“የእኛ ግዴታ ሲኖዶስ ያወጣውን ሕግ ማስከበር ነው” ሊቀ ኅሩያን ዓለም እሸት ገ/ጻድቅ
ባለፈው ጊዜ በሐዋሳ ከተማ በተለይም በደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የተፈጠሩትን ጉዳዮች አስመልክቶ ከሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ዓለም እሸት ገ/ጻድቅ ጋር ያደረግነውን ውይይት የመጀመሪያ ክፍል የሐዋሳ ጉዳይ 1 በሚል ርዕስ አቅርበንላችሁ ነበር። የውይይታችን ቀጣይ ክፍል ደግሞ እነሆ፤ መልካም ንባብ። (ፎቶ፦ ሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ግቢ ውስጥ ከሚገኙት ጥቅሶች መካከል)
• በብፁዕነታቸው መልካም ፈቃድና በሀገረ ስብከቱ ጥረት እርቅ እንደተካሄደ ይታወቃል። የእርቁ ሂደት እንዴት ነው? ከእርቁ በኋላ አለመግባባቶች እንዴት ሊፈጠሩ ቻሉ?
እንግዲህ በኛ በኩል እርቁ አልፈረሰም እንደተጠበቀና እንዳለ ነው፡፡ የዕርቅ ስምምነት የተባለው፤ የተጣላ ኖሮ አንተ ይህን አድርገሀል አንተ ይህን አድርገሀል ተብሎ እርስ በእርሱ የተጣላ ኖሮ አይደለም። ዋናው የቤተ ክርስቲያኒቱ መመሪያና ደንብ አልተከበረም ነው፡፡ ይህንን በሚመለከት በመንግሥት አካላት በኩልም የቤተ ክርስቲያኒቱን ደንብና መመሪያ እንዲያውቁት፥ ግንዛቤ እንዲኖር፥ በታዛቢነትም ተገኘተው ደግሞ የራሳቸውን ሀሳብና አስተያየት እንዲለግሱን አድርገናል። ይህን ከማድረግ አኳያ ከሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል ማለትም ከአገር ሽማግሌዎች፣ ከሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፣ ከሰበካው ጉባኤውና ከልማት ኮሚቴ ከሚመለከታቸው ክፍሎች ሁሉ የተውጣጡ አካላት ባሉበት፥ ከመንግሥት አካላትም በታዛቢነት አድርገን ባለ ሰባት ነጥብ የያዘ የእርቅ ሰነድ ወይም ውሳኔ የሚባለውን ያዘጋጀነው፡፡
ውሳኔውና የእርቅ ሰነዱ ብዙ ነገሮች ሲኖሩት ሌላው ሁሉ እንዳለ ሆኖ፥ ጠቅለል ባለ መልክ ሁሉም ነገር በቃለ አዋዲው እና በቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግና መመሪያ መሠረት እንዲሠራ የሚል ነው፡፡ በተለይ ደግሞ በእርቅ ሰነዱ ሰባተኛው እና የመጨረሻው ተራ ቁጥር ላይ ሰባክያንና ዘማርያንን የተመለከተ ነው፤ አብዛኛውን ጊዜ ችግር የሚያመጣውና አለመግባባት የሚያስከትለው ጉዳይ እሱ ነው፡፡ ምክንያቱም ሰዎች ይነሳሱና እነ እከሌ መስበክ አለባቸው ይላሉ፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱ አስተዳደርና አካሄድ ደግሞ ይህን አይፈልግም፥ ስለዚህ አሁን እገሌ ይስበክ እገሌ አይስበክ ሳይሆን፥ የሚሰብክ ሰው በቤተ ክህነቱ ሕጋዊ እውቅና ኖሮት ይስበክ የሚል ነው፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ምሳሌው አይሄድም እንጂ ፈቃድ ሲባል እንደ ንግድ ፈቃድ ወይም እንደ ቀበሌ መታወቂያ አንድ ጊዜ የሚሰጥ አይደለም። አንድ ጉባኤ፣ ክብረ በዓል ሲኖር ወይም ወደ አንድ ቦታ ላይ ተጉዞ የወንጌል ማስተማር ጉባኤም ካለ፥ ለዚያ ጉባኤ እገሌ የተባለ ሰባኬ ወንጌል ወይም መምህር እንዲያስተምር የሚል ደብደቤ መኖር አለበት ነው፡፡ ያን ደብዳቤ የሚጽፈው ደግሞ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ወይም ደግሞ የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤቱ ሊሆን ይችላል። በዚህ መልኩ ነው ሥራው መሠራት ያለበት፡፡ እነዚህን የመሳሰሉት ውሳኔዎች በእርቅ ሰነዱ ላይ ተካተው ከክልሉ መስተዳድር ጀምሮ ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ተላልፏል፤ የመንግሥት አካላትም በታዛቢነት በተገኙበት ሕጉን አስረግጠን ነግረን በግልጽ በጉባኤ ተነቧል። በተለይም ሰባክያንን፣ ዘማርያንን፣ ባሕታውያንንና የመሳሰሉትን በሚመለከት ቅድም እንዳልኩት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ፊርማ ለመላው አህጉረ ስብከት የተላለፈው መመሪያ በሚገባ ተነብቦ፣ ተገለጾ፣ ታይቶ መመሪያው ተጠብቆ በሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት እንዲሠራ፤ እንዲሁም በተለይ በሀገረ ስብከቱ ክልል ባሉ አብያተ ክርስቲያናት ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ወይም ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ያልተፈቀደለት አካል በቤተ ክርስቲያኒቱ አውደ ምሕረት ሲቆም ሀገረ ስብከቱ ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርግ የሚል ሰፍሯል። ስለዚህ የእኛ ትግል የሲኖዶስን መመሪያ ተግባራዊ ለማድረግ ነው ማለት ነው። በዚያ መሠረት ነው የምንሠራው። የእርቅ ሰነዱ ውሳኔ ከተላለፈ በኋላም ምንም ዓይነት ጭቅጭቅም ሁከትም አልነበረም።
ከጊዜ በኋላ እንግዲህ አሁንም ሰዎች እነ እገሌ የሚባሉት ሰባክያን ይምጡ፣ ዘማርያን ይምጡ፣ እነ እገሌ ይምጡ ማለት ጀመሩ። ቤተ ክህነቱ ደግሞ በሕጋዊ መንገድ ፈቅዶ የሚልካቸው መምህራንና ሰባኪያን አሉ፡፡ ሰዎችን ይምጡልን ቢሉም ቤተ ክህነቱ ደግሞ እኔ እነዚህን ነው የማሰማራው ብሎ ልኳል፡፡ ሀገረ ስብከቱ እንደ ተዋረድ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የሚተላለፍለትን መመሪያ የመፈፀምና የማስፈጸም ግዴታ አለበት፡፡ ይሄ ለምን ሆነ? ይሄ አይሆንም ማለት ሕጉም ሥርዓቱም አያስኬድም። በዚህ ምክንያት እንግዲህ እነ እገሌ ካልሰበኩ ወይም እኛ ካልሰበክን በሚል አንዳንድ ሰዎች ተነሥተዋል፡፡ ያው እነዚያ በግል ማለት ነው፡፡ አሁንም ግን የመላው ምእመንና ካህናቱ አመለካከት የውሳኔ ሰነዱ፣ ቃለ ዐዋዲው ይከበር፤ ለሀገረ ስብከቱ አቅርቦ ሲፈቀድለት ይሰማራ ነው፡፡ ይሄንን ሳያቀርቡ ደግሞ እራሳችንን እናሰማራ የሚሉ ክፍሎች ሲነሱ፤ ይሄ አይሆንም፥ ይሄ መደረግ የለበትም በሚል ነው አለመግባባቱ የተፈጠረው፡፡ ከዚህ አንጻር ነው እንጂ እርቅ የፈረሰ ነገር የለም እርቁም ደግሞ የቤተክርስቲያኒቱን መመሪያ ጠብቀን እንሂድ፤ ሁላችንም ለቤተ ክርስቲያንቱ መመሪያ ተገዥ እንሁን የሚል ውሳኔ ነው እንጂ እገሌና እገሌ ተጣልተው የሚል የግል ጥላቻ በዚህ ላይ የለውም፡፡ የቤተ ክርስቲያንኒቱን መመሪያ ግን በጋራ እናክብር፡፡ መንግሥትም መመሪያውንም ውሳኔውንም አውቆታል፤ ይሄ ውሳኔ ለብፁዕ ቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት፣ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት፣ በጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብከተ ወንጌልና ሐዋሪያዊ ተልእኮ መምሪያ በግልባጭ ደርሷል። በቃ ያንኑ የነበረውን መመሪያና ሕጉን የሚያጸና እንጂ የተለያየ ነገር የለውም። ይሄ ከተባለ በኋላ ግን አሁንም ሰዎች እንደግል ፍላጎታቸው እንዲህ ካልሆነ የሚሉ ሲነሱ አይ ይሄማ ከሕግ ውጪ ነው የሚል ነው ያለው ማለት ነው እንጂ የእርቅ መፍረስ አይደለም።
• ታዲያ ከዚህ ውሳኔ በኋላ አለመግባባቶችና ግጭቶች አልተነሱም ብለው ያስባሉ?
እንግዲህ አንዳንድ ሰባክያን እኛ እንሰብካለን፣ እኛ እንዲህ እናደርጋለን ብለው የሚሉት አብዛኛውን ወሬው የሚወራው በውጪ ነው፡፡ አንዳንዴ ግን ያልተፈቀደላቸው ሰዎች ወይም ያልተመደቡ ሰባክያን ወይም ቤተ ክህነቱ ያላሰማራቸው ዘማርያን ሆኑ ሰባክያን ወደ ዐውደ ምሕረቱ ሲመጡ፥ የለም፤ ይሄ አይደለም፤ ይላል ምእመኑ። ምእመኑ ነው መመሪያውን የሚያስከብረው። ይሄ ሰባኪ አይደለም የተመደበው ይላል። በዚህ ጊዜ የግድ አለመግባባቶች ይመጣሉ።
ሕጉ፣ መመሪያው፣ የሲኖዶሱ ደንብ፣ ቃለ አዋዲውና ሕገ ቤተ ክርስቲያኑ በአግባቡ በሥራ ላይ ይዋል ሲባል፥ የለም እኛ በፈቀድነው መሆን አለበት የሚሉ ክፍሎች ደግሞ ከተነሱ፥ ይኼማ የቤተ ክርስቲያናችን መመሪያዋ አይደለም የሚሉ ክፍሎች ይነሳሉ። በዚህ ጊዜ መቼም የሀሳብ አለመጣጣም አለመግባባት ግድ ይከሰታል። ያን ሲሆን ደግሞ ችግር ሊፈጠር ይችላል። ነገር ግን ያው ዞሮ ዞሮ ችግሮች ሲፈጠሩ በመንፈሳዊነት ሚዛን ይታያል። እንደ ሕግ የሚታየው ደግሞ በሕግ ይታያል። በዚህ ዓይነት ታይቶ እልባት እንዲያገኝ ይደረጋል፡፡
• በሀገረ ስብከቱ በኩል የወደፊት ዕቅዳችሁ ምንድን ነው?
እንግዲህ ለወደፊቱ እግዚአብሔር ፈቃዱ ቢሆን ከፍተኛው ሥራ ያለው ከታች ስለሆነ ያለው 13ቱንም የወረዳ ቤተ ክህነቶች በተሻለ መልኩ በተሟላ የሰው ኃይል የማጠናከር፥ ባለፈው ለወረዳ ሊቃነ ካህናት፣ ለርእሰ ከተማው አድባራት አስተዳዳሪዎችና ሰበካ ጉበኤያት በተቻለ መልኩ ትምህርታዊ ሴሚናር ለመስጠት ተሞክሯል። በቀጣይነት ደግሞ በሂደት ለእያንዳንዱ ወረዳ ቤተክህነት መርሐ ግብር ወጥቶ፥ በወረዳው ሥር ያሉ አብያተ ክርስትያናትን፣ የአብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎችን፣ የሰበካ ጉባኤ አባላትን፣ ሰባክያነ ወንጌልና ካህናትን አሳታፊ ያደረገ፥ የቃለ ዐዋዲውን መመሪያና ሕገ ደንብ በተመለከተ፣ የቃለ ዐዋዲውን ሕግና ደንብ በማይነካ መልኩ ቤተ ክርስቲያኒቱ በልማትና ሁለንተናዊ ሥራዎች ላይ ማከናወን ያለባትና ዘመኑን የተከተለ ዘመናዊ አስተዳደርና የሥራ ሁኔታዎችን በሚመለከት፥ እንደዚሁም ደግሞ የበጀትና የሂሳብ አያያዝ፣ የንብረት ጥበቃና አመዘጋገብን፣ የቅርሶች ምዝገባንና የመሳሰሉትን ሁሉ በየጊዜው ተከታታይ ስብሰባዎችን በማድረግ ሴሚናሮችን መስጠት አስበናል።
በወረዳ ደረጃ የተሰጠው ሴሚናር በአጠቢያው ሥር ላሉ ደግሞ ካልተሰጠ ሥራው ሁለት ዓይነት ስለሚሆን በየወረዳው ሥር ያሉትን አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናትን በየወረዳው ርእሰ ከተማ አቅም በፈቀደ መጠን ሴሚናሩ እዚያ ደርሶ ይህንን ሥልጠና መስጠት የመጀመሪያ እቅዳችን ነው፡፡
ከዚሁ ጋር ደግሞ ያው በሀገረ ስብከቱ ሥር በሚተዳደረው የደ/ታ/ቅ/ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን አጠገብ የካህናት ማሠልጠኛ ትምህርት ቤት አለን። በዚህ የካህናት ማሰለጠኛ ትምህርት ቤት ያለንን በጀት በመጠቀም ካህናትን እናሠለጥናለን። የሠለጠኑት ካህናትም ወደ ነበሩበት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት እየተመለሱ ምእመናኑን በስብከተ ወንጌልና በመሳሰለው ሁሉ እንዲያገለግሉ የማድረጉን ሥራ አጠናክረን እንቀጥላለን።
እንግዲህ ደቡብ ክልል ወደ 56 የሚጠጉ ብሔር ብሔረሰቦችን ያቀፈ ክልል ነው። የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች ተወላጅ የሆኑ እና የየብሔረሰቡን ቋንቋ የሚናገሩ የተወሰኑ ሕፃናትን በማሰባሰብ ለማስተማር ጥረት እያደረግን ነው። ለምሳሌ አሁን 12 ያህል ህፃናት አሉን። ሀገረ ስብከቱ ከኛ ቀደም ብሎ ወደዚሁ ማሠልጠኛ አምጥቶ ትምህርት ቤት ከፍቶ፥ መንፈሳዊውን ትምህርት ማለትም ከፊደል ቆጠራ ጀመሮ እስከ ሥርዓተ ቅዳሴ ሌላም ሌላም የመሳሰሉትን መንፈሳዊ ትምህርት እያስተማረ አሁን ለዲቁና የሚያበቃ ትመህርት ተምረው የሚገኙና በቅዳሴ አገለግሎት ላይ የሚገኙ አሉ። እነዚህ ልጆች ለጊዜው ቁጥራቸው 12 ቢሆንም ይሄ 12 የሆነው ቁጥር ወደ 24 ወደ 36 ብሎም ወደ 72 እንዲያድግ ቁጥሩ እየጨመረ የሚሄድበትን መንገድ ለመፍጠር ጥረት ይደረጋል።
እነዚህ ልጆች ደግሞ ከየብሔረሰቡ የተወጣጡና የየብሔረሰቡን ቋንቋ የሚችሉ እንደ መሆናቸው መጠን ወንጌልን በየቋንቋቸው ለማስተማር ይረዳቸዋል። ኅብረተሰቡም ይቀበላቸዋል። ከመንፈሳዊው ትምህርት ጎን ለጎን ዘመናዊ ትምህርትም እየተማሩ ነው። ይሄን በሚማሩ ጊዜ አንዳንድ በጎ አድራጊዎች ከሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር የሚቻለውን ድጋፍ በማድረግ ቀለባቸውን፣ ልብሳቸውን የትምህርት ቁሳቁስና የመሳሰሉትን ወጪ አድርጎ ዘመናዊውን ትምህርት ያስተምራቸዋል፡፡ ከመንፈሳዊውና አለማዊው ትምህርታቸው በተጨማሪ በቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን ደግሞ በዲቁና ያገለግላሉ። ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን፣ እንዲሁ አገለግሎትንም በኪዳንና በመሳሰለው እየተለማመዱትም ይገኛሉ ማለት ነው።
የነዚህ ልጆች ወደዚህ ማሠልጠኛ ገብቶ የማደግና የመማሩ ጉዳይ በብፁዕነታቸው ትኩረት ተሰጥቶበታል። እንግዲህ ይህን ሥልጠና ለማድረግ ቁጥራቸውንም ለመጨመር በጀት ያስፈልጋል፤ ሥራዎች ሁሌም የሚሠሩት በበጀት ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን በጀቷ ምእመናን ናቸው፡፡ በዚሁ በሐዋሳ ያሉ አንዳንድ ምእመናን ለልጆቹ የተቻላቸውን ያህል የሚያደርጉ አሉ። ወደፊት ደግሞ ፕሮፖዛል ቀርፀን፣ እቅድ አውጥተን፣ በጎ አድራጊዎችንም በማስተባበር፣ እርዳታ ሰጪ ክፍሎችንም በማፈላለግ ለመንቀሳቀስ አስበናል። ማኅበረ ቅዱሳንም በዚህ በኩል ይረዳናል የሚል ተስፋ አለን። እንዲሁም ማሠልጠኛው ራሱን ችሎ እንዲንቀሳቀስ የልማት ሥራዎችን በፕሮጀክት ቀርፀን ለመሥራት አስበናል። እንዲህ ዓይነት ሥራዎችን የምናከናውነው የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት እስከ ገጠሪቱ ቤተ ክርስቲያን ያለው በቃለ አዋዲው ድንጋጌ የሠፈረው የሥራ እንቅስቃሴ እንዳለና እንደተጠበቀ ሆኖ ማለት ነው፡፡ ያኛው እንዳለና እንደ ተጠበቀ ሆኖ ሌላው እቅዳችን ደግሞ በተለይ በቤተ ክርስትያኒቱ ተተኪ ትውልድ የመፍጠርና የመተካት፥ የዛሬው ትውልድ የነገይቱ የቤተ ክርስቲያን ተረካቢ እንዲሆን የማስቻል፥ የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልግሉት በጥንካሬና በስፋት ቀጣይነት እንዲኖረው የማድረግ፥ ለነገይቱ ቤተ ክርስቲያን በትምህርት ሰዎችን የማዘጋጀት እና ተተኪዎችን የማፍራቱን ጉዳይ ከምንግዜውም የበለጠ አቅም በፈቀደ መጠን አጠንክረን ለመሥራት ነው፡፡
• በመጨረሻ የሚያስተላለፋት መልእክት ካለ?
እንግዲህ በሲዳማ አማሮና ቡርጂ ልዩ ዞኖች እና ወረዳዎች ሀገረ ስብከት ለሚገኙ ለመላው ካህናትና ምእመናን በሀገረ ስብከታችን ጽ/ቤት ስም የማስተላልፈው መልእክት፤ አሁንም የቤተ ክርስትያኒቱን ሁለንተናዊ መንፈሳዊ፣ የልማት እና የሥራ እንቅስቃሴ ተባብረን ሁሉንም ለማከናወን እንድንችል መላው ምእመናን እና ካህናት የቅዱስ ሲኖዶሱን ውሳኔ እና መመሪያ፥ የቃለ አዋዲውን ድንጋጌ እና ደንብ ጠብቀን ቤተ ክርስቲያኒቱ በቅዱስ ሲኖዶስ አማካኝነት በተዋረድ በምታስተላለፍልን መሠረት ሕጓን ጠብቀን አክብረን ተባብረን እንድናገለግልና እንድናስገለግል ነው። ወደ ፊት ስብከተ ወንጌል እንዲስፋፋ፥ ሰንበት ትምህርት ቤቶች እንዲጠናከሩና ቤተ ክርስቲያናችን በልማት ልትጠናከር ያስፈልጋል።
ምእመናን ደግሞ በዕውቀታቸው በገንዘባቸውና በጉልበታቸው አብያተ ክርስቲያናትን በማስፋፋት፣ በማሳነጽና በማሠራት እንዲተጉ አሳስባለሁ። ሀገረ ስብከቱም ጠቅላላ ሥራውን የሚያከናውነው ከካህናትና ምእመናን ጋር ነውና፥ ካህናቱም ስብከተ ወንጌልን በማስፋፋት፥ መንፈሳዊ አገለግሎትን አጠናክሮ በመቀጠልና ልማትም በቤተ ክርስቲያን እንዲስፋፋ በማድረግ ሊተጉ ይገባል። ምእመናኑ እውነት በመንገር ማሳሰብ ብቻ ነው የሚፈለጉት። በእውነት ይሄ ቀረ የማይባል ከፍተኛ ሥራ የሚሠሩ በርካታ ምእመናን አሉ። በእውነት ከተነገረና ካሳሰቡአቸው፥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ለቤተ ክርስቲያናቸው ወደኋላ የሚሉበት አንድም ነገር የለም። ስለዚህ ከኛ የሚጠበቀው መንገርና ማስረዳት ብቻ ነው። እኛም የሚቻለንን ያህል እግዚአብሔር እንደፈቀደ ለማስረዳት ለመንገር እንሞክራለን። አሁንም እየነገርን እያሳሰብን ነው፤ ምዕመናኑም እየሰሙን ነው፡፡ ስለዚህ መላው ምእመናንና ካህናት ተባብረን ስብከተ ወንጌሉንም እንድናስፋፋ አብያተ ክርስቲያናቱንም በልማት እንድናጠናክር እላለሁ። የሁሉም ምእመናንና ካህናት ከሀገረ ስብከቱ ጋር መተባበር አስፈላጊ ስለሆነ እስከ አሁን ያለውን ቀና ትብብራቸውን አጠናክረው አንዲቀጥሉ በሀገረ ስብከቱ ጽ/ ቤት ስም መልእክቴን አስተላልፋለሁ፡፡
• በእውነት ጊዜዎን ሰውተው ለሰጡን ቃለመጠይቅ በእግዚአብሔር ስም እናመሰግናለን፡፡
እንግዲህ ከመጣን አጭር ጊዜ ቢሆንም ከሞላ ጎደል ያለውንና እንዲሁም ለወደፊት ያለውንና ለመሥራት የታቀዱትን እኔ የሚቻለኝን ያህል ብያለሁ፤ ብፁዕ አባታችን አቡነ ገብርኤል ደግሞ በአባትነታቸው በሀገረ ስብከቱ ያለውን ሁኔታ አስፍተው አምልተው ከኔ የበለጠ አድርገው፥ እኔ ምናልባት ያተረፍኩትም ያጎደልኩትም ካለ የበለጠ ብፁዕነታቸው አርመው አስተካክለው አስፍተው በጥሩ ቋንቋ በጥሩ ሁኔታ ለትውልዱ በሚመች መልኩ ይገለፁታል። እኔም በሀገረ ስብከቱ ስም ምስጋናዬን አቀርባለሁ፥ እግዚአብሔር ይስጥልኝ።
ማሳሰቢያ፦ይህ ቃለ መጠይቅ የተደረገው በ30/05/2003 ዓ.ም. ነው።




ክርስትያናትና 13 የወረዳ ቤተ ክህነቶች ይገኛሉ፡፡ በሌሎቹ አብያት ክርስቲያናት ምንም ዓይነት የተለየ ችግር አላጋጠመንም አልፎ አልፎ አንዳንድ ቦታዎች ቢታዩም ይሄን ያህል አይደሉም፡፡ ትልቁና ከፍተኛው ችግር አልፎ አልፎ እየተነሣ ያለው በመንበረ ጵጵስናው ርዕሰ ከተማ በሚገኘው ደብረ ምህረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ነው፡፡ ውሳኔዎች፣ መመሪያዎች፣ ሰርኩላሮች ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ወደ ሃገረ ስብከቱ በተዋረድ ይመጣሉ፤ ተወረዱንም ጠብቆ ወደ አድባራትና ገዳማት ይወርዳሉ፡፡ በደብረ ምህረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም አስተዳዳሪና ሰበካ ጉባኤ በኩል ግን መመሪያን የመፈጸምና የማስፈጸም፥ የቃለ አዋዲውን ሕግ የመጠበቅና የማስጠበቅ፤ በአጠቃላይ ግቢውን ከሁከትና አላስፈላጊ ከሆነ ነገሮች ሁሉ የመጠበቅና የማስጠበቅ ጉዳይ የሰበካ ጉባኤ ጉዳይ ሆኖ ሳለ አባላቱና የደብሩ አስተዳዳሪ ኃላፊነታቸውን ባለመወጣታቸው ምክንያት ነው ይሄ ሁሉ ችግር እየተፈጠረ ያለው። ይሄንንም ችግር እንዲፈቱ ለአስተዳዳሪው በብጹዕነታቸው ከአንድም ሁለት ሦስቴ መመሪያ ተሰጥቷል፡፡ የሰበካ ጉባኤውንም በጋራ አሰባስበን የአቅማቸውን ቃለ ዐዋዲውን ጠብቀው እንዲሠሩ፥ ከአቅም በላይ የሆነ ነገር ሲገኝ ደግሞ ለሃገረ ስብከቱና ለመንግሥት አካላት አቅርበው እንዲያስከብሩ፣ ግቢውን እንዲያስጠብቁ፤ ተደጋጋሚ ውይይቶች የጽሑፍም ሆነ የቃል መመሪያዎች ተሰጥተዋል፤ ነገር ግን ተፈጻሚነት ሳያገኙ እየቀሩ፥ በቸልታ እየታለፈ ችግሩ ወደ አለመወገድና መድረኩ በተለያየ ጊዜ የጭቅጭቅ መድረክ እንዲሆን አድርጎታል፡፡

በስምንት ዓመት የጎንደር ቆይታዬ በየዓመቱ በዓሉን የመካፈል ዕድል አግኝቻለሁ። እያንዳንዱ ዓመት የየራሱ የሆነ ለየት ያሉ ትዕይንቶች ነበሩት። በአጠቃላይ ግን የታዳሚው ቁጥር ለማመን በሚያስቸግር መልኩ ከዓመት ወደ ዓመት እየጨመረ መጥቷል። በሌላ መልኩ ደግሞ ወጣቱ በበዓሉ ላይ ያለው ተሳትፎ ለውጥም ከቤተ ክርስቲያን ሥርዓት አንፃር በጣም የሚበረታታ ነው።
ታቦታቱ ከየአብያተ ክርስቲያናቱ በክብር ወጥተው በሕዝቡ እልልታ፣ ሽብሽባ እና በካህናቱ ውብ ያሬዳዊ ዜማ ወደ ወንዝ ወይም የተዘጋጀ የውኃ ቦታ በመውረድ የሚጀምረው ይህ በዓል ሕዝቡን በሰፊው የሚያሳተፍ ነው።
በበዓሉ ላይ ትልቅ ተሳትፎ ያደርጋል። በዓሉ ከመከበሩ ከወራት በፊት በየሰንበት ትምህርት ቤቱ በልዩ ኮሚቴዎች የተለያዩ እንቅስቃሴዎች ሲያደርግ ቆይቷል።

በያዝነው የፈረንጆች አመት መጋቢት ወር ላይም በፋሽን፣ በፈንጠዝያ፣ በሙዚቃ፣ በመንገድ ላይ ቲአትሮችና በካርኒቫል ለማክበር እቅድ ተይዟል። 
መርካቶ የሚለውን ቃል እዚህ ጋር ስናነብ መቼም በየሕሊናችን የሚመጡ ብዙ የመርካቶ ሥዕሎች ይኖራሉ ፡፡ በተለይ ግርግሩ፣ ማጭበርበሩ፣ ሌብነቱ፣ በቀላሉ የማይገታዉ አመጹ፣ ምንም ነገር ፈልጎ የማይታጣበት መሆኑ፣ ቆሻሻው….በነዚህ ሁሉ ነገሮች እንደ መርካቶ ቅድሚያዉን የሚይዝ አካባቢ የሚኖር አይመስለኝም፡፡
ዛሬ የመርካቶን ሌላኛውን መልክ እንይ፡፡ በመርካቶ ውስጥ የሚኖሩ ነዋሪዎች፣ ነጋዴዎች እና ወጣቶች በደንብ ከሚታወቁባቸዉ ነገሮች መካከል አንዱ መንፈሳዊ አገልግሎታቸው ነዉ፡፡ ሁለት ወይም ሦስት ሆነው ሙሉ ቤተ ክርስቲያን የሚያሠሩ፣ ነዳያንን የሚያበሉ፣ የሚያለብሱ፣ በየዓመት በዓሉ የተቸገሩ ወገኖቻችን ከሌላው ወገናቸው ባልተናነሰ መንገድ በዓሉን እንዲያከብሩ በገንዘብ እና ለበዓላት በሚያስፈልጉ ነገሮች የሚረዱ በትክክል ገንዘባቸው ከየት እንደተገኘ የተረዱ ወገኖችን የያዘ አከባቢ መርካቶ ነው፡፡
መርካቶ ለሀገሪቷ ኢኮኖሚ ዋልታ አንዱ መሆኑ አይዘነጋም፡፡ ይሁን እንጂ ለቤተ ክርስቲያንም ትልቅ የገንዘብ እና የሰው ኀይል ምንጭ እንደሆነ ቤተ ክርስቲያኒቷ ምን ያህል እንደተገነዘበች እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ በአራቱም ማዕዘን የሚገኙ የገጠር አብያተ ክርስቲያናት ሕልውና እንዳይጠፋና በነዚሁ አከባቢ ለሚኖሩ ምዕመናን ተስፋ በመሆን እያገለገሉ ያሉ የቤተ ክርስቲያን አለኝታ የሆኑ የክርስቲያን ወገኖችን የያዘ ቦታ መርካቶ ነው፡፡
የመርካቶ መሬት ወትሮ ከሚታወቅበት ቆሻሻነት ጸድቶ እሱም እንደ አዲስ ክርስቲያን ተጠምቆ በቄጠማ፣ በምንጣፍ አምሮበት ለሚያይ የወትሮው መርካቶ ነው ብሎ ለማመን በጣም ያስቸግራል፡፡ አየሩ በዕጣን መዓዛ ተሞልቶ፣ በመዝሙርና ዕልልታ ደምቆ ልዩ ልዩ ቀለማት ባሏቸው ፊኛዎችና ጥቅሶች ተውቦ ለሚያየው እውነት ይህ መርካቶ ነው ብሎ እንዲጠይቅ ያደርገዋል፡፡
ወጣቶች በልዩ ልዩ ቲሸርቶችና ጥቅሶች ደምቀው ቄጠማ በመጎዝጎዝ፣ ርዝመቱ በውል የማይታወቀውን ምንጣፍ በመጠቅለል እና በመዘርጋት ታቦታቱን ያከበሩ ካህናት በባዶ አስፓልት ላይ እንዳይራመዱ የሚፋጠኑትን ወጣቶች ስናይ የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ ሳናደንቅ አናልፍም፡፡
ታዲያ ቤተ ክርስቲያን፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች እና ሌሎች የሚመለከታቸዉ የመንፈሳውያን ማኅበራት ይህንን ጊዜ ትልቅ የቤት ሥራ እንደሚጠብቃቸው ልብ ሊሉት ይገባል፡፡ ጌታችን ወደኔ የመጣውን ወደውጭ አላወጣውም ብሏልና እነዚህን ወጣቶች አሳልፈን እንዳንሰጥ የተቀበልነውን አደራ እናስታዉስ፡፡ ስለዚህ ቢታሰብላቸው፡፡
የ2003 ዓ.ም የጌታችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት ዋዜማ የከተራ በዓል በታላቅ ድምቀት ተከብሯል። በዋናው በዓል ዋዜማ፥ ከሥርዓተ ቅዳሴው ፍጻሜ በኋላ ታቦታተ ሕጉ ከመንበረ ክብራቸው ተነስተው በየምዕራፉ በሊቃውንት አባቶች ስብሐተ እግዚአብሔር እየተደረሰ በሰንበት ት/ቤት አባላትና ምዕመናን መዝሙር እየተዘመረ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ አምርተዋል።
መረዋሕ የያዙ ዲያቆናት፥ በሰልፍ ሆነው የሚዘምሩ ጥንግ ድርብና ካባ የለበሱ መዘምራን፥ የደንብ ልብስ የለበሱ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች፥ ፀአዳ የለበሱ የማኅበረ ቅዱሳን መዘምራን የጌታችን ጥምቀት የሚመለከቱ መዝሙሮችን በመዘመር፥ ወጣቶች ግራና ቀኝ እጅ ለእጅ በመያያዝ ሕዝበ ክርስቲያኑን ወደ ቀኝና ወደ ግራ ከፊትና ከኋላ በማድረግ ያለ ምንም ትርምስና ግርግር የተለያዩ ጥምቀትን የሚመለከቱ መዝሙሮችን በመዘመር፣ ወጣቶችም ፊት በመቅደም ለታቦታቱ ክብር ያዘጋጁትን ምንጣፍ በማንጠፍና ቄጠማ በመጎዝጎዝ የእግዚአብሔር ማደሪያ ለሆኑት ታቦታተ ሕጉና ለአባቶቻችን ካህናት ልዩ ክብር በማሳየት ወደ ባሕረ ጥምቀት/ጃንሜዳ/ ደርሰዋል።
ይህም በዓል መገለጥ/epiphany/ ይባላል። በዕለቱ ደግሞ ነገ ጌታችን በተጠመቀ ጊዜ መገለጥ ሆኗል። የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ አንድነትና ሦስትነት ተገልጿል። ክርስቲያኖችም ይህንን በዓል የምናከብረው ለበረከትና ለረድኤት ነው። ምዕመኑ በተለየ ሁኔታ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ማራኪና አስደናቂ ነገር ለቤተ ክርስቲያኒቱ እያበረከተ መሆኑንና ይህ ደግሞ የቤተ ክርስቲያኒቱንም የአገሪቱንም መልካም ገፅታ የሚያንፀባርቅ ይሆናል። አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ገጽታውም በጣም ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው መሆኑንና በዓሉ በነገው ዕለትም በከፍተኛ ድምቀት እንደሚከበር ገልጸዋል።
በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም የተገኙት የጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ንቡረ እድ ኤልያስ አብርሃ በሰጡት ትምህርት «ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ማን አጠመቀው ብንባል ማን እንላለን? ዮሐንስ አጠመቀው እንበል? እኔ ግን ቅዱስ ዮሐንስ አምላክን በማጥመቁ የሰዎች ልጆች ሁላችን ነው ያጥመቅነው ብየ አምናለሁ። ኃይሌ ገ/ሥላሴ ሩጫ ቢያሸንፍ ኢትዮጵያ አሸነፈች እንደሚባለው፣ ሁሉም እንደሚደሰተው። «ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ» እንደተባለው ሰማያዊው አምላክ እግዚአብሔር ወልድ በመሬታዊው በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ። ፈጣሪን የምናጠምቅ ሆነን አይደለም ምን ያህል እንደወደደን ያሳያል እንጂ። ብዙ ሰማያውያን ሠራዊት ነበሩ፣ በእነርሱ እጅ መጠመቅ ይችል ነበር፤ በባሕርይ አባቱ መጠመቅ ይችል ነበር፤ በባሕርይ ሕይወቱም መጠመቅ ይችል ነበር። ፈጣሪ አምላካችን በሰው እጅ ተጠመቀ እኮ? በእውነት ምን አይነት ፍቅር ነው? ምንስ አይነት መውደድ ነው? እኛም ፈጣሪ አምላክን ለማጥመቅ በቃን እኮ!» ብለዋል።

የጎንደር መንበረ መንግሥት መድኅኔዓለም ደብር አስተዳዳሪና የአራቱ ጉባኤያት /የብሉይ፣ የሐዲስ፣ የሊቃውንትና የመጻሕፍተ መነኮሳት/ የጉባኤ መምህር ከሆኑት ከሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ጋር የጥምቀትን በዓል አስመልክተን በ09/05/03 ዓ.ም አጭር ቃለ ምልልስ በስልክ አድርገናል፡፡ ለሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ከፍተኛ ምስጋናችንን እያቀረብን ለአንባቢዎቻችን የታላቁን ሊቅ ቃለ ምልልስ በማቅረብ እንኳን አደረሳችሁ እንላለን፡፡ መልካም ንባብ፡፡
አማርኛ መካነ ድር፡- የጥምቀትን በዓል ለምን እናከብራለን? ለክርስቲያኖች ያለው ፋይዳ ምንድን ነው?
ድርቡሽ /Mahdists of sudan/ የጎንደርን አብያተ ክርስቲያናትን ካቃጠለ በኋላ ግን 8 ታቦታት ብቻ ይወርዳሉ፡፡ እነዚህም-
