የማይሞተው ሞተ!

በመዝሙርና ሥነ ጥበባት ክፍል

ጥቅምት ፳፮፤፳፻፲፰ ዓመተ ምሕረት

ልዑል ሆይ ክንድህን ስደድ

ናማ ውረድ

ና ተወለድ

ብለው ነቢያት በጾም ጸሎት ተጉ ጮኹ!

ጨለማውን አስወግዶ ብርሃኑን ያበራልን

አንጠፋ ዘንድ በፍጹም ፍቅር የራራልን

 

በግብዞች በአይሁድ ሥርዓት

በሕጋቸው እንደጻፉት

የሾህ አክሊል ተቀዳጅቶ

መጻጻውን ተጎንጭቶ

 …..

እርሱ ሞተ ሊሰጥ ሕይወት

ወየው በሉ አልቅሱለት፤

የእጁን መዳን ያገኛችሁ የጌንሴሬጥ ድውይ ሁሉ

ለኢየሱስ አልቅሱለት፤ ፍዳን ስላያት በመስቀሉ

የ፲፪ ዘመን ሥቃይ በልብሱ ጫፍ ………

በቅጽበት ውስጥ የጠፋልሽ

ተገረፈ፤ ተንገላታ፤ የማይሞተው ሞትን ሞተ፤ ……..

ያ ርኅሩኅ ቸር መዳኒትሽ

ኢያሮስ የት ነው ያለህ!

ያ’ዓለም ጌታ ተተፋበት ሴት ልጅህን ያዳነልህ!

እመቤቴ የልጅሽን መከራውን እንዴት ቻልሽው አልልሽም

ቅዱስ ዳዊት በእሳት ፈረስ ሰባቱ ኃያል …..

መላእክቱ ካንቺ መጥተው ቢያፅናኑሽም

ለሦስት ቀን የአንዱ ልጅሽ ከሞቱ ይልቅ አሟሟቱ ….

እያስነባሽ እህል ውኃ እንኳን አልቀመስሽም

አብ ሆይ ማረን!

መንፈስ ቅዱስ ተዘከረን!

በልጅህ ደም የተገዛን ለመሆኑ አላወቅንም ዋጋችንን

ጽድቃችንም የመርገም ጨርቅ ከንቱ ሆኖ

መኖሪያችን በሲኦል ቋት ተወስኖ

ለዘመናት ስንገረፍ በእሳት ላንቃ

ያበቃ ዘንድ ይህ እንግልት ይህ ሰቆቃ

እሰይ እሰይ ይኸው አሁን የምሥራች

የሞት ዐዋጅ ተሻረልን፤ ገነት ዳግም ተከፈተች

የጥሉ ግድግዳ ፍርሶ ሰላም ሆኗል ከላይም ከታች

፶፻፭፻ የንስሐ የጣር ዘመን ተፈፀመ

በደላችን ተሰርዞ በክርስቶስ ደም ታተመ::

 

በእንተ ስምዐ ለማርያም

ዛሬ በፍልሰታዋ በአዛኝት የጾም ወራት

ልመናዬ አይደለም ፍርፋሪ ኩርማን ዱቄት

በደብረ ታቦሩ በዓል በተገለጸበት ምሥጢር

የዕለት ጉርሴን አልጠይቅም ቆሜ በደጅዎ በር

ልለምን . . . በእንተ ስማ ለማርያም

ስለ ወላዲተ አምላክ . . .

ተጠያቂው ማነው?

መምሬ እውነቱ ከንስሓ ልጆቻቸው ጋር በመሆን ሕሙማንን ለመጠየቅ በያዙት መርሐ ግብር መሠረት ከምእመናኑ ተወካዮች እና ከማኅበረ ካህናቱ ተወካዮች ጋር የተቃጠሩበት ሰዓት እስኪደርስ ከግቢያቸው ካለው ዛፍ ሥር ተቀምጠው ሌሎቹን በመጠበቅ ላይ ናቸው፡፡

ስማችን!

ሕፃን ሆኖ አባቷ፣ አባት ሲሆን ልጇ

በእምነት ያበረታት ወርዶ ከእቅፍ እጇ

ወደ ሞት እንዳትሄድ ሥቃይን ተሰቅቃ

ለልጄ እንዳትል የመከራ እሳት ሞቃ

ቆሞ መሰከረ ድምጹን አሰምቶ

ከአላዊው ንጉሥ በመንፈስ ተሞልቶ

ሰማያዊ ቤት

መዓልት ለሌሊት ጊዜውን ሰጥቶ ሊያስረክብ ከግምሽ በታች ደቂቃዎች ቀርተውታል፤ ጠዋት ለስላሳ ሙቀቷን ከብርሃን ጋር፣ ከሰዓት ጠንከር ያለ ሙቀቷን ለምድርና ለነዋሪዎቿ እየሰጠች ወደ ምዕራብ ስትጓዝ የነበረች ፀሐይ ከአድማሱ ጥግ ግማሽ አካሏን ደብቃለች፡፡ ጠዋት ስትወጣ እየጓጓ ከሰዓት በማቃጠሏ ተማረውባት የነበሩትን ሰርክ በመጥለቋ እንዲናፍቋት ደብዛዛ ብርሃኗን እያሳየች ስንብቷን ጀምራለች!

የእምነት አርበኞች!

ሕዝቡን እያሳተ ከገደል ቢመራ

ትእዛዙ ሲፈጸም ለሥጋው የፈራ

የእምነት አርበኖች ሠለስቱ ሕፃናት

ከፊቱ በመቆም መሰከሩ ለእምነት

በእሳት ሲያስፈራ በሚከስመው ነዶ

ጣኦትን ሊያስመልክ ፈጣሪን አስክዶ

ከላይ ከሰማያት መልአክን አውርዶ

እሳቱ ሲበርድ ሰይጣን በዚህ ሲያፍር

ጽናት ተጋድሏቸው ገሀድ ሲመሰክር

የጽድቅ ብርሃን

በብርሃናት ልብስ ተሸልሞ…
በብዙ ሀብታት ያጌጠ
ሥጋን ከነምኞቱ ሰቅሎ…
ለምትበልጠው ጸጋ ያለመታከት የሮጠ

ይህ ነው ዜና ማርቆስ ትውልድ የሚያወሳው
የጽድቅ ብርሃን… ጧፍ ሆኖ የሚያበራው!

ጽዮን ሆይ ክበቢኝ!

የገባልሽ ኪዳን የሰጠሽ መሐላ

ከንቱ ነበረ ወይ የጨረቃ ጥላ?

በአጋንንት ፍላጻ ነፍሴ ብትወጋ

ምልጃሽ ነው ተስፋዬ ከጥላሽ ልጠጋ፡፡

ጽዮን ሆይ ክበቢኝ ለውዳሴሽ ልትጋ

የኃጢአት ጎዳናዬ መንገዴ ይዘጋ!

እኔም ልመለስ!

እኔም ልመለስ ድንግል እናቴ
ከስደት ሕይወት ከባርነቴ
በልጅሽ ጉንጮች በወረደ ዕንባ
ባዘነው ልብሽ በተላበሰው የኀዘን ካባ
በእናት አንጀትሽ እንስፍስፍ ብሎ ያኔ በባባ

ልመለስ ድንግል ሆይ እኔም ከስደት
እውነትን ልያዝ ልራቅ ከሐሰት፡፡

ጥላቻ ገዝቶኝ ወንድሜን ከጠላው
እምነት ምግባሬን ሰይጣን ዘረፈው
መልሽኝ ድንግል ይብቃኝ ግዞቱ
በምግባር እጦት በቁም መሞቱ!

ከውድቀት አነሣን!

ለሰሚው በሚከብድ ቃላት በማይገልጸው

በመከራ ውሎ አዳምን አዳነው!

ዲያብሎስ ታሠረ አዳም ነጻ ወጥቶ

ልጅ ተባለ ዳግም በደሉ ተረስቶ

የማይሞተው አምላክ ስለ እኛ ሲል ሞቶ

ከውድቀት አነሣን ልጅነትን ሰጥቶ!