‹‹ሞትን አትፍሩ፤ ኃጢአትን ፍሩ›› ቅዱስ ያሬድ
የሰው ዘር በሙሉ ምድራዊ ሕይወቱ የሚፈጸምበት ዕለተ ሞቱ በመሆኑ ከዚህች ዓለም ይለያል፡፡ ነፍሳችን ከሥጋዋ ስትለይም ሥጋችን ሕይወት አይኖረውምና በድን ይሆናል፤ ሥጋ ፈራሽ እና በስባሽ ስለሆነም ወደ መቃብር ይወርዳል፤ ይህም ሥጋዊ ሞት ነው፡፡ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ በሚል መጽሐፋቸው ‹‹መሞት፣ መለየት፣ በነፍስ ከሥጋ፣ በሥጋ ከነፍስ መራቅ፣ እየብቻ መሆን፣ መድረቅ፣ መፍረስ፣ መበስበስ፣ መነቀል፣ መፍለስ፣ መጥፋት፣ መታጣት›› ሲሉ ስለሞት አስረድተዋል፡፡ (ኪዳነ ወልድ፣ገጽ፣፭፻፹፩)