ወርኃ ግንቦት
በቀደምት ዘመናት ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያን በተለይም ምእመናን ስለ ወርኃ ግንቦት (የግንቦት ወር) የነበራቸው አመለካከት የተሳሳት እንደነበር ታሪክ ያስረዳል፡፡ በዚያን ጊዜ ወቅቱ የተረገመ እንደሆነ በማሰብም ማንኛውንም ተግባር አይፈጽሙም ነበር። በዚህ ወቅት ነገሮች ሁሉ መጥፎ የመሆን ዕድል እንዳላቸው በማመን ምንም ዓይነት ምግባር አያከናውኑም፡፡ በርካቶችም የሚሠሩት ቤት ወይም የሚያስገነቡት ሕንፃ ፍጻሜው ጥሩ እንደማይሆንላቸው ያስቡ ነበር፡፡ ትዳር በግንቦት ወር የፈጸሙ ምእመናን ካሉ መጨረሻው እንደማያምር ያምኑም ነበር። ለዚህም አስተሳሰባቸው የሚያነሡት ሁለት ምክንያቶች የተሳሳቱ ናቸው፡፡…