ሥርዓተ አምልኮ
አምላካችን እግዚአብሔር ዓለምን ሲፈጥር ፍጥረት ሁሉ እንዲያመልከውና እንዲመሰግነው ነው፤ በአርአያውና በአምሳሉ የተፈጠርን ሰዎች ብቻም ሳይሆን በደመ ነፍስ የሚንቀሳቀሱ እንስሳት ሳይቀር ፈጣሪያቸውን ያመሰግናሉ፡፡ በተለይም በክርስቶስ ክርስቲያን ለተባልን ሰዎች የምናመልክበት የቅድስና ሕይወት ሰጥኖናል፡፡ ሕጉን ጠብቀን በሥርዓቱ ለምንኖር ለእኛ እርሱ ምሕረቱ የበዛ በመሆኑ በሕይወታችን ውስጥ ሊኖር ይወዳል፤ በቤቱም ስንገኝ ደስ ይሰኛል፡፡ እርሱን በዓይን ለማየት ባይቻለንም መኖሩን የምናውቀበትና የምናመሰግንበት፣ ለእርሱም የአምልኮት ስግደት የምናቀርብበትና የምናዜምበት በአጠቃላይ የምናመልክበት መንገድ ፈጥሮልናል፡፡ ለዚህም የከበረ ተግባር መፈጸሚያ ባርኮና ቀድሶ ንዋያተ ቅድሳትን ሰጥቶናል፡፡