‹‹ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባል›› (ሐዋ.፭፥፳፱)
መንፈስ ቅዱስ ያደረባቸው ቅዱሳን ሐዋርያት ይህንን ቃል የተናገሩት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከዓለም ለይቶ የጠራቸው፣ የመረጣቸው በመሆናቸው ነው። በዓለም እየተዘዋወሩ ቅዱስ ቃሉን በሚያስተምሩበት በስሙ ተአምራት በሚያደርጉበት ጊዜ ፈተና ነበረባቸው፤ እንቅፋት ያጋጥማቸው ነበረ። ብዙዎች በምቀኝነትና በቅናት እየተነሣሡ እንዳያስተምሩ ይከለክሏቸው ነበረ፤ ይናገሯቸውም ነበረ። በዚህ ሰዓት ነበር ቅዱሳን ሐዋርያት ‹‹ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባናል›› በማለት ያስተማሩት፤ እግዚአብሔር እንዲያስተምሩ አዟቸው ነበርና። (ሐዋ.፭፥፳፱)