ጋብቻና ጾታ

የክርስቲያናዊ ጋብቻ መነሻውም መድረሻውም እግዚአብሔር ነው፡፡ በቅዱስ ጋብቻ ሁለቱ ወንድና ሴት በቅዱስ ቊርባን አንድ ይሆናሉ፡፡ መንግሥቱን ከሚያወርሰን ጋር ኪዳን ሳንገባ ጋብቻን ብንጀምር እንደ ብሉይ ኪዳን ዓለማዊ፣ ምድራዊ፣ ሥጋዊ ልጅ ለመውለድ፣ የፍትወት ፈቃድን ለመፈጸም ወይም ለመረዳዳት ብቻ ዓለማውን ያደረገ ይሆናል፡፡ በክርስቲያናዊ ጋብቻ ግን እነዚህ ራሱ እግዚአብሔር የሚሰጠን ስጦታዎች ሲሆኑ በእምነታችን ጸንተን በበጐ ምግባር ከኖርን ደግሞ ሰማያዊ መንግሥቱን እንወርሳለን፡፡

ጋብቻና ጾታ

ፈቃድ ለሐሳብ መነሻ ነው፤ አንድ ሰው አንድን ጉዳይ ማሰብ የሚጀምረው ከፈቃዱ ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ሐሳብና ፈቃድ በአገባባዊ ፍቺአቸው ተለዋዋጭና ተመሳሳይ የሚተካካ ትርጒም ይኖራቸዋል፡፡ ጋብቻም በጥሬ ትርጉሙ ኪዳን ማለት በመሆኑ በሁለት አካላት መካከል የሚፈጸም ውል ስምምነት ነው፡፡ አንድን ጎጆ ለመምራት በፈቃድ ላይ የሚመሠረት ውል (ኪዳን) ነውና፤ የጋብቻ ኪዳን በፈቃደኝነት ላይ የተመሠረተ ሲሆን መጨረሻው ደግሞ ይህ ዓለም ሳይሆን ተስፋ የምናደርጋት መንግሥተ ሰማያት ናት፡፡

ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በዕረፍት ጊዜያችሁ ምን እየሠራችሁ ነው? ቤተ ክርስቲያን በመሄድ፣ መንፈሳዊ ትምህርት በመማር እንዲሁም ደግሞ ለዘመናዊ ትምህርታችሁ አንዳንድ ማጠናከሪያ የሆኑ ትምህርቶችን በመማር እያሳለፋችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን! ምክንያቱም በጨዋታ ብቻ ማሳለፍ የለብንም!

እንግዲህ አዲሱን ዘመን ልንቀበል በዝግጅት ላይ ነን! ባለፈው የቡሄ ዕለት ወንዶች ልጆች ዝማሬን እየዘመሩ በዓሉን እንዳከበሩት አሁን ደግሞ ተራው የእኅቶቻችን ነው! አበባ አየሽ ሆይ እያልን የፈጣሪያችንን ድንቅ ሥራ የሚገልጡ ዝማሬዎችን እየዘመራችሁ በዓሉን ለማክበር እየተዘጋጃችሁ ነው አይደል? በርቱ!

ታዲያ በአዲስ ዓመት በሚጀመረው ትምህርት በርትታችሁ ለመማር ዝግጅት ማደረጉንም እንዳንረሳ፤ ሌላው ደግሞ ቤተ ክርስቲያን መሄድን መንፈሳዊ ትምህርትን መማርን መቀጠል አለባችሁ፤ ባለፈው ትምህርታችን ከሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን የነፍስና የሥጋን ቁስል (ሕመም) የሚፈውሱ ስለሆኑት ምሥጢረ ንስሐ እና ምሥጢረ ቀንዲል ተምረን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ የአንድነትና የአገልግሎት ጸጋን ስለሚያሰጡን ሁለት ምሥጢራት እንማራለን፤ መልካም!

ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የዕረፍት ጊዜያችሁ እንዴት ነው? ጊዜያችሁን በአግባቡ ተጠቀሙ፤ በጨዋታ ብቻ ልታሳልፉት አይገባም፡፡ ልጆች! የክረምት ወቅት ከበድ ያለ ዝናም የሚዘንብበት ወቅት በመሆኑ በእያንዳንዱ ነገር ጥንቃቄ ማድረግ አለባችሁ! በባለፈው ትምህርታችን ስለ ሰባቱ ምሥጢራት ምንነት መግቢያውን ተምረናል፡፡ አሁን ደግሞ ስለ ምሥጢራት አፈጻጸም እንማራለን፤ ተከታተሉን!

ጣፋጯ ፍሬ

ዘለዓለማዊ ሕይወትን የማገኝብሽ ባለ መልካሟ መዓዛ ፍሬ የአምላኬ ስጦታ ነሽ፤ በገነት ፈጥሮ ቢያሳየኝ ሳላውቅሽ መቅረቴና ልመገብሽ ባለመቻሌ እጅጉን ኀዘን ይሰማኝ ነበር፡፡ ፈጣሪ በአንቺ ሕይወትን ሊሰጠኝ ጣፋጭ አድርጎ ቢፈጥርሽ ሳላውቅሽ ያልታዘዝኩትን ፍሬ በልቼ መራራ ሞትን በራሴ አመጣሁ፡፡ አሁን ግን አወኩሽ! የሕይወቴ ጣፋጯ ፍሬ በአንቺ ነፍሴ ተፈውሳለችና፡፡

ምሥጢረ ሥጋዌ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን! እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ! የትንሣኤ በዓል እንዴት ነበር? ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን በፈቃዱ በቅዱስ መስቀል ላይ ተሰቅሎ በመቃብር ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ከቆየ በኋላ ሞትን ድል አድርጎ ተነሣ፤ ይህች ዕለት ታላቅ ዕለት ናት!  መልካም! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ፤ ባለፈው ምሥጢረ ሥላሴን ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ ስለ ምሥጢረ ሥጋዌ እንማራለን፤ ተከታተሉን!

በዓለ ደብረ ታቦር

በተከበረች በነሐሴ ፲፫ በታቦር ተራራ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ዕለት በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ”በዓለ ደብረ ታቦር‘ ተብሎ ይከበራል፡፡

ቤተ ክርስቲያን

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁ? የዓመቱ የማጠቃለያ ፈተና እንዴት ነበር? በየትምህርት ወቅት መምህራን ሲያስተምሯችሁ የነበረውን ዕውቀት በማስተዋል ሲከታተል የነበረ፣ ያልገባውን ጠይቆ የተረዳና በደንብ ያጠና ተማሪ በጥሩ ውጤተ ከክፍል ክፍል ይሸጋገራል፤ መቼም እናንተ ጎበዝ እንደሆናችሁ ተስፋችን እሙን ነው፤ መልካም!

ልጆች! ባለፈው ጊዜ ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ትርጉም እንዲሁም የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን በማን፣ መቼና የት ቦታ እንደታነጸች ተመልክተናል፤ ዛሬ ደግሞ በያዝነው ቀጠሮ መሠረት በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስላሉት ሦስት ክፍላት ማለትም ስለቅኔ ማኅሌት፣ ቅድስት፣ መቅደስ አገልግሎትና ምሥጢራዊ ትርጉም እንማማራለን፤ መልካም ቆይታ!

ጥምቀት

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዮርዳኖስን ብርህት ማኅፀን እንድትሆን፣ ምእመናንም ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ፣ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ዳግም ተወልደው መንግሥተ ሰማያት እንዲገቡ  እንደዚሁም ሥርዓተ ጥምቀትን ለማስተማርና አብነት ለመሆን በጥር ዐሥራ አንድ ቀን ተጠምቋልና ይህችን የተከበረች ቀን ሕዝበ ክርስቲያን ያከብር ዘንድ ይገባል፡፡

‹‹ሚስቶች ሆይ፥ በጌታ እንደሚገባ ለባሎቻችሁ ተገዙ›› (ኤፌ.፭፥፳፪)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቤተ ክርስቲያን በፍቅር ሞቷል እና ቤተ ክርስቲያን ለክርስቶስ ትገዛለች፤ በተመሳሳይ ፍቅር ምክንያት ‹‹ሚስቶች ሆይ፤ ለጌታ እንደምትገዙ ለባሎቻችሁም ተገዙ፤ ክርስቶስ አካሉ ለሆነችው ቤተ ክርስቲያን ራስዋ እንደሆነ ሁሉ፣ አዳኝዋም እንደ ሆነ ወንድ ለሴት ራስዋ ነውና፡፡