሎች ያካተተ /የያዘ/ ክፍል ማለት ነው፡፡ እነዚህንም የአካል ክፍሎች ከዚህ በመቀጠል እንመለከታለን፡፡
ሰብእ – ሰው
– ሰብእ ዘተፈጥረ እምነ ሠለስቱ ባሕርየተ ነፍስ ምስለ አርባዕቱ ባሕርያተ ሥጋ ውእቱ
ሰው የተፈጠረው ከሦስቱ ባሕርያተ ነፍስ እና ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ ነው፡፡
– ሠለስቱ ባሕርያተ ነፍስ ብሂል
ሦስቱ ባሕርያተ ነፍስ ማለት
፩. ሕያዊት – ሕዋሳትን የምታንቀሳቅስ ሕይወት ያላት
፪. ለባዊት – ልብ የምታደርግ /የምታስብ/
፫. ነባቢት – የምትናገር
ክርስትና “አክራሪነት”ን የሚያበቅል ነገረ ሃይማኖታዊ መሠረት የለውም
ነሐሴ 21 ቀን 2005 ዓ.ም.
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገራችን የሃይማኖት “አክራሪነት” ስጋት እንዳለ በተለያዩ ወገኖች የሚነሣ ሐሳብ አለ፡፡ የ “ሃይማኖት አክራሪነት” በሀገራችን የለም የሚል እምነት አይኖርም፡፡ “አክራሪነት” የሚተረጎመውም የራስን የሃይማኖት የበላይነት ለማስፈን ሲባል ሌላው የሃይማኖት ሐሳቡን እንዳይ ገልጥ፣ ተግባራዊ የአምልኮ ሥርዓቱን እንዳይፈጽም ማድረግ፣ በኃይል ወይም በዐመፅ ቦታ ማሳጣት ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ አንድ ቤተ እምነት ራሱ ከሚከተለው እምነት ውጪ ያሉ በቁጥር ትንሽ ወይም ብዙ ተከታይ ያሏቸው እምነቶች በአንድ ሀገር ወይም ቦታ መኖር የለባቸውም ብሎ ማመን ወይም ማድረግ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ይህ ደግሞ የሰዎችን የፈቃድ ነጻነት፣ ምርጫ አለማክበር፤ አለመጠበቅ ነው፡፡
የምሥጢር ቀን
ነሐሴ 13 ቀን 2005 ዓ.ም.
ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መላክ
በምዕ/ጐጃም ሀገረ ስብከት የ፬ቱ ጉባኤያት መምህር
በግብፅ አብያተ ክርስቲያናትና ክርስቲያኖች የጥቃት ሰለባ እየሆኑ ነው
ነሐሴ 11 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዝርወት ክፍል ሁለት
ሐምሌ 3 ቀን 2005 ዓ.ም
በዲ/ን ዶ/ር መርሻ አለኸኝ
ባለፈው ዕትማችን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ በዝርወት /ከኢትዮጵያ ውጪ/ ያደረገችውን ረዥም ሐዋርያዊ ጉዞ የሚዳስስ ጽሑፍ ማውጣታችን ይታወሳል፡፡ ቀጣዩን ደግሞ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡
2. አፍሪካ
የኢ.ኦ.ተ.ቤ. የጥቁሩን ሕዝብ መወከል የሚያስችላት ታሪካዊ አጋጣሚ ቢኖራትም ከዓለም ቀድማ በተመሠረተችበት አህጉር ለሚገኘው ሕዝቧ የሰጠችው አገልግሎት ሰፊ የሚባል አይደለም፡፡ እሷ አገልግሎት ባለመስጠቷ ጥቁሩ ሕዝብ ባሕሉና ልማዱ በፈጠረው ሀገረ ሰብአዊ እምነት ተይዞ ከአሚነ እግዚአብሔር ርቆ ለረጅም ዘመናት እንዲቆይ ሆኗል፡፡ አፍሪካውያን ከብዙ ሺሕ ዓመታት በኋላ ከኢትዮጵያ በእጅጉ ዘግይተው ወንጌልን የተቀበሉ አውሮ¬ውያን ያስተማሯቸውን ተቀብለዋል፡፡ ይልቁንም ቤተ ክርስቲያናችን ወደ ሕዝቡ መሔዷ ቀርቶ ራሱ ሕዝቡ እሷን ፈልጎ እንዲመጣ ኾኗል፡፡ በእርግጥ ቤተ ክርስቲያናችን ቀደም ባሉት ጊዜያት እስከ ሱዳንና ሱማልያ ተስፋ ፍታ እስልምና እስከሚቀማት ድረስ በርካታ አፍሪካውያንን በሃይማኖት ይዛ እንደቆየች የሚያስረዱ የታሪክ መዛግብት አሉ፡፡ ቤተ ክርስቲያኗ በአፍሪካ ያላት የሳሳ ታሪክ በአጭሩ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
የግእዝ ቁጥሮች አጻጻፍ
ሐምሌ 17 ቀን 2005 ዓ.ም.
በመ/ት ኑኀሚን ዋቅጅራ
የግእዝ ቋንቁ ጥንታዊያን ከተሰኙ ቋንቋዎች መካከል አንዱ ሲሆን ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት በቀን አቆጣጠርና በሥነ ጽሑፎቻቸው ሲጠቀሙበት ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፍ ቆይቷል፡፡ ዛሬም የግእዝ ቁጥሮች በኢትዮጵያውያን ዘንድ ሰፊ ሥፍራ አላቸው፡፡
በዚህ ዓምዳችን የግእዝ ቁጥሮችን አጻጻፍና የንባብ ስያሜአቸውን ማቅረባችንን እንቀጥላለን፡፡
የግእዝ ቋንቋ እንደ ማንኛውም ቋንቋ እራሱን የቻለ የቁጥር አጻጻፍ ስልቶች አሉት፡- እነዚህ ቁጥሮች እኛ በተለምዶ አጠራር የአማርኛ ቁጥሮች ብለን እንጠራቸዋለን፡፡ ይሁን እንጂ ትክክለኛውን አካሄድ ስንመለከት በአጠቃላይ የአማርኛ ብቻ ሳይሆኑ ልክ እንደ አማርኛ ፊደሎች ሁሉ ቁጥሮቹም መነሻቸው ግእዝ መሆኑን እንረዳለን፡፡
አቡነ ጎርጎርዮስ የሥልጠና ማእከል የበገና ተማሪዎችን አስመረቀ
ሐምሌ 17 ቀን 2005 ዓ.ም.
በታመነ ተክለ ዮሐንስ
ከፍተኛ ውጤት ለማስመዝገቤ ምስጢሩ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ መኖሬ ነው
ሐምሌ 5 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ሰሞኑን ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በመመረቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ ከተመራቂ ተማሪዎች መካከል ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ሁለት የወርቅ ሜዳልያዎች የተሸለመችውን
አንዲት እኅት ለዛሬ እንግዳችን አድርገናታል፡፡ አንዱን የወርቅ ሜዳልያዋንም “በግቢ ጉባኤ ውስጥ በመሳተፍ በመንፈሳዊ ሕይወቴ እንድበረታና ዓላማዬን እንዳሳካ እገዛ አድርጎልኛል” ለምትለው ማኅበረ ቅዱሳን በሥጦታ አበርክታለች፡፡ የዩኒቨርስቲ ቆይታዋን፤ በግቢ ጉባኤ ውስጥ ስለነበራት ተሳትፎ እና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ አነጋግረናታል፡፡ መልካም ቆይታ፡፡
ጥያቄ፡- ራስሽን ብታስተዋውቂን?
ፋንታነሽ ፡- ፋንታነሽ ንብረት እባላለሁ፡፡ የመጣሁት ከሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ሚዛን ግቢ ጉባኤ ነው፡፡ የተመረቅሁት አዲስ የትምህርት ዘርፍ በሆነው በኮፕሬቲቭ አካውንቲንግ /Cooprative Accounting/ በመጀመሪያ ዲግሪ ነው፡፡
ብዙ ከተሰጠው ከእርሱ ብዙ ይፈለግበታል
ሐምሌ 4 ቀን 2005 ዓ.ም.
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ቤተ ክርስቲያናችን ካሏት አህጉረ ስብከት ሁሉ ለየት የሚልበት ባሕርያት አሉት፡፡ ሀገረ ስብከቱ የሀገሪቱ ዋና ከተማ እንደመሆኑ በተለያዩ ምክንያቶች ከሁሉም አህጉረ ስብከት የሚመጡ ክርስቲያኖች አገልግሎት የሚያገኙባቸው ገዳማትና አድባራት ያሉበት ሀገረ ስብከት ነው፡፡ በተለያዩ ቋንቋዎች የሚናገሩ የተለያዩ ባህሎች ያሏቸው የቤተ ክርስቲያን ቤተሰቦች ተገናኝተው በአንድነት መንፈስ አገልግሎት የሚያገኙበትና የሚቀበሉበት ሀገረ ስብከትም ነው፡፡
ሀገረ ስብከቱ በርካታ የቤተ ክርስቲያናችን መምህራን ሊቃውንት የሚገኙበትም ሀገረ ስብከት ነው፡፡ በመንፈሳዊው ትምህርት ብቻ ሳይሆን በዓለሙ የሚሰጠውን ማኅበራዊና የተፈጥሮ ሳይንስ፣ የሙያና የቀለም ትምህርቶች የተማሩ አንቱ የተባሉ የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆችም የሚገኙበት ሀገረ ስብከት ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንን በታላቅ ፍቅር የሚጠብቃት፣ አገልግሎቷን ዕለት ዕለት የሚሻ ቸርና የዋህ ሕዝበ ክርስቲያን ያለበት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ቤተ ክርስቲያን የምትተዳደርበትን ብዙ የገንዘብ የቁሳቁስና የሰው ኃይል ሀብት ይዞ የሚገኝ ነው፡፡ ከዚህም የተነሣ አርአያነት ያለው አግልግሎትን ሊሰጥም እንደሚችል የሚታሰብ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዝርወት
ሐምሌ 3 ቀን 2005 ዓ.ም
በዲ/ን ዶ/ር መርሻ አለኸኝ
የዚህ ጽሑፍ ዓላማ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዝርወት /ከኢትዮጵያ ውጭ/ ያደረገችውን ረጅም ሐዋርያዊ ጉዞ በአጭሩ በመዳሰስ፤ ጉዞዋ ዛሬ የደረሰበትን ምዕራፍ መቃኘት ነው፡፡ የዛሬው ከታየ ዘንድ ግን ጽሑፉ በመጠኑም ቢሆን ጥናታዊ መልክ ይኖረው ዘንድ ዛሬ ቤተ ክርስቲያኗ በውጭው ዓለም ለምትሰጠው አገልግሎት እንቅፋት ናቸው ተብለው ሊጠቀሱ ከሚችሉ ችግሮች ዋና ዋና የሚባሉትን በማቅረብ የይሁንታ አሳብ ይሰነዝራል፡፡
ኢትዮጵያ እንደ ሀገር እምነትን በተመለከተ የግንኙነት መስመሯን ወደ ውጭ መዘርጋት የጀመረችው ቅድመ ክርስትና ከ1000 ዓ.ዓ. ገደማ ጀምሮ ነው፡፡ በቃልም በመጣፍም የቆየን የሀገራችን ወፍራም የእምነት ታሪክ እንደሚነግረን ንግሥተ ሳባ በሕገ ልቡና እግዚአብሔርን ሲያመልክ የነበረ ሕዝቧን በመወከል ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዛ ከንጉሡ ከሰሎሞን ጋር በመወያየት እግዚአብሔር ለእሱና ለሕዝቡ የገለጠውን ሕገ ኦሪት ይዛ ወደ አገሯ ተመልሳለች፡፡ ሕዝቧንም በዚሁ የኦሪት ሕግና እምነት እንዲመራ አድርጋለች፡፡ እሷ የጀመረችው ግንኙነትም በኋላ የመንፈሳዊ ጥበብ ፍለጋ ጉዞዋ ሌላ ውጤት በሆነው ልጇ ቀዳማዊ ምንልክና እሱ ባመጣቸው ሌዋውያን ካህናት አማካይነት ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡