መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት ያዳናቸው መልአክ ማን ነው? – ክፍል ሦስት (የመጨረሻ ክፍል)
ስለዚህ የሠለስቱ ደቂቅ ድኅነትን በተመለከተ በድርሳነ ሚካኤል ላይ ሚካኤል፤ በድርሳነ ገብርኤል ላይ ገብርኤል፤ በድርሳነ ሩፋኤል ላይ ደግሞ ሩፋኤል አዳናቸው ተብሎ መገለጹ ከላይ በወንጌል እንዳየነው ትውፊቱን ለያይቶ መዘገብ እንጂ ተቃራኒ ነገር አይደለም፡፡
ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት ያዳናቸው መልአክ ማን ነው? – ክፍል ሁለት
በዚህ በሠለስቱ ደቂቅ ድኅነት ውስጥ የታየው መገለጠጥ ዋነኛው ምሥጢርና መልእክትም የእግዚአብሔርን ሰው መኾንና አዳኝነት፤ እንደዚሁም እንደ ሠለስቱ ደቂቅ እሳትና ስለት፣ ሰይፍና ጐራዴ፤ እስራትና ግርፋት የሚቀበሉ ሰማዕታትን ዅሉ የሚያድናቸው እርሱ መኾኑን መግለጽ ነው፡፡
ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት ያዳናቸው መልአክ ማን ነው? – ክፍል አንድ
የማያመሰኳ እንስሳ የዋጠውን መልሶ እንደማያደቀው መልሶ መላልሶ እንደማያኝከው ዅሉ መናፍቃንም አንድ ጥቅስን በኾነ መንገድ ጐርሰው ከዋጡት በኋላ ምሥጢር አያመላልሱም፤ ደጋግመውም አያኝኩትም፡፡ ማለትም የሚመላለሱ ምሥጢራትን አያገኙም፤ አይመረምሩም፡፡
የአዳዲስ አማንያኑ ቍጥር ወደ ሰማንያ አምስት ሺሕ አደገ
‹‹አጥምቃችሁን መመለስ ብቻ ሳይኾን ለወደ ፊትም አስተማሪ፣ መካሪ ካህን አጥተን ወደ ሌላ ቤተ እምነት እንዳንወሰድ እየመጣችሁ በመምከር፣ በማስተማርና በማበረታታት በሃይማኖታችን እንድንጸና ድጋፍ አድርጉልን፤››
ነገረ ድኅነት በትንቢተ ነቢያት (ካለፈው የቀጠለ)
‹‹ፈኑ ብርሃነከ ወጽድቀከ እማንቱ ይምርሐኒ ወይሰዳኒ ደብረ መቅደስከ ወውስተ አብያቲከ እግዚኦ፤ ብርሃንህን እና ጽድቅህን ላክ፤ እነርሱ መርተው ወደ ቅድስናህ ተራራና ወደ ማደሪያህ ይውሰዱኝ፤›› (መዝ. ፵፪፥፫)
ነገረ ድኅነት በትንቢተ ነቢያት (የመጀመሪያ ክፍል)
እጅ ቢወድቁ ተመርጕዘው ይነሡበታል፡፡ እጅ የወደቀውን ንብረት ከአካል ሳይለይ ለማንሣት፣ የራቀውን ለማቅረብ፣ የቀረበውን ለማራቅ ይችላል፡፡ እግዚአብሔር ወልድም ከባሕርይ አባቱ ከአብ፣ ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ሳይለይ ከእግዚአብሔር ርቆ የነበረውን አዳምን ወደ እርሱ አቅርቦታል፤ ከወደቀበት አንሥቶታል፡፡
ከሃያ አምስት በላይ የግብጽ ምእመናን በቦምብ ፍንዳታ ሕይወታቸው ዐለፈ
በፍንዳታው ሕይወታቸው ያለፈ ምእመናን ሥርዓተ ቀብርም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዎድሮስ ካልዕ መሪነት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና ብዙ ሺሕ የግብጽ ምእመናን በተገኙበት ታኅሣሥ ፫ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም በግብጽ ቅድስት ማርያም እና ቅዱስ አትናቴዎስ ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡
ዘመነ አስተምሕሮ (አስተምህሮ) ካለፈው የቀጠለ
ትምህርቶቹ የተለያዩ ናቸው ስንል የሚነገረው ምሥጢርና ይዘት በወቅታዊ በዓላት ላይ የሚያተኵር መኾኑን ለመግለጽ ነው እንጂ በየትኛውም ጊዜ በቤተ ክርስቲያናችን የሚቀርበው ትምህርት አንዱ የእግዚአብሔር ቃል ብቻ ነው፡፡
ዘመነ አስተምሕሮ (አስተምህሮ) የመጀመሪያ ክፍል
የአራቱ እሑዶቹ ስያሜ ከዐቢይ ጾም ሰንበታት ጋር ተመሳሳይ በመኾኑ መደናገራቸውን አንዳንድ ምእመናን ገልጸውልናል፡፡ እውነት ነው፤ የሰንበታቱ ስያሜ ከዐቢይ ጾም ሰንበታት ጋር ተመሳሳይ ይኹን እንጂ የሚዘመሩ መዝሙራት፣ በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ ምንባባትና የሚቀርቡ ትምህርቶች ግን ይለያያሉ፡፡
የጽዮን ምርኮ – የመጨረሻ ክፍል
ሜልኮል እስከ ዕለተ ሞቷ መካን ኾና እንደ ቀረች የእመቤታችንን ክብር የሚያቃልሉ መናፍቃንም የመንፈስ ቅዱስ ፍሬን ከማፍራት የመከኑ ናቸው /ገላ. ፭፥፳፪/፡፡