እስራት
ሰዎች በልዩ ልዩ ምክንያቶች በወኅኒ ቤት ይታሰራሉ፡፡ አንዳንዶች ወንጀል ፈጽመው፣ ያልታረመ ንግግር ተናግረው፣ በማታለል ተግባር ተሰማርተው፣ ሴት አስነውረው፣ ቤት ሰርስረውና የመሳሰሉትን እኩይ ተግባራትን ፈጽመው ሊሆን ይችላል፡፡ የሰው ልጆችም በሲኦል ወኅኒ ቤት ተጥለን ለአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመናት ስንሠቃይ የነበረው አባታችን አዳም ትእዛዘ እግዚአብሔርን ጥሶ፣ አምላክነትን ሽቶ፣ አትብላ የተባለውን በመብላቱ ነበር፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ይህን አስመልክቶ ሲናገር ‹‹በሥጋ ሞተ በመንፈስ ግን ሕያው ሆነ በእርሱም ደግሞ ሄዶ በወኅኒ ለነበሩት ነፍሳት ሰበከላቸው›› ይላል፡፡ (፩ኛጴጥ.፫፥፲፱)