የክርስትና መሠረተ እምነት በጸሎተ ሃይማኖት (ሦስተኛ መጽሐፍ)

በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ
 
‹‹ ጌታ ማኅየዊ ›› የተባሉት ቃላት ለአምላክ ብቻ የሚሰጡ ናቸው፡፡ ስለዚህም መንፈስ ቅዱስ ‹‹ ጌታ ማኅየዊ ›› መሆኑንና አምላክነቱንም በቅዱሳት መጻሕፍት ቃል በማረጋገጥ ፣ የመንፈስ ቅዱስ ተቃዋሚዎችን የረቱት የጥንቶቹ የቤተ ክርስቲያን አባቶች በአንቀጸ ሃይማኖታቸው ደንግገውልናል፡፡ መንፈስ ቅዱስም ከአብ ከወልድ ጋር እኩል ስለሆነ ከእነርሱ ጋር ልንሰግድለትና ልናመሰግነው እነደሚገባን አስተምረውናል፡፡

የክርስትና መሠረተ እምነት በጸሎተ ሃይማኖት (ሁለተኛ መጽሐፍ)

በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ
 
ሰው ባጠፋው ጥፋት ከደስታ ሕይወት ወጥቶ፣ ከክብሩ ተዋርዶና ወድቆ በችግርና በመከራ ኖሮ በመጨረሻ ሥጋው በመቃብር በስብሶ ሲቀር፣ ነፍሱ ደግሞ በሲዖል ስትሠቃይ በማየቱ ወልደ እግዚአብሔር ሰውን ከዚህ ክፉ ነገር ለማዳን ሰው ሆኖ ሕማምና ሞትን ተቀብሎ እንዳዳነው እናምናለን፡፡

የክርስትና መሠረተ እምነት በጸሎተ ሃይማኖት (አንደኛ መጽሐፍ)

በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ
እግዚአብሔር አምላክ የሁሉም አባት ነው መባሉ እርሱ ለፍጥረታት ሁሉ ማለት ለዓለም ሁሉ ሠራኢና መጋቢ ፣ ለሕዝብና ለአሕዛብ ሁሉ መሪና ጠባቂ በመሆኑ ነው፡፡ ‹‹እርሱ በክፉዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና በጻድቃንና በኃጢያተኞችም ላይ ዝናቡና ያዘንባልና››(ማቴ.5፣45)፡፡ እርሱ የሰማይ ወፎችን ይመጋባቸዋል ፤ የሜዳ አበቦችንና የሜዳውን ሣር ሁሉ በልዩ ልዩ ኅብረ ቀለም ያስጌጣቸዋል ፣ ያለብሳቸዋልም (ማቴ. 6፣26-30)፡፡

የትምህርተ ሃይማኖት መቅድም

በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ
አሚንሰ መሰረት ይእቲ ወካልአኒሃ ሕንጻ ወንድቅ እሙንቱ- እምነት መሠረት ናት ፤ ሌሎቹ ግን ሕንጻና ግንብ ናቸው:: በማለት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የሚያስገነዝበን እንደ ሕንጻና ግንብ ከሚቆጠሩት ከምግባርና ከትሩፋት ሁሉ በፊት የሃይማኖትን ቀዳሚነትና መሠረትነት ነው፡፡ መሠረት ሕንጻውን ሁሉ እንደሚሸከም እምነትም ምግባራትን ሁሉ ትይዛለች ፤ ሕንጻ ያለ መሠረት እንደማይቆም ምግባርም ያለ ሃይማኖት አይኖርም፡፡ ስለሆነም ከሁሉ በፊት የሃይማኖትን ትርጉም በማስቀደም ትምህርታችንን እንጀምራለን፡፡

ነገረ ክርስቶስ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ

በአቤል ሚካኤል
ብርህት፣ ንጽህት፣ ጽድልት፣ የሆነች ቤተክርስቲያናችን ከምታስተምራቸው ትምህርቶች አንዱና ዋነኛው ነገረ ክርስቶስ ነው፡፡ በቤተክርስቲያን ትምህርት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ሥላሴ አንዱ አካል ወልድ ሲሆን ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር የተካከለ ሲሆን በኋላኛ ዘመን ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ ሰው ሆነ፡፡