መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ነገረ ድኅነት በትንቢተ ነቢያት (ካለፈው የቀጠለ)
‹‹ፈኑ ብርሃነከ ወጽድቀከ እማንቱ ይምርሐኒ ወይሰዳኒ ደብረ መቅደስከ ወውስተ አብያቲከ እግዚኦ፤ ብርሃንህን እና ጽድቅህን ላክ፤ እነርሱ መርተው ወደ ቅድስናህ ተራራና ወደ ማደሪያህ ይውሰዱኝ፤›› (መዝ. ፵፪፥፫)
ነገረ ድኅነት በትንቢተ ነቢያት (የመጀመሪያ ክፍል)
እጅ ቢወድቁ ተመርጕዘው ይነሡበታል፡፡ እጅ የወደቀውን ንብረት ከአካል ሳይለይ ለማንሣት፣ የራቀውን ለማቅረብ፣ የቀረበውን ለማራቅ ይችላል፡፡ እግዚአብሔር ወልድም ከባሕርይ አባቱ ከአብ፣ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ ከእግዚአብሔር ርቆ የነበረውን አዳምን ወደ እርሱ አቅርቦታል፤ ከወደቀበት አንሥቶታል፡፡
ከሃያ አምስት በላይ የግብጽ ምእመናን በቦምብ ፍንዳታ ሕይወታቸው ዐለፈ
በፍንዳታው ሕይወታቸው ያለፈ ምእመናን ሥርዓተ ቀብርም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዎድሮስ ካልዕ መሪነት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና ብዙ ሺሕ የግብጽ ምእመናን በተገኙበት ታኅሣሥ ፫ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም በግብጽ ቅድስት ማርያም እና ቅዱስ አትናቴዎስ ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡
ዘመነ አስተምሕሮ (አስተምህሮ) ካለፈው የቀጠለ
ትምህርቶቹ የተለያዩ ናቸው ስንል የሚነገረው ምሥጢርና ይዘት በወቅታዊ በዓላት ላይ የሚያተኵር መኾኑን ለመግለጽ ነው እንጂ በየትኛውም ጊዜ በቤተ ክርስቲያናችን የሚቀርበው ትምህርት አንዱ የእግዚአብሔር ቃል ብቻ ነው፡፡
ዘመነ አስተምሕሮ (አስተምህሮ) የመጀመሪያ ክፍል
የአራቱ እሑዶቹ ስያሜ ከዐቢይ ጾም ሰንበታት ጋር ተመሳሳይ በመኾኑ መደናገራቸውን አንዳንድ ምእመናን ገልጸውልናል፡፡ እውነት ነው፤ የሰንበታቱ ስያሜ ከዐቢይ ጾም ሰንበታት ጋር ተመሳሳይ ይኹን እንጂ የሚዘመሩ መዝሙራት፣ በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ ምንባባትና የሚቀርቡ ትምህርቶች ግን ይለያያሉ፡፡
የጽዮን ምርኮ – የመጨረሻ ክፍል
ሜልኮል እስከ ዕለተ ሞቷ መካን ኾና እንደ ቀረች የእመቤታችንን ክብር የሚያቃልሉ መናፍቃንም የመንፈስ ቅዱስ ፍሬን ከማፍራት የመከኑ ናቸው /ገላ. ፭፥፳፪/፡፡
የጽዮን ምርኮ – ክፍል አራት
ወደ ታቦተ ጸዮን በመመልከታቸው ቤትሳምሳውያን ከተቀሠፉ አማናዊት ጽዮን በኾነችው በእመቤታችን ላይ እባብ ምላሳቸውን የሚያውለበልቡ መናፍቃንማ ዕድል ፈንታቸው ጽዋ ተርታቸው እንዴት የከፋ ይኾን!
ካህናተ ሰማይ
‹‹ካህናተ ሰማይ ቅዉማን በዐውዱ አክሊላቲሆሙ ያወርዱ ቅድመ መንበሩ እንዘ ይሰግዱ ይርዕዱ ወኢይዝብጦሙ ሶበ ይበርቅ ነዱ፤ ካህናተ ሰማይ (ሱራፌል) በመንበሩ ዙሪያ ቆመው በፊቱ ሲሰግዱ የመለኮት እሳት ሲበርቅ እንዳይመታቸው ይንቀጠቀጣሉ፤›› /መጽሐፈ ሰዓታት/፡፡
የጽዮን ምርኮ – ክፍል ሦስት
ታቦተ ጽዮን ዳጎንን እንደ ቀጠቀጠችው ዅሉ ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ዲያብሎስንና ሠራዊቱን ቀጥቅጧቸዋል፡፡ ታቦተ ጸዮን የወርቅ ካሣ ተሰጥቷት ከምድረ ፍልስጥኤም እንደ ወጣች ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በወርቀ ደሙ ካሣነት የሲዖልን ነፍሳት ከሲዖል አውጥቷል፡፡
የጽዮን ምርኮ – ክፍል ሁለት
በሐዋርያት እግር የተተኩ አባቶች ሊቃነ ጳጳሳትን እያቃለሉ ‹‹በቅዱስ ሲኖዶስ አንመራም፡፡ ቤተ ክርስቲያን አርጅታለች፤ እናድሳት፤›› በማለት በክርስቶስ ደም የተመሠረተች የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ዶግማና ቀኖና የሚጥሱ ራሳቸውን ‹‹ተሐድሶ›› እያሉ የሚጠሩ ምናምንቴዎች እጣ ፈንታቸው እንደ አፍኒንና ፊንሐስ ነው፡፡