የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ደቀ መዛሙርቱን ዛሬ አስመረቀ፡፡
ሰኔ ፲፰ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ በብሉይና በሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ ለአምስትና ለሦስት ዓመታት ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት ዛሬ ረፋድ ላይ በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ አስመረቀ፡፡
This author has not written his bio yet.
But we are proud to say that Mahibere Kidusan contributed 1445 entries already.
ሰኔ ፲፰ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ በብሉይና በሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ ለአምስትና ለሦስት ዓመታት ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት ዛሬ ረፋድ ላይ በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ አስመረቀ፡፡
ሰኔ ፲፯ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው
መንፈስ ቅዱስ ማለት ከሦስቱ አካላት (ከቅድስት ሥላሴ) አንዱ፤ የእግዚአብሔር አብ፣ የእግዚአብሔር ወልድና የራሱም አካላዊ እስትንፋስ የኾነው እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡
ሰኔ ፲፯ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በመምህር ማዕበል ፈጠነ
ጰራቅሊጦስ ማለት ከሣቴ ምሥጢር ማለት ነው፡፡ ይኸውም በግብሩ ታውቋል፡፡ በበዓለ ጰራቅሊጦስ አበው ሐዋርያት ብዙ ምሥጢር በመንፈስ ቅዱስ ተገልጾላቸው ብሉይና ሐዲስን ተርጕመዋል፡፡
ሰኔ ፲፮ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ እንደሚነግረን በጉባኤ ኤፌሶን የተወገዘውን፣ በኋላም በጉባኤ ኬልቄዶን ጊዜ በመለካውያን አማካኝነት የመጣውን የሁለት አካል፣ ሁለት ባሕርይ የኑፋቄ እምነት አንቀበልም በማለታቸው በባዛንታይን ነገሥታት ስቃይ የጸናባቸው ተስዓቱ (ዘጠኙ) ቅዱሳን መነኮሳት ከሶርያና ከታናሽ እስያ ተሰደው በአልአሜዳ ዘመነ መንግሥት በ፬፻፹ ዓ.ም ወደ አገራችን ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል፡፡
ሰኔ ፲፬ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
እንደሚታወቀው በዓለ ጰራቅሊጦስን ተከትለው ሁለት ዐበይት አጽዋማት ይጀመራሉ፡፡ እነዚህም ጾመ ሐዋርያት እና ጾመ ድኅነት (ረቡዕና ዓርብ) ሲኾኑ፣ ቍጥራቸውም ከሰባቱ አጽዋማት ውስጥ ነው፡፡ ስለኾነም ኹላችንም ልንጾማቸው እንደሚገባ በቤተ ክርስቲያን ሕግ ታዝዟል፡፡ ይህም ከቀደሙ አባቶቻችን ጀምሮ የመጣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥርዓት እንጂ እንግዳ ሕግ አይደለም፡፡
ሰኔ ፲፬ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዓለ ጰራቅሊጦስ ከዘጠኙ የጌታችን ዐበይት በዓላት አንዱ ሲኾን በዕለቱ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን የሚዘመረው የቅዱስ ያሬድ መዝሙርም ይትፌሣሕ የሚለው የትንሣኤ መዝሙር ነው፡፡ እንደ መዝሙሩ ኹሉ በጰራቅሊጦስ በዓል በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ የቅዱሳት መጻሕፍት ክፍሎችም በትንሣኤ ዕለት የተነበቡት ምንባባት ናቸው፡፡
ሰኔ ፲፬ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
የተወደዳችሁ የድረ ገጻችን ተከታታዮች ሰኔ ፲፩ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም በዓለ ጰራቅሊጦስ በሚል ርእስ አቅርበነው የነበረውን ጽሑፍ ለንባብ እንዲያመች በዓለ ጰራቅሊጦስ፣ የጰራቅሊጦስ መዝሙርና ምንባባት፣ እንደዚሁም ጾመ ሐዋርያትና ጾመ ድኅነት በሚሉ ሦስት ንዑሳን አርእስት ከፋፍለን እንደሚከተለው አቅርበነዋል፤
ሰኔ ፲፫ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በደመላሽ ኃይለ ማርያም
በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በከላላ ወረዳ ቤተ ክህነት በ፳፻፫ ዓ.ም በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ መሠረቱ የተቀመጠው፣ ከስምንት ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት በአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ስም የተገነባው ባለ ሦስት ፎቅ ኹለገብ ዘመናዊ ሕንጻ ሰኔ ፲፪ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም ተመረቀ፡፡
፲፪.በዘመናችን ሚዲያ በወጣቱ እና በሕፃናት አስተዳደግ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እየፈጠረ ስለሚገኝ፣ የቤተ ክርስቲያኒቷን አስተምህሮ ለምእመናን በስፋት ማዳረስ እንዲቻል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የሚመራ እና የሚተዳደር፣ ቤተ ክርስቲያኒቷንም የሚወክል የቴሌቭዥን መርሐ ግብር ሥርጭት በመጀመሩ ከመምሪያው ጀምሮ እስከ አጥቢያ ያለን ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በጋራ ለመሥራት ቃል እንገባለን፡፡
ሰኔ ፲፩ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም
በዲያቆን ኤፍሬም የኔሰው
*ጰራቅሊጦስ* የሚለው ቃል ከሦስቱ አካላት አንዱ ለኾነው ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ስሙ ሲኾን፣ ትርጕሙም በጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ ናዛዚ (የሚናዝዝ)፣ መጽንዒ (የሚያጸና)፣ መስተፍሥሒ (የሚያስደስት) ማለት ነው፡፡ በዓለ ጰራቅሊጦስ በሌላ ቃል በዓለ ጰንጠቆስጤ በመባልም ይታወቃል፡፡ ይኸውም በግሪክ ቋንቋ በዓለ ኀምሳ፣ የፋሲካ ኀምሳኛ ዕለት፣ በዓለ ሠዊት (የእሸት፣ የመከር በዓል) ማለት ነው /ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፱፻፮ እና ፱፻፯/፡፡