የምን አለበት መዘዝ!
በዚህ ቃል ብዙዎች ሕይወታቸው ተጎድቷል፤ ሃይማኖታቸውም እንዲሁ፤ ለምሳሌ “ባንጾም ምን አለበት? እግዚአብሔር ምን ሠራችሁ እንጂ ምን በላችሁ አይለንም” የሚሉ አሉ፤ “መስቀል ባንሳለም ምን አለበት? ወደ ቤተ ክርስቲያን ባንሄድ ምን አለበት? እግዚአብሔር በሁሉ ቦታ አለ” የሚሉ ሰዎችም አሉ፤ ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንም ሆነ ከሕዝባችን ባህል ውጪ “በምን አለበት” የሚጓዙ ሰዎች ጥቂቶች አይደሉም።፡