Entries by Mahibere Kidusan

ግስ

የግስ አርስቶች አልፎ አልፎ በአንዳንድ ጉባኤ ቤቶች በተወሰነ መንገድ ልዩነት አላቸው። ልዩነታቸው ግን የቁጥር ሳይሆን ግሶችን የመለዋወጥ ሁኔታ ነው። በቁጥር ሁሉም ስምንት ያደርጓቸዋል። ይሁን እንጂ በዚህ ጽሑፍ አብዛኛዎቹ የሚከተሉትን እናቀርባለን። ለማሳያ ያህል ሊቀ ሊቃውንት ያሬድ ሽፈራው መጽሐፈ ግስ ወሰዋስው መርኆ መጻሕፍት በተባለ መጽሐፋቸው የግስ አርስቶች የምንላቸው ስምንት ናቸው ። እነርሱም ቀተለ፣ ቀደሰ፣ ተንበለ፣ ባረከ፣ ማኅረከ፣ ሴሰየ፣ ክህለ፣ ጦመረ ናቸው በማለት ይገልጹአቸዋል። (ያሬድ፣ገጽ ፬፻፳፭) 

ጾመ ሐዋርያት እና ጾመ ድኅነት

በዚህ ዓመት ጾመ ሐዋርያት ሰኔ ፩፤ ጾመ ድኅነት ደግሞ ሰኔ ፫ ቀን ይጀመራሉ፡፡ በመሆኑም የምንጠቀመው በራሳችን መልካም ተግባር፤ የምንወቀሰውም በራሳችን ኃጢአት መሆኑን ተረድተን ‹ይሄ የቄሶች፤ ይሄ የመነኰሳት ነው› የሚል ሰበብ ሳንፈጥር ሁላችንም በአንድነት ብንጾማቸው ከእግዚአብሔር ዘንድይቅርታ ጸጋና ምሕረትን እናገኛለንና ራሳችንን ለጾም እናዘጋጅ፡፡

ዘጠነኛው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ ሊካሄድ ነው

ዘጠነኛው የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጉባኤ በመጭው እሑድ ግንቦት ፴ ቀን ፳፻፲፪ ዓ/ም ሊካሄድ እንደሆነ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ መምህር ዕንቈ ባሕርይ ተከሥተ አስታወቁ፡፡

በዓለ ጰራቅሊጦስ

በዓለ ጰራቅሊጦስ የሚከበረው ርደተ መንፈስ ቅዱስን መሠረት በማድረግ በመሆኑ ምክንያት ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ለመቀበል ነው፤ በዕለቱም ኢየሩሳሌም በተባለችው ቤተክርስቲያን ስለመጽናት፤ ከግለኝነት ይልቅ መንፈሳዊ አንድነትን ስለማስቀደም እና ስለመጸለይ  እንማራለን፡፡  

ግስ

ግስ ከቃል ክፍሎች አንዱ ሲሆን በብዙ መንገድ ሊፈታ ይችላል። በዋናነት ግን ድርጊት አመልካች የሆነ በዐረፍተ ነገር ውስጥ የሐሳብ መደምደሚያ፣ ወይም የዐረፍተ ነገር ማሠሪያ ተብሎ ይተረጎማል። በርካታ ምሁራን በተለያየ መልኩ ስላብራሩት የምሁራኑን አገላለጽ እንደሚከተለው እንመልከት።

የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኀጢአታችን ሁሉ ያነጻናል፡፡ (፩ኛ ዮሐ.፩፥፯)

የሰው ልጅ ንስሓ ገብቶ ከኀጢአት ነጽቶ ቅዱስ ቊርባንን የሚቀበል ከሆነ ዳግም ሞት የለበትም፡፡ በፍጻሜ ዘመኑ ከዚህ ዓለም ተለይቶ ወደ ወዲያኛው ዓለም በሚሸጋገርበት ጊዜም ወደ ገነት እንጅ ወደ ሲኦል አይወርድም፡፡ ወደ ሲኦል ቢሄድም እንኳ ልትቀበለው አትችልም፤ ምክንያቱም በሕይወተ ሥጋ ሳለ በደመ ክርስቶስ ታትሟልና፡፡

‹‹እመን እንጂ አትፍራ›› (ማር. ፭፥፴፮)

በክርስቶስ ክርስቲያን ለተባልን ለእኛ ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች እምነት የድኅነታችን መሠረት ነው፤ በፈተናና መከራ ለተሞላው ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ለጠላት ከመሸነፍም ሆነ በኃጢአት ከመውደቅ የሚያድነን እንዲሁም በተስፋ ነገን እንድንጠብቅ የሚረዳን እምነታችን ነው፡፡ ዘወትር በጸሎት አምላካችን ድኅነተ ሥጋን እና ድኅነተ ነፍስን ለምንማጸን እርሱ እግዚአብሔር ቸርነቱና ምሕረቱ የበዛ ነው፡፡

‹‹ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ሰው ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች›› (ያዕ. ፭፥፲፮)

እዚህ ላይ ማስተዋል ያለብን አምላካችንን በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ ሌት ከቀን ያለማቋረጥ በጸሎት፤ በጾም እና በስግደት ያገለገሉ ቅዱሳን አባቶቻችንን በማሰብ ለኃጢአተኞች ምሕረትን እንደሚያደርግ ነው፡፡ በተለይም ጻድቁ አባታችን አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ ተጋድሏቸውን ሲፈጽሙ በተሰጣቸው ቃል ኪዳን መሠረት እኛን ከቸነፈር እንደሚጠብቁን በማሰብ ልንጽናና ይገባል፡፡ …..
እንዲሁም ሕፃኑ ቂርቆስ በሰማዕትነት ባረፈበት ዕለት ‹‹…ስምህ በተጠራበት፣ ቤተ መቅደስህ በታነጸበት ሥዕልህ ባለበት ቦታ ሁሉ የሕፃናት እልቂት፣ የከብት በሽታ፣ የእህል እጦት፣ ረኃብ፣ ቸነፈር አይደርስም›› የሚል ቃል ኪዳን ሰጥቶታል፡፡

‹‹እግዚአብሔር ይቅርታን ይረሳልን? በቁጣውስ ምሕረቱን ዘጋውን?›› (መዝ. ፸፮፥፱)

ብዙዎች በአሁኑ ሰዓት ስጋትና ጭንቀት ላይ ናቸው፤ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር ይቅርታን ይረሳልን? በቁጣውስ ምሕረቱን ዘጋውን?›› ብሎ በጸሎት እንደጠየቀው አዛውንቶችም የዚህ መቅሰፍት ማብቂያ የሚቆምበትን ጊዜ በመመኘት አምላካቸው ስለምን ቸል እንዳለ ሲጠይቁ ይሰማሉ፤ ምሕረትንም እንዲያበዛልን አብዝተው ሲለምኑ ይደመጣሉ፡፡ (መዝ. ፸፮፥፱)