ወርኃ ሰኔ
ወርኃ ሰኔ በዓመት ውስጥ ከሚገኙ ዐሥራ ሦስት ወራቶች መካከል ዐሥረኛው ወር ነው፤ ስለ ቃሉ ትርጒም መምህር ክፍለ ጊዮርጊስ ጀምረው አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ፈጽመውት ደስታ ተክለ ወልድ ባሳተሙት መዝገበ ቃላት መጽሐፍ ላይ “ሰነየ” ከሚለው ግስ የተገኘ መሆኑን ይገልጻል፡፡ ሰኔ ማለትም “ሰነየ፣ አማረ፣ መሰነይ፣ ሁለት ማድረግ፣ ማጠፍ ፣መደረብ፣ በመልክ በባሕርይ መለወጥ፣ ሌላ መሆን፣ መምሰል” እያለ ይተረጉመዋል፡፡ (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ ፰፻፸፭)

