New Search

If you are not happy with the results below please do another search

1 search result for:

1

የዐቢይ ጾም ስብክት (ክፍል 5)

መጋቢት 7/2004 ዓ.ም.

በአያሌው ዘኢየሱስ

 

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤

 

የዐቢይ ጾም አምስተኛ ሳምንት ሰንበት «ደብረ ዘይት» ተብሎ ይጠራል፡፡ ደብረ ዘይት ከኢየሩሳሌም በስተ ምሥራቅ የሚገኝ ተራራ ነው፡፡ ተራራው በዚህ ስም የሚጠራው ለዘይት የሚሆን የወይራ ተክል በብዛት ስለሚበቅልበት ነው፡፡ ጌታችን ቀን ሲያስተምር ውሎ በደብረ ዘይት ያድር ነበር፡፡ ለደቀ መዛሙርቱም ለሕዝቡ በምሳሌ ያስተማረውን ይተረጉምላቸው ነበር፡፡ የዓለም ፍጻሜና የዳግም ምጽአቱን ምልክት ለደቀ መዛሙርቱ ያስተማራቸው በዚሁ ተራራ ላይ ነውና የጌታን ዳግም ምጽአት የምናስብበት አምስተኛው የዐቢይ ጾም ሰንበት ስሙን ከተራራው ወስዷል ማለት ነው፡፡ ደብረ ዘይት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን ዘንድ «እኩለ ጾም» ተብሎ ይጠራል፡፡ በዚህ ስያሜ የሚጠራውም የጾሙ ሳምንታት አጋማሽ ወይም እኩሌታ ስለሆነ ነው፡፡ አንዳንድ የቤተ ክርስቲያን አባቶች መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ እሑድ፣  የደብረ ዘይት ዕለት ይመጣል ብለው ስለሚያስተምሩ በዚህ ሰንበት የሚበዙት ምዕመናን ዕለቱን በታላቅ ዝግጅት ማለትም በንስሓና በቅዱስ ቁርባን ይቀበሉታል፡፡ በዚህ ዕለት የሚሰበከው ምስባክ፣ የሚሰጠው የወንጌል ትምህርትና የሚነበቡት የሐዋርያት ሥራና የመልእክታት ንባባት በሙሉ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ሁለተኛ አመጣጥ የሚናገሩ ናቸው፡፡