ማይኪራህ
ከሌሊት ወፍ በመዓልቱ:
…… እልፍ እንቁላል ሊሰበሰብ፣
የወንዱ ጽንስ እንዲገፋ
…… ከበቅሎው ወተት ሊታለብ፤
ከማር ቀፎ የዝንብ መንጋ
…… አውሬው ጓዳ ገብቶ እንዲያድር፣
የተፈጥሮ ሕጉን ስቶ
…… ያለቦታው እንዲሰደር፤
ከሌሊት ወፍ በመዓልቱ:
…… እልፍ እንቁላል ሊሰበሰብ፣
የወንዱ ጽንስ እንዲገፋ
…… ከበቅሎው ወተት ሊታለብ፤
ከማር ቀፎ የዝንብ መንጋ
…… አውሬው ጓዳ ገብቶ እንዲያድር፣
የተፈጥሮ ሕጉን ስቶ
…… ያለቦታው እንዲሰደር፤
ኢትዮጵያዊው ማኅሌታይ፣ የዜማ ደራሲና ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ድንቅ ተጋድሎን ፈጽሞ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም የገባበት ዕለት ግንቦት ፲፩ የከበረች እንደመሆኗ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ታከብረዋለች፡፡
ይህን ኃይለ ቃል የተናገረው ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ ቃሉን ደግሞ የሚበላ ፈልገው ዓሣ ለማጥመድ ሌሊቱን ሲደክሙ ለነበሩ ግን የሚፈልጉትን ሳያገኙ በረኀብ ዝለው በፍለጋ ደክመው ለነበሩ ለቅዱሳን ሐዋርያት ነው፡፡ ሞትን በሞቱ ገድሎ፣ በትንሣኤው ትንሣኤያችንን አብሥሮ፣ ሞትን ድል አድርጎ ከተነሣ በኋላ ለቅዱሳን ሐዋርያት በጥብርያዶስ ባሕር ዳርቻ ተገለጠላቸው፤ ይህ ከትንሣኤው በኋላ ሲገለጥላቸው ሦስተኛው ጊዜ ነው፡፡ መጀመሪያ ሲገለጥላቸው አይሁድን ፈርተው በፍርሃት ተሸብበው በራቸውን ዘግተው በተስፋ መቁረጥ ውስጥ በነበሩ ጊዜ በዝግ ቤት ገብቶ ፍርሃትን አስወገደላቸው ተስፋቸውን ቀጠለላቸው፤ ለተረበሸው ልባቸው ‹‹ሰላም ለእናንተ ይሁን›› በማለት ሰላምን ሰጣቸው አረጋጋቸው፡፡ (ሉቃ.፳፬፥፴፮፣ዮሐ.፳፥፲፱)
መውደድ በሰዎች መካከል የሚኖር ስሜት ነው፤ ያለ መዋደድም በዚህ ምድር ላይ መኖር አይቻለንም፤ መጠኑ ይብዛም ይነስ በሰው ልብ ውስጥ የመዋደድ ስሜት ይፈጠራል፡፡ ሰዎች ተቻችለንና ተሳስብን እንዲሁም ተዛዝነን የምንኖረው ስንዋደድ ነው፡፡ ግን ይህ ስሜት ከምንም ተነሥቶ በውስጣችን ሊፈጠር አይችልምና መውደድ መነሻው ምንድነው? የሚለውን ነገር ብንመረምር መልካም ነው፡፡
ወርቃማው የወጣትነት ዘመናችን በተስፋ፣ በመልካም ምኞትና በትጋት የተሞላ፣ ዕውቀትንና አቅምን ያማከለ ማንነታችን የሚታነጽበት፣ መንፈሳዊነታችን የሚገለጽበት የዕድሜ ክልል እንደመሆኑ የሕይወታችን መሠረት ነው፡፡ መንፈሳዊ ፍሬን አፍርተን ርስተ መንግሥተ ሰማያት ለምንወርስብትም የሕይወት ስንቅ የምንሰንቅበት የተጋድሎ ዘመን ስለመሆኑ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከልጅነታችን ጀምሮ አበክራ ታስተምረናለች፡፡ በሰንበት ትምህርት ቤቶቿም ኮትኩታ አሳድጋ መንፈሳዊ ፍሬ ለማፍራት ታበቃናለች፡፡ ለዚህ የመሸጋገሪያ ዕድሜ በደረስንበት ጊዜም የሕይወታችን መርሕ የሆነው ትምህርተ ወንጌል እንዳይጓደልብን በዐውደ ምሕረቷ ላይ ጉባኤ ዘርግታ ሰማያዊ ኅብስትን አዘጋጅታ ትመግበናለች፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? እየበረታችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን? በርቱ! ዛሬ የምንነጋራችሁ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ልደት ይሆናል!መልካም ንባብ!
እግዚአብሔር መላእክትንና የሰው ልጅን ሲፈጥር የፈጠረበት ትልቁ ዓላማ ስሙን ቀድሰው ክብሩን እንዲወርሱ ነው፤ ነገር ግን ክፋትን ኃጢአትን ዲያብሎስ (አስቀድሞ ሳጥናኤል የተባለ) ከልቡ በሐሳቡ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለመ መላእክት አመነጫት፤ አመንጭቶም አልቀረም፤ ከራሱ ጋር ሌሎች እርሱን የመሰሉ መናፍስትን (መላእክትን) ይዞ ከሰማያዊ ክብሩ ወደቀ::
በብዙ ኅብረ አምሳል አምላካችን እግዚአብሔር የሰውን ልጅ አስተምሯል። ነቢያቱን በብዙ ቋንቋና ምሳሌ አናግሯል። የሰው ልጅ በልቡናው መርምሮ የተወደደ ሕይወት መኖር ሲሳነው በሊቀ ነቢያት ሙሴ በኩል ሕገ ኦሪትን ሰጥቶታል። በሕገ ልቡና “እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን” እንደሚል ቀደምት አበው የተጻፈ ነገር ሳይኖር እንደ እግዚአብሔር አሳብ መኖር ችለዋል። (ሮሜ.፰፥፳፰) እንደ አሳቡ መኖር ላልቻሉት ደሞ ጽሕፈቱን እያዩ በንጽሕና እንዲኖሩ ኦሪት ተጽፋ በሙሴ በኩል ተሰጠች። በኋላም ራሱ ጌታችን ሰው ሁኖ ፻፳ ቤተሰብ መርጦ በቃልና በገቢር አስተምሯል። ይህን ትምህርትም ወንጌላውያን ጽፈው ደጉሰው እንዲያስቀምጡት የጌታችን ፈቃድ ሁኖ ለትውልድ ተላልፏል።
ፀሐይና የአጥቢያ ኮከብ የተባለ ታላቅና ክቡር የሆነ የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ የምስክርነት ፍጻሜ የሆነበት ቀን ሚያዚያ ፳፫ የከበረ ነው፡፡
የቅዱስ ጊዮርጊስ አባት ቀጰዶቅያ አገር ይኖር የነበረ አንስጣስዮስ የተባለ መስፍን ነው፡፡ እናቱም ቴዎብስታ የተባለች ፍልስጥዔማዊ ነበረች፤ የዚህ ቅዱስ አባትም የሞተው በልጅነቱ ስለዚህም ሌላ ደግ ክርስቲያናዊ መስፍን ወስዶ አሳደገው፡፡ መስፍኑም በጦር ኃይል አሰለጠነው፡፡ ሃያ ዓመትም በሞላው ጊዜ መስፍኑ የ፲፭ ዓመት ልጁን ሊያጋባውና ሀብቱን ሊያወርሰው ድግስ ደገስ፤ ነገር ግን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ጊዮርጊስን ለዚህ አልመረጠውምና የመስፍኑን ነፍስ ወሰደ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ኀዘኑን ከጨርሰ በኋላ ወደ ቤሩት ሀገር ሄደ፡፡ በዚያም ደራጎንን ያመልኩና ሴት ልጆቻቸውን ይገብሩለት ነበር፤ ሰማዕቱም ደራጎኑን በኃይለ መስቀል ድል ነሥቶት ገድሎታል፤ ሕዝቡንም ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መልሷቸዋል፡፡