የሐዋርያት ጾም
ጾሙን በጰራቅሊጦስ ማግሥት ጀምረው የጥያቄያቸውን መልስ እስኪያገኙ እስከ ሐምሌ አምስት ቆይተዋል። የጌታ ፈቃዱ ሆኖም በሐዋርያነት አገልግሎታቸው የሚታወቁት የሰማዕትነት ኅልፈታቸው ጾሙን ፈተው ለአገልግሎት በተሠማሩበት ዕለት ሁኗል (ስንክሳር ዘሐምሌ አምስት)። በረከታቸው ይደርብን!
ጾሙን በጰራቅሊጦስ ማግሥት ጀምረው የጥያቄያቸውን መልስ እስኪያገኙ እስከ ሐምሌ አምስት ቆይተዋል። የጌታ ፈቃዱ ሆኖም በሐዋርያነት አገልግሎታቸው የሚታወቁት የሰማዕትነት ኅልፈታቸው ጾሙን ፈተው ለአገልግሎት በተሠማሩበት ዕለት ሁኗል (ስንክሳር ዘሐምሌ አምስት)። በረከታቸው ይደርብን!
ጰራቅሊጦስ ማለት ናዛዚ፣ ከሣቲ፣ መንጽሒ፣ መጽንዒ፣ መስተስርዪ፤ መስተፍሥሒ ማለት ነው። መንጽሒ ማለት ከኃጢአት የሚያነጻ፣ የሚቀድስ፣ የቅድስና ነቅዕ፣ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ በሰውነታችን የሚያሳድር ነው። መጽንዒ ማለት የሚያጸና፣ ኃይል፣ ብርታት፣ ጥብዓት የሚሆን፣ ቅዱሳንን ከሀገር ምድረ በዳ ከዘመዳ ባዳ አሰኝቶ ዳዋ ጥሰው፣ ጤዛ ልሰው፣ ደንጋይ ተንተርሰው፣ ግርማ ሌሊቱን፣ ጸብአ አጋንንቱን ታግሠው፣ ጸንተው እንዲኖሩ የሚያደርግ ማለት ነው። መሥተፍሥሒ ማለት ሙሐዘ ፍሥሓ የደስታ መፍሰሻ፣ ሰዎችን ደስ የሚያሰኝ፣ በመከራ በኀዘን ውስጥ ደስታን የሚሰጥ ነው። “ሐዋርያትንም ወደ እነርሱ ጠርተው ገረፉአቸው፥ በኢየሱስም ስም እንዳይናገሩ አዝዘው ፈቱአቸው። እነርሱም ስለ ስሙ ይናቁ ዘንድ የተገባቸው ሆነው ስለ ተቈጠሩ ከሸንጎው ፊት ደስ እያላቸው ወጡ” እንዲል፤ (የሐዋ.፭፥፵)
ነጻነት ከሰው ልጅ አፈጣጠር ጋር የተያያዘ ግብር መሆኑን ማወቅ እጅጉን ተገቢ ነው። አምላካችን እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው በአርአያውና በአምሳሉ ሲፈጥረው ሙሉ ነጻነት ያለው ፍጥረት አድርጎ ነው፡፡ ይህም ይታወቅ ዘንድ በተሰጠው አእምሮ የወደደውን (ክፉውን ከሻተ ክፉውን፣ መልካሙን ከሻተ መልካሙን) እንዲመርጥ የመምረጥ መብት ተሰጥቶታል።
ማመንንና መታመንን የሚፈታተኑ ነገሮች በዓለም ባይኖሩ ኖሮ ስለ ጽናት አይነገርም ነበር፡፡ ጽናትን የሚወልደው የመከራና የፈተና ብዛት ነው፡፡ በዚህ ዘመን ክርስቲያን ለመሆን እንዲሁም ስመ እግዚአብሔርን ለመጥራት እንፈልግ እንጂ ስለ ክርስትና መከራን ለመቀበል ግን አንፈልግም፡፡ ይህ ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ግን አይዟችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ›› በማለት ለተናገረው ቃል ምንኛ ባዕድ እየሆንን ለመምጣታችን ማሳያ ነው፡፡ (ዮሐ.፲፮፥፴፫)
መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያንብቡ!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ለከበረው ጤንነታችሁ እንዴት አላችሁ? የበዓለ ሃምሣ ሳምንታት እንዴት ናቸው? ቤተ ክርስቲያን እየሄዳችሁ ታስቀድሳላችሁ? በሰንበታትስ ከወላጆቻችሁ ጋር ወደ ቤተ ክርስቲያን ትሄዳላችሁ? ከሆነ በርቱ! ልጆች! ለዛሬ የምንነግራችሁ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ደብረ ምጥማቅ በሚባል ገዳም ያደረገችውን ተአምር ነው፤
በጉባኤ ኒቅያ ፫፻፲፰ቱ ሊቃውንት“ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት ወነበረ በየማነ አቡሁ…፤ በክብር ወደ ሰማይ ዐረገ፤ በአባቱም ቀኝ ተቀመጠ…” እንዳሉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከትንሣኤው በኋላ በአርባኛው ቀን በዚህ ዓለም የነበረውን የማዳኑን ሥራ ጨርሶ ወደ ላይ ማረጉንና በቀደመ ክብሩ በአብ ቀኝ መቀመጡን በማሰብ በዘወትር ጸሎታችንም እንዘክረዋለን፡፡
ዐሥራ ሁለተኛው የቊስጥንጥንያ መንበር የነበረ፣ ከአራቱ የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያን ዐቃቢያነ እምነት ከሆኑት ከቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ፣ ከቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያና ከቅዱስ ባስልዮስ ጋር በግብር የተካከለ፣ በገዳማዊ ሕይወቱ ብሕትው፣ በንጽሕናው ተአማኒ፣ በአእምሮ ምጡቅ፣ በአንደበቱ ርቱዕ፣ በስብከቱ መገሥጽ፣ በፍርዱ ፈታሒ በጽድቅ፣ በመግቦቱ አበ ምንዱባን (የድኆች አባት) በጥብቅናው ድምፀ ግፉዓን፣ በጥቡዕነቱ መገሥጽ፣ በክህነቱ የቤተ ክርስቲያን መዓዛ፣ የዓለም ሁሉ መምህር የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዕረፍቱ መታሰቢያ በግንቦት ፲፪ ቀን ሆነ።
ከሌሊት ወፍ በመዓልቱ:
…… እልፍ እንቁላል ሊሰበሰብ፣
የወንዱ ጽንስ እንዲገፋ
…… ከበቅሎው ወተት ሊታለብ፤
ከማር ቀፎ የዝንብ መንጋ
…… አውሬው ጓዳ ገብቶ እንዲያድር፣
የተፈጥሮ ሕጉን ስቶ
…… ያለቦታው እንዲሰደር፤
ኢትዮጵያዊው ማኅሌታይ፣ የዜማ ደራሲና ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ድንቅ ተጋድሎን ፈጽሞ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም የገባበት ዕለት ግንቦት ፲፩ የከበረች እንደመሆኗ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ታከብረዋለች፡፡