‹‹እግዚአብሔር ግን ለዘለዓለም ይኖራል›› (መዝ.፱፥፯)

ዘመን የማይቆጠርለት፣ ዓለምን አሳልፎ የሚኖር፣ መጀመሪያና መጨረሻ የሌለው አምላካችን እግዚአብሔር ለዘለዓለም ይኖራል፡፡ በምድር ላይ ያሉ የምናያቸው አስደናቂና አስገራሚ የምንላቸው ነገሮች ሁሉ ያልፋሉ፡፡ እግዚአብሔር ግን እነዚህን ሁሉ አሳልፎ የሚኖር ዘለዓለማዊ አምላክ ነው፡፡‹ ‹‹እምቅድመ ዓለም ወእስከለዓለም ሀሎ እግዚአብሔር በመንግሥቱ፤ ዓለምን ከመፍጠሩ በፊት ዓለምን ከፈጠረ በኋላ ለዘለዓለም እግዚአብሔር በመንግሥቱ አለ›› እንዲል ቅዳሴ::

‹‹እግዚአብሔር ልቡናንና ኵላሊትን ይመረምራል›› (መዝ.፯፥፱)

ልበ አምላክ ነቢዩ ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር ልቡናንና ኵላሊትን ይመረምራል›› በማለት አስተምሯል፡፡ (መዝ.፯፥፱) ከዚህም ቃል እንደምንረዳው አምላካችን የሚሣነው ነገርም ሆነ ከእርሱ የሚሠወረውም ነገር እንደሌለ ነው፡፡ ሁሉንም ሳንነግረው የሚያውቅ አምላክ እንደሆነ ያሰብነውን ብቻም ሳይሆን ገና ያላሰብነውን እግዚአብሔር ያውቃል፡፡

ፈቃደ እግዚአብሔር

በሰዎች ሕይወት ውስጥ የእግዚአብሔር ክቡር ፍቃድ አለ፤ እነዚህም ሁለት ፍቃዳት ናቸው፡፡ አንደኛው ግልጽ ፈቃድ ሲባል ሁለተኛው ደግሞ ስውር ፈቃድ ይባላል፡፡ ግልጽ ፍቃዳት የሚባሉት በመጽሐፍ ተጽፈው የምናነባቸው ናቸው፤ በሕግ መልክ በብሉይ እና በሐዲስ ኪዳን የተቀመጡልን ትእዛዛቱ እንድንሰማቸው፣ እንድንማራቸው፣ እንድንኖራቸው የተሰጡትን ነው፡፡ መጽናናትን፣መረጋጋትን ገንዘብ የምንዳርባቸው፣ ተግሣጽንና ምክርን የምንሸምትባቸው ገባያችን ናቸው፡፡

‹‹እግዚአብሔር ከእኛ በላይ ለእኛ ያውቃል›› (ሮሜ ፷፥፳፯)

ሰዎች በሕይወት ዘመናችን ውስጥ በሁለት ነገሮች ታጥረን እንጸልያለን፤ እንሠራለን፤ እንኖራለን፡፡ ሁለቱ ነገሮችም እኛ የምንፈልጋቸውና የሚያስፈልጉን ናቸው፡፡ እነርሱንም ይዘን ከእግዚአብሔር ፊት በመቆም የሚያስፈልገንን ነገር እንጠይቀዋለን፡፡ ነገር ግን የፈለግነውን ወይም የጠየቅነውን ሁሉ ሳይሆን የሚያስፈልገንን አምላካችን ለእኛ ያደርግልናል፤ ወይም ይሰጠናል፡፡

‹‹እናት ልጇን እንደምታጽናና እንዲሁ አጽናናችኋለሁ››(ኢሳ.፷፮፥፲፫)

የእግዚአብሔር ነቢይ ኢሳይያስ በዚያን ዘመን ይኖሩ ለነበሩት እስራኤላውያን እንዲናገር በታዘዘው መሠረት ይህን ቃል ነገራቸው፤ ‹‹እናት ልጇን እንደምታጽናና እንዲሁ አጽናናችኋለሁ፡፡›› (ኢሳ.፷፮፥፲፫) ከነበሩበት መከራና ከጭንቀታችው ሁሉ እንደሚያጽናናቸው እግዚአብሔር አምላክ በነቢዩ አማካኝነት ተስፋ ሰጣቸው፡፡ ነገር ግን ይህ ቃል በዚያን ዘመን ላለው ሕዝብ ብቻ የሚያልፍ ሳይሆን ዛሬ ያለነውም ትውልድ በተለይም እኛ ልናስተውለው የሚገባ ቃል ነው፡፡

ዐራቱ የእግዚአብሔር ሠራዊት

‹‹በእግዚአብሔር ዘንድ ዐራት ሠራዊት አየሁ፡፡ ሰባቱ ነጎድጓድ በተናገሩ ጊዜ ልጽፍ አሰብሁ፤ ከሰማይም ‹ሰባቱ ነጎድጓድ የተናገሩትን ነገር በማኅተም ዝጋው፤ አትጻፈውም› የሚል ድምጽ ሰማሁ››፤…

‹‹በገሊላ አውራጃ በቃና መንደር ሠርግ ሆነ፤ ውኃውንም ወደ ወይንነት ለወጠው›› (ዮሐ. ፪፥፩-፲፩)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም እና ከቅዱሳን ሐዋርያቱ ጋር በመሆን በገሊላ አውራጃ በቃና መንደር በሠርግ ቤት ተገኝቶ ቤተ ከብካቡን በትምህርቱ በተአምራቱ ባረከ።በጥምቀት በዓል ማግስት ጥር ፲፪ ቀን ይህንኑ ጠብቀን በዓሉን እናከብራለን፡፡

‹‹ሁል ጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ›› (ፊልጵ.፬፥፬)

ከመከራው በላይ የእግዚአብሔርን ቸርነት እያሰበ የሚያመሰግን ሰው፥ ዘወትር ደግሞ ከመንፈስ ቅዱስ የተነሣ ደስተኛ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ እስር ቤት ሁኖ በደቀ መዝሙሩ በአፍሮዲጡ አማካኝነት በወንጌል ለተከላቸው ተክሎች ምእመናን በላከላቸው መልእክት እንዲህ ይላቸዋል፦ ‹‹ሁል ጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፥ ደግሜ እላለሁ ደስ ይበላችሁ!›› (ፊልጵ.፬፥፬)

በጎ ኅሊና

በዓለም የምናያቸው መልካምም ሆኑ ክፉ ነገሮች ሁሉ መነሻቸው ሐሳብ መሆኑን ስናስተውል ኅሊና ምን ያህል ታላቅ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ኅሊና የሚለው ቃል ‹ሐሳብ፣ ምኞት፣ ከልብ የሚመነጭ ሐሳብ› ማለት ነውና፡፡ በሰው ልጆችም የአእምሮ ሥራ ሂደት ውስጥ ሐሳብ ሲደጋገም ወደ አመለካከት፣ ከሐሳብ የተነሣ አመለካከት ሲያድግም ክፉ ወይም በጎ ወደ ሆነ ማመን፣ አንድ ሰው ከሐሳቡ ወደ ማመኑ የደረሰበት መንገድም ማንነቱን እንደሚወስኑት ባለሙያዎች ያስተምሩናል፡፡ ከሐሳባችን ተነሥቶ ወደ ማንነታችን የደረሰ ነገርም ፍጻሜያችንን ይወስነዋል፡፡…

ጸሎት በቤተ ክርስቲያን

የተወዳዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች! እንደምን ሰነበታችሁ? እግዚአብሔር ይመስገን አላችሁ? መልካም፤ እግዚአብሔር አምላካችን የተመሰገነ ይሁን፡፡ በቤታችሁ ሆናችሁ ትምህርታችሁን በጥሞና ተከታተሉ!