ምሥጢረ ጥምቀት
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የትንሣኤ በዓል እንዴት ነበር? ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በማስቀደስ አከበራችሁተ አይደል! የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ በዓል የደስታ በዓላችን ነው! በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አባቶቻችን በሠሩልን ሥርዓት መሠረት እስከ በዓለ ሃምሣ (ጰራቅሊጦስ) ይታሰባል፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! በሰንበት ትምህርት ቤት በመግባትም ተማሩ አገልግሉ፤ በቤተ እግዚአብሔር ማደግ መታደል ነውና! ሌላው ደግሞ በዘመናዊ ትምህርታችሁም በርቱ! ሁለተኛው የመንፈቀ ዓመት ትምህርት እየተገባደደ ስለሆነ በተማራችሁት መሠረትም ስለምትፈተኑ በርትታችሁ ማጥናት አለባችሁ፡፡ መልካም! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ፤ ባለፈው ምሥጢረ ሥጋዌን ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ ምሥጢረ ጥምቀትን እንማራለን፤ ተከታተሉን!