ማኅበረ ቅዱሳን ከስደት ተመላሾችን ለመደገፍ እንደሚሠራ አስታወቀ
ኅዳር 24 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ማኅበረ ቅዱሳን ከሳውዲ አረቢያ ተመላሽ ወገኖቻችንን ለመደገፍ ቀጣይ ሥራዎችን እንደሚሠራ አስታወቀ፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን ከሳውዲ አረቢያ በመመለስ ላይ ለሚገኙ ከ2ሺሕ በላይ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ኅዳር 23 ቀን 2006 ዓ.ም. ቦሌ በሚገኘው የስደተኞች ጊዜያዊ መቀበያ ጣቢያ በመገኘት የምሳ ግብዣ ባደረገበት ወቅት የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጸሐፊ አቶ ተስፋዬ ቢሆነኝ ማኅበሩ በዚህ በጎ አድራጎት ተግባር ላይ ለመሳተፍ የተነሣበትን ምክንያት ሲገልጹ “ማኅበረ ቅዱሳን እንደ ክርስትናም፤ እንደ ዜግነት የወገኖቻችን በዚህ ሁኔታ ላይ መገኘት ያስጨንቀዋል፡፡ ችግሩንም ለመፍታትና ወገኖቻችንን ለመደገፍ ማኅበራችን የበኩሉን ድርሻ መወጣት እንዳለበት በማመን በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ይህ የምሳ ግብዣ የመጀመሪያ ምዕራፍ ሲሆን ወንድሞቻችንና እኅቶቻችንን ለመደገፍ ምእመናንንና አባላትን በማስተባበር ቀጣይ ሥራዎችን እንሠራለን፡፡” ብለዋል፡፡