መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ዐርባ ምንጭ ማእከል ተተኪ ሰባክያንን አስመረቀ
‹‹ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያትን በመላው ዓለም ዞረው ወንጌልን እንዲያስተምሩ እንደላካቸው ኹሉ፤ እናንተም በየአካባቢው ቋንቋ ወንጌልን በማስተማር አሕዛብን ከምእመናን ማኅበር እንድትጨምሯቸው አደራችንን እናስተላልፋለን፡፡››
የሊቀ ማእምራን ወመጋቤ ሐዲስ ወልደ ሰንበት ባይነሳኝ አጭር የሕይወት ታሪክ
በመምህርነት ከተመደቡበት ከ፲፱፻፸ ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዕለተ ሞታቸው ድረስ ትርጓሜ መጻሕፍትን በማስተማር በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር በልሉ ልዩ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ የሚገኙ በርካታ የቤተ ክርስቲያን መምህራንን አፍርተዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል ብፁዕ አቡነ ያሬድ እና ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስ ይጠቀሳሉ፡፡
ዘመነ ክረምት ክፍል ሁለት
ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹ወገብረ መብረቀ ለጊዜ ዝናም፤ መብረቅን ለዝናም ምልክት አደረገ፤›› በማለት እንደ ገለጸው መብረቅ በዝናም ጊዜ የሚገኝ ፍጥረት ሲኾን የሚፈጠረውም ውሃ በደመና ተቋጥሮ ወደ ላይ ከተወሰደ በኋላ በነፋስ ኃይል ወደ ምድር ሲወርድ በደመና እና በደመና መካከል በሚከሠት ግጭት አማካይነት ነው፡፡ ይህንን የመብረቅ አፈጣጠርም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በቅቤና በዐረቄ አወጣጥ ይመስሉታል፡፡
ተስእሎተ ቂሣርያ
ይህም ሥልጣነ ክህነት በቅዱስ ጴጥሮስ አንጻር ከሐዋርያት ጀምሮ ለሚነሡ አባቶች ካህናት የተሰጠ ሰማያዊ ሀብት ነው፡፡ ዛሬ ምእመናን በኀጢአት ስንሰናከል ከካህናት ፊት ቀርበን የምንናዘዘውና ንስሐ የምንቀበለው፣ እንደዚሁም እየተባረክን ‹‹ይፍቱኝ›› የምንለው ጌታችን ለእነርሱ የሰጣቸውን ሥልጣነ ክህነት መሠረት በማድረግ ነው፡፡
ፅንሰተ ማርያም ድንግል
‹‹ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ፤ ድንግል ሆይ በሥጋዊ ፈቃድ የተፀንሽ አይደለሽም፤ ሕጋዊ በኾነ ሥርዓት ከሐና እና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ›› /ቅዳሴ ማርያም/፡፡
ፅንሰተ ድንግል ወተስእሎተ ቂሣርያ
በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው ነሐሴ ፮ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም በነሐሴ ወር በሰባተኛው ቀን ከሚከብሩ በዓላት መካከል በዛሬው ዝግጅታችን የእመቤታችንን ፅንሰት እና ተስእሎተ ቂሣርያን የተመለከተ ጽሑፍ ይዘንላችሁ ቀርበናል፡፡ በመጀመሪያም ፅንሰተ ድንግል ማርያምን እናስቀድም፤ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ሲል በዕለተ ዓርብ በመስቀል ላይ የቈረሰውና ያፈሰሰው፤ እርሱን የበሉና የጠጡ ኹሉ መንግሥቱን የሚወርሱበት፤ ዘወትር በቤተ መቅደሱ የሚፈተተው ቅዱስ ሥጋውና […]
በፕሪንስተን ዩኒቨርሲቲ፣ በኖቲንግሃምና በጎንደር ከተሞች ዐውደ ጥናቶች ተካሔዱ
ነሐሴ ፬ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም በአሜሪካ፣ በአውሮፓና በጎንደር ማእከላት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማእከል በፕሪንስተን ዩኒቨርሲቲ ልዩ ዐውደ ጥናት እንደሚያካሒድ ሐምሌ ፮ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም ባወጣነው ዘገባ ማስነበባችን ይታወሳል፡፡ በዚህ መሠረት ማእከሉ ከፕሪንስተን ዩኒቨርሲቲ እና የሴሜቲክና የአፍሮ እስያ ከፍተኛ ምርምርና ጥናት ተቋም (The Institute for Advanced […]
ስለ ሀገራችን ወቅታዊ ሁኔታ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ
ነሐሴ ፫ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ‹‹ወሰላሙ ለክርስቶስ ይጽናዕ በልብክሙ ዘሎቱ ተጸዋዕክሙ በአሐዱ ሥጋ፤ በአንድ አካል የተጠራችሁለት የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይጽና፤›› (ቆላ 3÷15):: ይህ ቃል ሰው ሁሉ ለሰላም እንደተጠራ፣ ልቡንም ለሰላም ማስገዛት እንዳለበት ያስገነዝበናል፤ በእርግጥም ለሰው ከሰላም የበለጠ አስፈላጊ ነገር የለምና ለሰላም መገዛት ተገቢ ነው፡፡ ሰው ከሰላም ተጠቃሚ […]
ጾመ ፍልሰታ ለማርያም
ነሐሴ ፫ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው በነገረ ማርያም ተጽፎ እንደምናገኘው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጥር ፳፩ ቀን በ፵፱ ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ባረፈች ጊዜ ቅዱሳን ሐዋርያት ሊቀብሯት ወደ ጌቴሴማኒ ይዘዋት ሲሔዱ አይሁድ “እንደ ልጇ ተነሣች፤ ዐረገች እያሉ እንዳያውኩን በእሳት እናቃጥላት” ብለው በዓመፃ ተነሡ፡፡ ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊም አጎበሩን ይዞ ሊያወርዳት ሲል የእግዚአብሔር መልአክ […]
ቅዱስ ፓትርያኩ ጾመ ማርያምን በማስመልከት ቃለ ምዕዳን ሰጡ
ሐምሌ ፳፰ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ጾመ ማርያምን በማስመልከት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ የጠቅላይ ቤተ ክህነት፣ የማኅበረ ቅዱሳን፣ የመንግሥትና የግል መገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኞች በተገኙበት ሐምሌ ፳፰ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም በመላው ዓለም ለሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ቃለ ምዕዳን ሰጥተዋል፡፡ የቅዱስ ፓትርያርኩን […]