በኮሌራ በሽታ ጉዳት ለደረሰባቸው ምእመናን ድጋፍ ተደረገ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት በኮሌራ ወረርሽኝ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው የዳሰነች ሕዝበ ክርስቲያን የእርዳታ ድጋፍ ተደረገ፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት በኮሌራ ወረርሽኝ ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው የዳሰነች ሕዝበ ክርስቲያን የእርዳታ ድጋፍ ተደረገ፡፡
ዘጠነኛው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ በመጭው እሑድ ግንቦት ፴ ቀን ፳፻፲፪ ዓ/ም ሊካሄድ እንደሆነ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ መምህር ዕንቈ ባሕርይ ተከሥተ አስታወቁ፡፡
በዚህ ወቅቱ ዓለም በከባድ እና አስቸጋሪ ፈተና ውስጥ ነው፡፡ ይህን ቸነፈር በሰው ጥንቃቄ ብቻ መቋቋም የሚቻል አይደለም፡፡ ሆኖም በግዴለሽነት እንዳንጓዝ ይልቁንም አስፈላጊውን ሁሉ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባን ቅዱሳት መጻሕፍት ይመክሩናል፡፡ በሃይማኖት ጸንተው በምግባር ቀንተው፣ ጥንቃቄም አድርገው የኖሩ አባቶቻችን በነፍሳቸውም፣ በሥጋቸውም ድነዋል፡፡ እኛም አባቶቻችንን አብነት አድርገን በነፍስም በሥጋም እንድንድን ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል፡፡
በመጀመሪያ ደረጃ ቤተ ክርስቲያን መንግሥትን እየተከተለች፣ በጦር እያስፈራራች ሃይማኖቷን እንዳስፋፋች አድርጎ ማቅረብ የተዛባ አስተሳሰብ የወለደው መሆኑን መናገር እንፈልጋለን። ይህ ብቻ ሳይሆን የቤተ ክርስቲያኗን ታሪክ በማዛባት የቀረበው ሐሳብ እንዲስተካከል እንጠይቃለን። እውነቱ ግን በተቃራኒው ነው። ቤተ ክርስቲያን ያለሰለሰችው የአረማውያን እና የአሕዛብ ልቡና ወደ ማእከላዊ መንግሥት ለመታቀፍ እንዳላስቸገረ እና መንግሥት የራሱን ሥራ ለመሥራት እንዳገዘው መረዳት ይገባል። ያለፈው ሥርዓት ፈጽሞታል ለሚሉት ጥፋት ቤተ ክርስቲያንን ተጠያቂ ማድረግ አንደበቷን ዘግታ እንድትቀመጥ ለማድረግ የተሸረበ ሴራ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል። ገለጻው እውነታን ያላገናዘበ መሆኑን መረዳት እና ተገቢውን መልስ መስጠት አስፈላጊ ሲሆን በሕግ መጠየቅ ይገባል።