Entries by Mahibere Kidusan

በሰማዕቱ አቡነ ጴጥሮስ ሐውልት ጉዳይ ውይይት ተደረገ

በዳዊት ደስታ

መጋቢት 9 ቀን 2005 ዓ.ም.

ሰማዕቱ የአቡነ  ጴጥሮስ ሐውልት

 

የሰማዕቱ የአቡነ  ጴጥሮስ ሐውልት የቴክኒክ ጥናት ኮሚቴ ሐውልቱ ያለምንም ጉዳት እንዴት መነሣት እዳለበት ከባለ ድርሻ  አካላት ጋር ውይይት አደረገ፡፡

 

የቴከኒክ ጥናት ኮሚቴው የካቲት ፲፫ ቀን ፳፻፭ ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስብሰባ አዳራሽ ለግማሽ ቀን ባካሔደው ውይይት ሐውልቱ ተነሥቶ ወደ ሥራ ከመገባቱ በፊት በሚያስፈልጉ ጉዳዮች ላይ በስፋት መክሯል፡፡

 

በሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ላይ እንዲመለሱ የቀረቡ ጥያቄዎች

የተወደዳችሁ የሐዊረ ሕይወት አዘጋጆች ሰላመ እግዚአብሔር ይብዛላችሁ፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ለማንኛውም ጥያቄ መልስ ለመስጠት ዝግጁ እንደሆነች አምናለሁ፡፡ እናም ሁለት በአእምሮየ የሚመላለሱ ጥያቄዎች አሉኝ፡፡

የመጀመሪያው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ዓለምን እንደሚያድን ለሐዋርያት በሚያስተምርበት ወቅት ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የሆነው ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታ ሆይ ይህስ አይሁንብህ ብሎ በተናገረ ጊዜ ጌታችን አንተ ሰይጣን ከዚህ ሂድ ብሎ በጴጥሮስ ላይ አድሮ የክርስቶስን የማዳን ሥራ የተቃወመውን ዲያብሎስን ተቃውሞታል፡፡ እኔ እንደገባኝ ከሆነ የቅዱስ ጴጥሮስ ሀዘኔታ ተገቢ እንዳልነበ ነው በጌታችን የማዳን መንገድ ልንደሰት ይገባል እንጅ በስቅለት ወቅትና በሌሎችም ጊዜያት ስለ ጌታችን ስቅለት የሚደረገው የሐዘን ስሜት ከክርስትና አስተምሮ አንጻር ተገቢ ነው ወይ?

ሐዊረ ሕይወት ማለት…

ይህ ሁለት ቃል ተናቦ ፫ ሱባዔ (፳፩) ትርጉምን ይሰጠናል።
፩.    ቃል በቃል የሕይወት ጉዞ ማለት ነው።
፪.    የሕይወት ኑሮ ማለት ይሆናል።
“ሕይወት እንተ አልባቲ ሞት = ሞት የሌለባት የሕይወት ፍሬ/ኑሮ።” ዕዝ. ሱቱ. ፭፥፲፫
ደግሞም “ይኄይስ መዊት እመራር ሕይወት = ከመራር ኑሮ ሞት ይሻላል።” ሢራ ፴፥፲፯
፫.    የመዳን ጉዞ፣ ወይም የደኅንነት ጉዞ፣
“ዛቲ ይእቲ ቀዳሚት ሕይወት = ይህች የመጀመሪያዋ ትንሣኤ ድኅነት ናት።” ራእ ፳፥፭
ደግሞም “መጻእኪ ለሕይወትኪ = ለሕይወትሽ፣ ለደኅንነትሽ መጣሽ።” ዮዲ. ፲፮፥፫
፬.    የፈውስ ጉዞ፣ ወይም የጤንነት ጉዞ፣
“ወሰሚዖሙ ሕይወተ እሙታን = ከሙታን ተለይቶ መነሣትንም በሰሙ ጊዜ” ግ.ሐዋ. ፲፯፥፴፪
፭.    የመኖር ጉዞ፣

የዲላ ዮኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ የተመሠረተበትን አስራ ስድስተኛ ዓመቱን አከበረ

መጋቢት 6 ቀን 2005 ዓ.ም.


በዲ/ን ቴዎድሮስ ኃይሉ

በማኅበረ ቅዱሳን በዲላ ወረዳ ማእከል ሥር የሚገኘው የዲላ ዮኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ የተመሠረተበትን ዐሥራ ስድስተኛ ዓመቱን በዋለሜ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በደመቀ ሁኔታ አከበረ፡፡

ግቢ ጉባኤው ከየካቲት 29 ቀን እስከ መጋቢት 1 ቀን 2005 ዓ.ም የተመሠረተበትን በዓል ሲያከብር በማኅበረ ቅዱሳን የአዋሣ ማእከል ለግቢ ጉባኤ ተማሪዎች የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፏል፡፡ ማእከሉ በወከለው በአቶ ታደሰ ፈንታ በኩል ባስተላለፈው መልእክት “ዛሬ የምሥረታ በዓላችሁን የምታከብሩ ተማሪዎች ከመደበኛው ትምህርታችሁ ጎን ለጎን መንፈሳዊ ተግባራችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ጥሪያችንን በማቅረብ ነው” በማለት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡

 

===== ዜና ሐዊረ ሕይወት ======

የሐዊረ ሕይወት ጉዞ አዘጋጅ ኮሚቴ ወደ ደብረ ኤዶም ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በመሄድ የመንገዱንና የቦታውን ምቹነት አረጋግጦ መጣ፡፡ዝግጅቱ በከፍተኛ ሁኔታ እየተከናወነ ሲሆን የትኬት ሥርጭቱም በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡ አጫጭር መረጃዎች   ደብረ ኤዶም ቅዱስ ገብርኤል፡-   ቦታው : ከአዲስ አበባ ወደ አምቦ መስመር ላይ 40(?) ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ሲሆን የመንገዱ ጥራት ለማንኛውም ተጓዥ ምቹ መሆኑ ታይቷል፡፡ […]

ቅዱስነታቸው የመጀመሪያ እንኳን አደረሳችሁ መልእክታቸውን አስተላለፉ

የካቲት 28 ቀን 2005ዓ.ም

በእንዳለ ደምስስ

abune mathias1ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የአብይ ጾምን በማስመልከት የካቲት 29 ቀን 2005 ዓ.ም. የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ፡፡

 

ወደ ቤቴል ውጣ በዚያም ኑር ዘፍ.35፥1

የካቲት 27 ቀን 2005 ዓ.ም.

ዲ/ን ሰለሞን መኩሪ

ይህንን የተናገረ አምላካችን እግዚአብሔር ነው፡፡ ይህ የተነገረው እስራኤል ለተባለ ያዕቆብ ነው፡፡ በቅዱስ መጽሐፍ ታሪኩ ተጽፎ እንደምናገኘው ከወንድሙ ከዔሳው ሸሽቶ የአባቱን የይስሐቅን በረከት ተቀብሎ ወደ አጎቱ ወደ ላባ ሲሄድ ሎዛ ከምትባለው ምድር ሲደርስ ጊዜው መሸ፡፡ እርሱም ደክሞት ስለነበር ድንጋይ ተንተርሶ ተኝቶ ሳለ ሌሊት በራእይ እግዚአብሔር ተገለጠለት ራእዩም የወርቅ መሰላል ከምድር እስከ ሰማይ ተተክሎ በመሰላሉ መላእክት ሲወጡ ሲወርዱ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም በዙፋኑ ተቀምጦ ነበር፡፡

 

ያዕቆብንም “እኔ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅ አምላክ እግዚአብሔር ነኝ፤ አትፍራ፣ ይህችን አንተ የተኛህባትን ምድር ለአንተም ለዘርህም እሰጣለሁ ዘርህም እንደ ባሕር አሸዋ ይሆናል፡፡ በአንተ በዘርህ አሕዛብ ይባረካሉ፡፡ እነሆም እኔ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፡፡ የነገርኩህን ሁሉ እስካደርግልህ ድረስ አልተውህም” አለው፡፡ ያዕቆብም ከእንቅልፍ ተነሥቶ በእውነት እግዚአብሔር በዚህ ስፍራ አለ፤ እኔ አላወቅሁም ነበር፡፡

 

ይህ ሥፍራ እንዴት ያስፈራል? ይህ ስፍራ የእግዚአብሔር ቤት ነው እንጂ ሌላ አይደለም፤ ይህችም የሰማይ ደጅ ናት፡፡ ያዕቆብም ማልዶ ተነሣ ተንተርሷት የነበረችውንም ድንጋይ ወስዶ ሐውልት አድርጎ አቆማት፤ በላይዋም ዘይት አፈሰሰባት፡፡ ያዕቆብም ያን ሥፍራ ቤቴል ብሎ ጠራው አስቀድሞ ግን የዚያ ከተማ ስም ሎዛ ነበር፡፡ ያዕቆብም ስዕለትን ተሳለ፡፡ እግዚአብሔር ከእኔ ጋር ቢሆን በምሄድበት መንገድ ቢጠብቀኝ፣ የምበላውን እንጀራ የምለብሰውን ልብስ ቢሰጠኝ ወደ አባቴ አገር በሰላም ቢመልሰኝ እግዚአብሔር አምላኬ ይሆንልኛል፡፡ ለሐውልት ያቆምኳት ይህች ድንጋይ የእግዚአብሔር ቤት ትሆንልኛለች፤ ከሰጠኸኝ ሁሉ ለአንተ ከአስር እጅ አንዱን እሰጥሃለሁ አለ፡፡ እግዚአብሔርም ስእለቱን ሰምቶ ሁሉንም ፈጸመለት ወደ አጎቱ ወደ ላባ ደርሶ ሚስት አግብቶ ብዙ ልጆችን ወልዶ እንዲሁም ብዙ ባሮችን እና ሀብት ንብረት አፍርቶ ወደ አባቱ ሀገር ሲመለስ እግዚአብሔር አምላክ ተገለጠለትና “ወደ ቤቴል ውጣ በዚያም ኑር” ብሎ አዘዘው ዘፍ.28፥10-20፣ ዘፍ.35፥1፡፡

x

የ6ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ሥርዓተ ሢመት ፈጸሙ

የካቲት 27 ቀን 2005ዓ.ም

በእንዳለ ደምስስ

ሪፖርታዥ

1-bealesimet“የቤተ ክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን አከብራለሁ አስከብራለሁ” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 6ኛ ፓትርያርክ ሆነው የተመረጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሥርዓተ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም. እንደተፈጸመላቸው ቤተ ክርስቲያንንና ምእመናንን ለማገልገል ቃለ መሐላ የፈጸሙ ሲሆን ከሰሜን አሜሪካ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር የሚካሄደው የእርቀ ሰላም ሂደት እንደሚቀጥልም ተናግረዋል፡፡

የ6ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ሥርዓተ ሢመት ፈጸሙ

የካቲት 26 ቀን 2005ዓ.ም

በእንዳለ ደምስስ
ሪፖርታዥ
1-bealesimet

“የቤተ ክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን አከብራለሁ አስከብራለሁ” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 6ኛ ፓትርያርክ ሆነው የተመረጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሥርዓተ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም. እንደተፈጸመላቸው   ቤተ ክርስቲያንንና ምእመናንን ለማገልገል ቃለ መሐላ የፈጸሙ ሲሆን ከሰሜን አሜሪካ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር የሚካሔደው የእርቀ ሰላም ሂደት እንደሚቀጥልም ተናግረዋል፡፡

የ6ኛው ፓትርያርክ ሥርዓተ ሢመት ተፈጸመ

የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 6ኛ ፓትርያርክ ሆነው የተመረጡት የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ሥርዓተ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የካቲት 24 ቀን 2005 ዓ.ም. ተፈጸመ፡፡

ከዋዜማው ጀምሮ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የማኅሌት ጸሎት በማድረስ የተጀመረው ሥርዓተ ጸሎት ከሌሊቱ 10፡00 ሰዓት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ከአቃቤ መንበረ ፓትርያርኩ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፤ እንዲሁም ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በመሆን በመንበረ ጸባዖት ቅድሥት ሥላሴ ካቴድራል በመገኘት ሥርዓተ ጸሎቱ ቀጥሏል፡፡
ከኪዳን ጸሎት በኋላ ሥርዓተ ቅዳሴው ቀጥሎ ፤ ከሥርዓተ ቅዳሴው ጋር በማያያዝ የቅዱስ ፓትርያርኩ ሥርዓተ ሢመት በአቃቤ መንበሩ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል እየተመራ በማከናወን ቅዱስ ፓትርያርኩ ቤተ ክርስቲያኒቱን ለማገልገል ቃለ መሐላ ፈጽመዋል፡፡ ከሥርዓተ ሢመቱ በኋላ ከአኀት ቤተ ክርስቲያናት መካከል የሕንድ፤ የግብጽ እንዲሁም የአርመን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያናት በየተራ ጸሎት አድርሰዋል፡፡
abune mathias entronment