Entries by Mahibere Kidusan

መልካም አስተዳደር እና ቤተ ክርስቲያን

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ከዚህ ቀደም ከክፍል አንድ እስከ ክፍል ሦስት ድረስ ስለ መልካም አስተዳደር፣ የመልካም አስተዳደር እጦት  በቤተ ክርስቲያን እና ያስከተለው ጉዳት ወይም ተጽእኖ በጥቂቱ አስነብበናችኋል፡፡ በዚህ በመጨረሻው ክፍል አራት ደግሞ የመልካም አስተዳደር መስፈን የሚያስገኛቸውን ጥቅሞችን  በከፊል ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ መልካም ንባብ!

በዓለ አጋእዝተ ዓለም ሥላሴ

አጋእዝተ ዓለም ሥላሴ በኃጢአት የተገነባውን የሰናዖር ግንብ ያፈረሱበት አንድነታቸውንና ሦስትነታቸውን በግልጽ ያሳዩበት ጥር ሰባት ቀን የከበረ በዓል እንደመሆኑ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡

ግዝረተ ክርስቶስ

በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ከርስቶስ ዘጠኙ ንዑሳን በዓላት አንዱና የመጀመሪው ሲሆን ይህም ግዝረተ ክርስቶስ ይባላል። በቅዱስ ሉቃስ ወንጌል እንደተጻፈው “ሊገርዙት ስምንት ቀን በሞላ ጊዜ፥ በማኅፀን ሳይረገዝ በመልአኩ እንደ ተባለ፥ ስሙ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ወደ ግዘረት ቤት ወሰደችው፤ ገራዡ ምላጩን ይዞ ቀረበ፤ ነገር ግን ምላጩ እጁ ላይ ሳላ ውኃ ሆኖ ፈሰሰ። ጌታችንም በተአምራት የተገረዘ ሆኖ ተገኘ፡፡” (ሉቃ.፩፥፳፩)

በዓለ ልደቱ ለአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ

አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሀገራቸው ንሂሳ ግብጽ ነው፡፡መላው ሕይወታቸውንም በምድረ በዳ የኖሩ አባት ናቸው፤ በዝቋላ ተራራ ባለው ባሕር ውስጥ ፻ (መቶ) ዓመት ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያውያን ምሕረትን በመለመን ለብዙዎች ድኅነት የሆኑ ታላቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ የተወለዱት ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ቢሆንም በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል ምክንያት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በሠሩልን ሥርዓት መሠረት ጥር ፭ በድምቀት እናከብራለን፡፡

ቁጣና መዘዙ

ቁጣ የሚጫር የእሳት ክብሪት ማለት ነው፡፡ እሳት አንድ ጊዜ በክብሪት ከተጫረች በኋላ ሰደድ እሳት ትሆናለች፡፡ በቁጣ ሁሉም የኃጢአት ዓይነቶች ከመዛግብቶቻቸው ወጥተው ይቀጣጠላሉ፡፡ አንድን ሰው ድንገት አንድ ቁጡ ሰው ተነሥቶ ክፉ ቢናገረውና በይቅር ባይነት መንፈስ ቢያልፈው እንኳን ያ ቁጡ ሰው ቀኑን ሙሉ በቁጣ ላይ ሠልጥኖ ይውላል።

“ሰው ችግሩን በልቡ እያወቀ በዓይኑ እያየ እንዴት ገደል ውስጥ ይገባል? ዕርቅና ይቅርታ ማንን ጐዳ? ሰላምና አንድነት ማንን አከሰረ? ሰበብ አስባብ እየተፈለገ በሆነውም ባልሆነውም ከመተላለቅ ለምን ኢትዮጵያ የሁላችን ናት ብለን በእኩልነትና በስምምነት መኖር አቃተን?”

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ በዓለ ልደትን አስመልክቶ ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው ያስተላለፉት መልእክት።

ወልድ ተወለደልን!

ኧረ ይህች ቀን ምንኛ ድንቅ ናት!

በዓይን የማይታየው የተገለጠባት

የማይዳሰሰው በአካል የተገኘባት

አንድ አምላክ ፈጣሪ የተወለደባት

እርሱ ነው ተስፋችን የዓለም መድኃኒት

የሆነው ቤዛ ለሁሉ ፍጥረት!

ወልድ ተወለደልን መድኃኒዓለም

በከብቶች በረት በቤተ ልሔም!

‹‹ወደ ቤተ ልሔም እንሂድ!›› (ሉቃ.፪፥፲፭)

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን! ትምህርት እንዴት ነው? አሁንማ ፈተና ደርሷል አይደል ልጆች? ስለዚህ ጨዋታ ሳያታልላችሁ በትኩረት በማጥናት፣ ያልተረዳችሁትን በመጠየቅ፣ የግማሽ ዓመት ፈተናውን በጥሩ ውጠየት ለማለፍ ማቀድ አለባችሁ!

ታዲያ በቀደሙት ትምህርታችን ስለ ጾመ ነቢያትና ስለ ነቢያት አባቶቻችን ስንማማር ነበር፤ አሁን ደግሞ የጌታችን መድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል እናከብራለን፤

መልካም አስተዳደር እና ቤተ ክርስቲያን

የእግዚአብሔር ቤተ ሰቦች! እንዴት ሰነበታችሁ? በክፍል ሁለት ጽሑፋችን ‹‹የቤተ ክርስቲያን መልካም አስተዳደር እጦት መንሥኤዎች›› በሚለው ርእስ ከተራ ቁጥር አንድ እስከ አምስት የዘረዘርናቸውን ምክንያቶች ታስታውሳላችሁ፡፡ በዚህ ክፍልም ከዚያው የቀጠለውን ይዘንላችሁ ቀርበናል፤ መልካም ንባብ!

ሰባቱ ኪዳናት

ኪዳን በሰውና በእግዚአብሔር እንዲሁም በሰውና በሰው መካከል የሚመሠረት ስምምነት ነው።ዋናው ጉዳያችን እግዚአብሔር ከፍጥረቱ ጋር የሚያደርገው ቃል ኪዳን ነው። በባሕርይ የማይታየው እግዚአብሔር ምሕረቱ የበዛ ስለሆነ ብዙ ጊዜ ከፍጥረቱ ጋር መሐላ ፈጽሟል። ከብዙ አበው ጋርም ቃል ኪዳን አድርጓል። የማይታይና ኃያል እግዚአብሔር ከፍጥረቱ ጋር የሚያደርገውን ውል ለተመለከተ ቸር አምላክ እንዳለው ያውቃል።