‹‹የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ ትወደኛለህን?›› (ዮሐ. ፳፩፥፲፭)
የዮና ልጅ ስምዖን በቤተ ሳይዳ ዓሣ አጥማጅ የነበረ ሰው ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተጠመቀበት ዕለት ማግሥት ከዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ አድርጎ መረጠው፤ ስሙም ጴጥሮስ ተባለ፡፡ ወንጌልን ይሰብክ እና ምእመናንም ይፈውስ ዘንድ ሥልጣንና ኃይልን የተሰጠው ቅዱስም ሆነ፡፡ የአስቆርቱ ይሁዳ ጌታን ለአይሁድ አሳልፎ እስኪሰጠው ድረስም ከእርሱ ጋር ኖሯል፡፡ ፍጹም ሃይማኖት፣ ለጌታውም ቅንዓት እና ፍቅርም ነበረው፡፡ (ስንክሳር ሐምሌ ፭)