12

ገብርኄር /ለሕፃናት/

መጋቢት 14/2004 ዓ.ም.

በቴዎድሮስ እሸቱ

 

ደህ12ና ሰነበታችሁ ልጆች? እንዴት ናችሁ? በጾሙ እየበረታችሁ ነው አይደል? ጎበዞች፡፡ ዛሬ ስድስተኛው ሳምንት ላይ ደርሰናል፡፡ ይህ ሳምንት ገብርኄር ይባላል፡፡ ገብርኄር ማለት ልጆች መልካም አገልጋይ ማለት ነው፡፡ በዚህ ሳምንት በቤተ ክርስቲያናችን ክርስቶስ ስለመልካም አገልጋይ ያስተማረው ትምህርት ይነገራል፡፡ ይህን የተመለከተ ምስጋናም ይቀርባል፡፡

 

አንድ ባለጸጋ አገልጋዮቹን ያስጠራቸውና ለአንኛው 5 መክሊት ለሁለተኛው 2 መክሊት ለሦስተኛው ደግሞ 1 መክሊት ወርቅ ይሰጣቸዋል፡፡ ከዚያም እኔ እስክመጣ በዚህ ወርቅ በመነገድ ተጠቀሙ ብሏቸው ወደሩቅ ሀገር ይሔዳል፡፡ ልጆች መክሊት የወርቅ መለኪያ /መስፈሪያ/ ነው፡፡

ይህም ባለጸጋ ከሔደበት ሀገረ ብዙ ከቆየ በኋላ ወደ ሀገሩ ይመለስና ወርቅ የሰጣቸውን ሰዎች በመጥራት ስለንግዳቸው1212 ይጠይቃቸዋል፡፡ አምስት የተሰጠው አገልጋይ ሌላ አምስት መክሊት አትርፌአለሁ አለው፡፡ ጌታውም አንተ መልካም አገልጋይ ነህ ወርቁን ከነትርፉ ውሰድ ወደጌታህም ደስታ ግባ አለው፡፡ ሁለት መክሊት የተሰጠውም ሌላ ሁለት መክሊት እንዳተረፈ ተናገረ ጌታው እሱንም አንተም መልካም አገልጋይ ነህ በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሀለሁ ወደጌታህ ደስታ ግባ አለው፡፡ በመጨረሻም አንድ መክሊት የተሰጠው አገልጋይ መጣ እንዲህም አለ “ጌታዬ አንተ ካልዘራህበት የምታጭድ ያልበተንከውን የምትሰበስብ ክፉ ጌታ መሆንህን አውቃለሁ ስለዚህ ሌቦች እንዳይሠርቁኝ አታላዮች እንዳይቀሙኝ ብዬ መክሊትህን ቀብሬ እስክትመጣ አስቀምጨዋለሁ አሁንም እንካ ይኸው አንድ መክሊትህ” ብሎ ሰጠው፡፡ ጌታውም “አንተ ክፉ አገልጋይ መቼ ነው እኔ ያልዘራሁትን ያጨድኩት፣ ያልበተንኩትን የሰበሰብኩት አሁን ወርቁን ተቀበሉትና ለባለ አምስት መክሊቱ ስጡት እሱን ደግሞ ወደ ዘለዓለም ሃዘንና መከራ ወዳለብት ወደጭለማው አውጥታችሁ ጣሉት” አላቸው፡፡ አገልጋዮችም ይህንን ክፉ አገልጋይ ወደ ጭለማው አውጥተው ጣሉት፡፡

 

ልጆች እንግዲህ በዚህ ሳምንት የሚነገረው ታሪክ ይህ ነው፡፡ እናንተ ክፉ አገልጋይ እንዳትባሉ ተግታችሁ ሥሩ በሃይማኖት ጠንክሩ እሺ! መልካም ደህና ሰንብቱ፡፡

ሆሣዕና (የዐቢይ ጾም 8ኛ ሳምንት)

የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)

ወእንዘ ሰሙን በዓለ ፋሲካ ቀርቡ አርዳኢሁ ለአምላከ ጽድቅ ኀበ ደብረ ዘይት ሙራደ ዓቀብ ሀገረ እግዚአብሔር ወተቀበልዎ ሕዝብ ብዙኃን አዕሩግ ወሕፃናት ነሢኦሙ አዕፁቀ በቀልት እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም ተፅዒኖ ዲበ ዕዋል ቦአ ሀገረ ኢየሩሳሌም በትፍሥሕት ወበሐሴት ይሁቦሙ ኃይለ ወሥልጣነ፡፡

ትርጉም: “በፋሲካ በዓል ሰሞን የእውነት አምላክ ደቀ መዛሙርት ወደ ደብረ ዘይት ቀረቡ፤ በሀገረ እግዚአብሔር (ኢየሩሳሌም) አቀበቱ ላይ ብዙ አረጋውያንና ሕፃናት የዘንባባ ቅጠል ይዘው ሆሣዕና በአርያም እያሉ ተቀበሉት፣ በአህያ ውርንጫ ላይ ተጭኖ በፍጹም ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ። ለእነዚህ ኃይልና ሥልጣንን ይሰጣቸዋል።

መልዕክታት

ዕብ.8÷1-ፍጻ. ከተናገርነውም ዋናው ነገር ይህ ነው፤ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን፡፡ እርሱም የመቅደስና የእውነተኛይቱ ድንኳን አገልጋይ ነው፤ እርስዋም በሰው ሳይሆን በእግዚአብሔር የተተከለች ናት፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)

 

ምስባክ

 

መዝ.80÷3 “ንፍሑ ቀርነ በዕለት ሠርቅ፡፡ በእምርት ዕለት በዓልነ፡፡ እስመ ሥርዓቱ ለእስራኤል ውእቱ”

 

ትርጉም፦ በመባቻ ቀን በታወቀችው በዓላችን ቀን መለከትን ንፉ፤ ለእስራኤል ሥርዐቱ ነውና÷ የያዕቆብም አምላክ ፍርድ ነውና፡፡

ወይም

መዝ.80÷2 “እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሓተ፡፡ በእንተ ጸላዒ፡፡ ከመ ትንሥቶ ለጸላዒ ወለገፋዒ፡፡”

 

ትርጉም፦ ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ፡፡ ስለ ጠላት÷ ጠላትንና ግፈኛን ታጠፋው ዘንድ፡፡

ወንጌል

ዮሐ.12÷1-11 ፋሲካ ከሚውልበት ከስድስተኛው ቀን አስቀድሞ ጌታችን ኢየሱስ ከሙታን ያስነሣው አልዓዛር ወደ ነበረበት ወደ ቢታንያ መጣ፡፡(ተጨማሪ ያንብቡ)

ቅዳሴ

Normal
0

false
false
false

EN-US
X-NONE
X-NONE

MicrosoftInternetExplorer4

DefSemiHidden=”true” DefQFormat=”false” DefPriority=”99″
LatentStyleCount=”267″>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Normal”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”heading 1″/>

UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Title”/>

UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Subtitle”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Strong”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Emphasis”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Table Grid”/>

UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”No Spacing”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Shading”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light List”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Grid”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Dark List”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Shading”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful List”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Grid”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Shading Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light List Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Grid Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 1 Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 2 Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 1 Accent 1″/>

UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”List Paragraph”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Quote”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Intense Quote”/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 2 Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 1 Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 2 Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 3 Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Dark List Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Shading Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful List Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Grid Accent 1″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Shading Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light List Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Grid Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 1 Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 2 Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 1 Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 2 Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 1 Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 2 Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 3 Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Dark List Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Shading Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful List Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Grid Accent 2″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Shading Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light List Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Grid Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 1 Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 2 Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 1 Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 2 Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 1 Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 2 Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 3 Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Dark List Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Shading Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful List Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Grid Accent 3″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Shading Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light List Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Grid Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 1 Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 2 Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 1 Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 2 Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 1 Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 2 Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 3 Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Dark List Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Shading Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful List Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Grid Accent 4″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Shading Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light List Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Grid Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 1 Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 2 Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 1 Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 2 Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 1 Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 2 Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 3 Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Dark List Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Shading Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful List Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Grid Accent 5″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Shading Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light List Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Light Grid Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 1 Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Shading 2 Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 1 Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium List 2 Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 1 Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 2 Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Medium Grid 3 Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Dark List Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Shading Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful List Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” Name=”Colorful Grid Accent 6″/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Subtle Emphasis”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Intense Emphasis”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Subtle Reference”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Intense Reference”/>
UnhideWhenUsed=”false” QFormat=”true” Name=”Book Title”/>

/* Style Definitions */
table.MsoNormalTable
{mso-style-name:”Table Normal”;
mso-tstyle-rowband-size:0;
mso-tstyle-colband-size:0;
mso-style-noshow:yes;
mso-style-priority:99;
mso-style-qformat:yes;
mso-style-parent:””;
mso-padding-alt:0in 5.4pt 0in 5.4pt;
mso-para-margin-top:0in;
mso-para-margin-right:0in;
mso-para-margin-bottom:10.0pt;
mso-para-margin-left:0in;
line-height:115%;
mso-pagination:widow-orphan;
font-size:11.0pt;
font-family:”Calibri”,”sans-serif”;
mso-ascii-font-family:Calibri;
mso-ascii-theme-font:minor-latin;
mso-hansi-font-family:Calibri;
mso-hansi-theme-font:minor-latin;
mso-bidi-font-family:”Times New Roman”;
mso-bidi-theme-font:minor-bidi;}

ቅዳሴ ዘጎርጎርዮስ፡፡

መዝሙሩንና ምንባባቱን በዜማ ለማዳመጥ ይህን ይጫኑ

የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)
ወእንዘ ሰሙን በዓለ ፋሲካ ቀርቡ አርዳኢሁ ለአምላከ ጽድቅ ኀበ ደብረ ዘይት ሙራደ ዓቀብ ሀገረ እግዚአብሔር ወተቀበልዎ ሕዝብ ብዙኃን አዕሩግ ወሕፃናት ነሢኦሙ አዕፁቀ በቀልት እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም ተፅዒኖ ዲበ ዕዋል ቦአ ሀገረ ኢየሩሳሌም በትፍሥሕት ወበሐሴት ይሁቦሙ ኃይለ ወሥልጣነ፡፡

ትርጉም: “በፋሲካ በዓል ሰሞን የእውነት አምላክ ደቀ መዛሙርት ወደ ደብረ ዘይት ቀረቡ፤ በሀገረ እግዚአብሔር (ኢየሩሳሌም) አቀበቱ ላይ ብዙ አረጋውያንና ሕፃናት የዘንባባ ቅጠል ይዘው ሆሣዕና በአርያም እያሉ ተቀበሉት፣ በአህያ ውርንጫ ላይ ተጭኖ በፍጹም ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም ገባ። ለእነዚህ ኃይልና ሥልጣንን ይሰጣቸዋል።

 
መልዕክታት
ዕብ.8÷1-ፍጻ. ከተናገርነውም ዋናው ነገር ይህ ነው፤ በሰማያት በግርማው ዙፋን ቀኝ የተቀመጠ እንዲህ ያለ ሊቀ ካህናት አለን፡፡ እርሱም የመቅደስና የእውነተኛይቱ ድንኳን አገልጋይ ነው፤ እርስዋም በሰው ሳይሆን በእግዚአብሔር የተተከለች ናት፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 

1ኛ ጴጥ.1÷13 ስለዚህ የልቡናችሁን ወገብ ታጥቃችሁና ነቅታችሁ ኑሩ፤ ኢየሱስ ክርስቶስም ሲገለጥ የምታገኙትን ጸጋ ፈጽማችሁ ተስፋ አድርጉ፡፡  (ተጨማሪ ያንብቡ)
ግብረ ሐዋርያት
የሐዋ.8÷26-ፍጻ. የእግዚአብሔር መልአክም ፊልጶስን ተናገረው፤ እንዲህም አለው÷ “በቀትር ጊዜ ተነሣና በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ በሚያወርደው በምድረ በዳው መንገድ ሂድ፡፡” ተነሥቶም ሄደ፡፡” እሆም÷   (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
ምስባክ
 

መዝ.80÷3 “ንፍሑ ቀርነ በዕለት ሠርቅ፡፡ በእምርት ዕለት በዓልነ፡፡ እስመ ሥርዓቱ ለእስራኤል ውእቱ”

 

ትርጉም፦ በመባቻ ቀን በታወቀችው በዓላችን ቀን መለከትን ንፉ፤ ለእስራኤል ሥርዐቱ ነውና÷ የያዕቆብም አምላክ ፍርድ ነውና፡፡

ወይም

መዝ.80÷2 “እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሓተ፡፡ በእንተ ጸላዒ፡፡ ከመ ትንሥቶ ለጸላዒ ወለገፋዒ፡፡”

 

ትርጉም፦ ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ፡፡ ስለ ጠላት÷ ጠላትንና ግፈኛን ታጠፋው ዘንድ፡፡

ወንጌል
ዮሐ.12÷1-11 ፋሲካ ከሚውልበት ከስድስተኛው ቀን አስቀድሞ ጌታችን ኢየሱስ ከሙታን ያስነሣው አልዓዛር ወደ ነበረበት ወደ ቢታንያ መጣ፡፡(ተጨማሪ ያንብቡ)
ቅዳሴ
Normal 0 false false false EN-US X-NONE X-NONE MicrosoftInternetExplorer4 ቅዳሴ ዘጎርጎርዮስ፡፡

መዝሙሩንና ምንባባቱን በዜማ ለማዳመጥ ይህን ይጫኑ

የትንሣኤ 2 መዝሙርና ምንባባት

የትንሣኤ 2 መዝሙር (ከመጽሐፈ ዚቅ)
ትትፌሣሕ ሰማይ ወትታኃሠይ ምድር ወይንፍሑ ቀርነ መሠረታተ ሕምዝ ወይጸውዑ አድባር ወአውግር ወኩሉ ዕፀወ ገዳም ወዮምሰ ዐባይ ፍሥሐ በሰማያት ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ ተሐፂባ በደመ ክርስቶስ፡፡

ትርጉም: ሰማይ ይደሰታል ምድርም ትደሰታለች የምድር መሠረቶችም ቀንደ መለከትን ይንፉ /ይደሰቱ/ ተራሮችና ኮረብቶችም /ነገሥታት መኳንንት/ ይጩኹ/ይደሰቱ/ የምድረ በዳ እንጨቶችም ይጩኹ ዛሬ በሰማያት ታላቅ ደስታ ሆነ ምድርም በክርስቶስ ደም ታጥባ ፋሲካን/ደስታን/ ታደርጋለች።

 
 
መልዕክታት
1ቆሮ. 15፥20-41
አሁንም ክርስቶስ ከሞቱ ሰዎች ሁሉ አስቀድሞ ተነሥቶአል፡፡ በመጀመሪያው ሰው ሞት መጥቶአልና፥ በሁለተኛው ሰው ትንሳኤ ሙታን ሆነ፡፡ ሁሉ በአዳም እንደሚሞት እንዲሁ በክርስቶስ ሁሉ ሕያዋን ይሆናሉ፡፡ ነገር ግን ሰው ሁሉ በየሥርዐቱ ይነሣል፤ በመጀመሪያ ከሙታን የተነሣ ክርስቶስ ነው፤ ከዚያ በኋላ በክርስቶስ ያመኑ እርሱ በሚመጣበት ጊዜ ይነሣሉ፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 

1ጴጥ.1፥1-13
ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ ከጴጥሮስ፥ በጳንጦስ፥ በገላትያና በቀጰዶቅያ፥ በእስያና በቢታንያ ሀገሮች ለተበተኑ ስደተኞች፥ እግዚአብሔር አስቀድሞ እንዳወቃቸው፥ በመንፈስ ቅዱስም እንደሚቀደሱ፥ ይታዘዙና በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ይረጩ ዘንድ፥ ለተመረጡት፥ ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
ግብረ ሐዋርያት
ሐዋ.2፥22-37
እናንተ የእስራኤል ሰዎች ሆይ፥ ይህን ነገር ስሙ፤ እንደምታውቁት በመካከላችሁ እግዚአብሔር በእጁ ባደረገው በከሃሊነቱ በተአምራቱና በድንቅ ሥራዎቹ እግዚአብሔር የገለጠላችሁን ሰው የናዝሬቱን ኢየሱስን ስሙ፡፡ እርሱንም በተወሰነው በእግዚአብሔር ምክርና በቀደመው ዕውቀቱ እናንተ አሳልፋችሁ በኃጥኣን እጅ ሰጣችሁት፤ ሰቅላችሁም ገደላችሁት፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
 
ምስባክ
 

ዛቲ ዕለት እንተ ገብረ እግዚአብሔር
ንዑ ንትፌሣሕ ወንትሐሠይ ባቲ
ኦ እግዚኦ አድኅንሶ

 

ትርጉም፦

ይህች እግዚአብሔር የፈጠራት /የሠራት/ ቀን ናት
ፈጽሞ ተድላ ደስታን እናድርግባት
አቤቱ አድነን

ወንጌል
ዮሐ.20፥1-19 ከሳምንቱም በመጀመሪያዉ ቀን ማርያም መግደላዊት በማለዳ ገና ጨለማ ሳለ ወደ መቃብር መጣች፤ ድንጋዩንም ከመቃብሩ አፍ ተነሥቶ አገኘችው፡፡ ፈጥናም ወደ ስምዖን ጴጥሮስና ጌታተን ኢየሱስ ይወደው ወደ ነበረው ወደዚያ ወደ ሌላዉ ደቀ መዝሙር መጥታ፥ “ጌታዬን ከመቅብር ወስደውታል፤ ወዴትም እንደ ወሰዱት አላውቅም” አለቻቸው፡፡ (ተጨማሪ ያንብቡ)
ቅዳሴ
ቅዳሴ ዘዲዮስቆሮስ

ሰበር ዜና ከአሰቦት ገዳም

መጋቢት 12/2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

የአብነት ተማሪው በታጣቂዎች ተገደለ

በምዕራብ ሐረርጌ ሜኤሶ ወረዳ በአሰቦት ሥላሴና አባ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ ገዳም የአብነት ተማሪ የሆነው የ7 ዓመቱ ሕፃን ናታን አንበስ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች በ3 ጥይት ተመትቶ መገደሉን የገዳሙ ዋና መጋቢና ምክትል አበምኔት አባ ዘወልደ ማርያም ገለጹ፡፡ ከአባ ሳሙኤል ገዳም በተወሰኑ ሜትሮች ርቀት ላይ ከእናቱ ጋር ወደ ገዳሙ በመውጣት ላይ እያለ ከእናቱ እጅ ቀምተው በመውሰድ ፊት ለፊቷ በሦስት ጥይት ገድለውት ሊያመልጡ ችለዋል፡፡ በእናትየው ጩኸትና በጥይት ድምጽ የተደናገጡት መነኮሳት ገዳዮቹን ለመያዝ ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

 

የገዳሙ መነኮሳት እንደገለጹት ጉዳዩን ለፖሊስ በስልክ ያሳወቁ ሲሆን ፖሊስ “መኪና አግኝተን እስክንመጣ ድረስ ሟቹን  ቅበሩት” በማለታቸው ከቀኑ 8፡00 አካባቢ ሊቀበር ችሏል፡፡ ባቲ በተባለው አካባቢ በአሰቦት ቅድስት ከሥላሴ ገዳም ጀርባ ከሚገኘው አካባቢ ታጣቂ አርብቶ አደሮች ተሰባስበው ወደ ገዳሙ በመቃረብ ላይ መሆናቸውንና መነኮሳቱ ስጋት ላይ እንደሚገኙ ጨምረው ገልጸውልናል፡፡

 

መጋቢት 1 ቀን ባቀረብነው ዘገባ መሣሪያ የታጠቁ ሰዎች እሳቱን በሚያጠፉት ምእመናን ላይ ተኩስ ከፍተው እንደነበርና የፌደራል ፖሊስ አባላት ምላሽ ሰጥተው ከአካባቢው እንዳራቋቸው መዘገባችን ይታወሳል፡፡

Zeqwala 4

የዝቋላ ገዳም እንዴት አደረ?

መጋቢት 12/2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

 

በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገ/መንፈስ ቅዱስ ገዳም ደን ላይ ከቅዳሜ ጀምሮ የተቀሰቀሰው ቃጠሎ እስከ ማክሰኞ ምሽት ድረስ የዘለቀ ሲሆን ሌሊቱን ግን በሰላም እንዳደረና የመርገብ ሁኔታ እየታየበት መሆኑን በስፍራው የሚገኙ ምእመናን ገለጹ፡፡ ቃጠሎው ቢበርድም የተዳፈነው ፍም ነፋሱ እያራገበZeqwala 4ው በአንዳንድ ቦታዎች ላይ ጭስ እየታየ እንደሆነ በተለይም የቅዱሳን ከተማ የተሰኘው የአባቶች የጸሎት ሥፍራ ላይ በከፍተኛ ሁኔታ ጪስ በመጨስ ላይ መሆኑን በስጋት በመግለጽ ላይ ናቸው፡፡ በዚህ ቦታ ላይ ቃጠሎው ዳግም ካገረሸ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ሊያመራ እንደሚችል መነኮሳቱ ይናገራሉ፡፡

 

ከሥፍራው በደረሰን መረጃ መሠረት ምእመናን የመዳከም ሁኔታ የሚታይባቸው ሲሆን የአዳማ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ሌሎችም ምእመናን ወደየመጡበት በመመለስ ላይ ናቸው፡፡ የፌደራል ፓሊስና የኦሮሚያ ፖሊስ ከቀሩት ምእመናን ጋር በመሆን የሚጨሰውን ፍም በማጥፋት ሥራ ላይ ተጠምደዋል፡፡ ወደ ዝቋላ ገዳም ከተለያዩ አቅጣጫዎች ምእመናን እየሔዱ ሲሆን በሥፍራው የሚገኙ ምእመናን አሁንም ተጨማሪ የሰው ኀይል እንዲደርስላቸው በመጠየቅ ላይ ናቸው፡፡

የመነኮሳቱ የድረሱልን ጥሪ ከዝቋላ ገዳም

መጋቢት 11/2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

ቃጠሎውን መቆጣጠር አልተቻለም

ከገዳሙ ጸሐፊ የደረሰን መረጃ፡-

ቃጠሎው ከአቅም በላይ ሆኗል፡፡ መነኮሳቱና ምእመናን በመዳከም ላይ ናቸው፡፡ ከእግዚአብሔር በረከትን የምትሹ ምእመናን ድረሱልን፡፡ እሳቱ በአንድ አቅጣጫ ጠፋ ሲባል በሌላ በኩል እየተነሣ ተሰቃይተናል፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ በመገሥገሥ ላይ ስለሆነ የቅዱስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች፣ ማኅበራት፣ ከዩኒቨርሲቲዎችና የኮሌጅ ተማሪዎች፣ እንዲሁም ምእመናንና ወጣቶች፣ አቅም ያለው ሁሉ እሳቱን ለማጥፋት በተቻላችሁ አቅም ድረሱልን፡፡ መምጣት የማትችሉ በጸሎት አትለዩን በማለት ጥሪ አቅርበዋል፡፡

 

 

የዝቋላ ደን ቃጠሎ ተጨማሪ እርዳታ እንደሚያስፈልገው ተገለጠ፡፡

መጋቢት 11/2004 ዓ.ም

በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ

የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ደን ቃጠሎ ተጨማሪ እርዳታ እንደሚያስፈልገው ተገለጠ፡፡

በቦታው የተገኙት የማኅበረ ቅዱሳን ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም እንደገለጡልን በቦታው በርካታ ምእመናን ተገኝተው እሳቱን ለማጥፋት ጥረት ቢያደርጉም በአስቸጋሪው የአየር ጠባይ የተነሣ ፍህሙ እየተነሳ እንደገና እንዲያገረሽ ስለሚያደርገው ከፍ ያለ እርዳታ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡

ከመንገዱ አስቸጋሪነት እና ከፀሐዩ ግለት አንፃር ከእሳቱ ቃጠሎ ጋር ለሚታገሉ ምእመናንም  የጥም ማስታገሻ የሚሆን ውሃ በመኪና ለማድረስ እንዳልተቻለ ከስፍራው የደወሉልን ምእመናን ገልጠውልናል፡፡

በአሁኑ ወቅት የእሳት አደጋው አርብ ረቡዕ በሚባለው ቦታ እየነደደ እንደሆነና የገዳሙን ደን የምሥራቁን ክፍል እየጨረሰ ወደ ደቡብ አቅጣጫ እየዞረ እንደሆነ ታውቋል፡፡ በአካባቢው ያለው ማኅበረሰብ ትብብር አነስተኛ እንደሆነባቸው ያልሸሸጉት ምእመናኑ፣ ለእርዳታ የሚመጡ ምእመናንም በተቻላቸው አቅም መጥረቢያ፣ አካፋና መቆፈሪያ ይዘው ቢመጡና ምእመናኑም እሳቱን ለማጥፋት አቅም ያላቸው ቢሆኑ ይመረጣል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም በቅርብ ሰዓት በደረሰን መረጃ መሠረት፣ ከሌሊቱ 8፡00 አካባቢ እሳት ወደሚነድበት አካባቢ ለቅኝት የተጓዙ ምእመናን መሬት ላይ ያለው ፍሕም ነፋሱ በመራው አቅጣጫ እየተነሳ እንደሚያቀጣጥል መመልከታቸውንና ከቦታው አስቸጋሪነት አንፃር ምንም ማድረግ እንዳልቻሉ ተናግረዋል፡፡

ለእርዳታ የተጓዘውን ምእመን የማስተናገድ ሸክም በገዳሙ ጫንቃ ላይ እንደወደቀ መነኮሳቱ የተናገሩ ሲሆን፣ ከጊዜ በኋላ ከዐቅም በላይ ሊሆን ስለሚችል ስንቅ በማቅረብ በኩልም ቢሆን ሊተባበሩ የሚችሉ ምእመናንን እርዳታ እንደሚሹ ገልጠዋል፡፡

አምላክ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በይቅርታው ይታደገን!!!

Zeqwala

A Burning Heaven in This World – Mt. Zeqwala Monastery

March 20/2012                                                                                  Hiruy Simie

ZeqwalaThe area of Mt. Zeqwala is a product of intense volcanic activity during a quaternary period. The cooling age produced a well preserved cone structure form of the volcanic eruption. The vent formed after the cooling of the eruption was filled by rain to become a huge crater lake. Written Church sources came to mention the place after the coming of his holiness Abune Gebre Menfes Kidus and his founding of the monastery that is still dedicated to him in 1168 Ethiopian calendar. However, the story of a church built by King Gebre Meskel and St. Yared on the mountain which vanished miraculously is told by the local monks. (read more)
Abuye [Ethiopic for our father] st. Gebre Menfes Kidus [means the salve of the Holy Spirit] was born of Egyptian parents called Simon and Aklisia on November 28, 868 E.C. From the moment he was born he praised the lord and refused to suckle the breast of his mother being separated from the ways of men for the glory of the lord. He has not as a result eaten a worldly food all his life. When he became three years old the Angle of God (St. Gabriel) took him from his parents and gave him to a saintly monk by the name ‘the relative of Light’ in an Egyptian Coptic monastery. He thus started to learn the Holy Scriptures until he was old enough to be made a deacon and a priest by a Bishop called Abraham. After that he was called by God to depart to a jungle and live the life of an anchorite. He faithfully obeyed and lived in a locality called ‘Gebota’ [most probably in Upper Egypt]. There he stayed for 300 years and his cloth wore out and he became perfectly naked suffering from the fierce heat and the terrible cold for in the rainy seasons. God seeing his fortitude and struggle against the weakness of the flesh gave him a white fur as thick as the wool of sheep. At last after 300 years our God Jesus Christ came to him followed by His holy mother and the Apostles including the heavenly angels and gave him his first covenant of forgiveness for the people of Gebota.
After that he was ordered by our Lord and God Jesus Christ to go and continue his prayers and struggle against evil spirits in Ethiopia. Being blessed and made strong by the Holy Spirit Saint Gebre Menfes Kidus came to Ethiopia, sitting on a cloud with his pets of 60 lions and leopards. He reached Ethiopia during the reign of St. Lalibela, and gave the saintly king his blessings. King Lalibela was exceedingly happy and bowed to the saint many times. These two saints then traveled side by side like father and son to Zeqwala. After reaching the mountain, saint Abune Gebre Menfes Kidus decided to stay, told King Lalibela to depart to a place called Adadi and build a church in the name of Holy Mary. The saintly king then went and did just as the holy father had told him.            

During his stay on Mount Zeqwala, our father entered the crater lake upside down, and prayed for Ethiopia and the whole world for 100 years. Then, millions of devils came and began to pound his bones until they became  powder and dissolve in the water. After the end of these years, our Lord Jesus Christ appeared, and told him that he would forgive the sins of the Ethiopian people.  The saint rejoicing traveled to Arabia and met a king who worshiped idols there. As soon as the king and his people saw the saint, a great fear came up on them and they asked him whether he was a beast or a human being because of the fur which covered him from head to toe. Then our father answered saying ‘Yes … I am a man and more a Christian.’ The evil king hearing this wanted to kill him but he and his people became dead instead. Our Father then prayed to God and raised them from the dead. This put the fear of the lord in their hearts and even the evil king became a changed man. Abune Gebre Menfes Kidus then baptized them all and made them Christians and came back to Ethiopia happy. Then he returned back to Ethiopia and stood for many years to pray at a place called Medre Kebd. Then the devil came in the shape of a craw and pulled out his eyes by his beak. Then God ordered the angels St. Gabrieal and Michael to come to him and breathe on his eyes and he was made as he was before. Then he was told by God to travel to the top of Zeqwala and destroy the devils his enemies who live in the heart of evil men who oppose all those who belong to God. He then traveled on a cloud and destroyed 700,000 devils.  Being an anchorite none saw him except a dozen anchorites who recorded his hagiography and others whom he preached the words of God and lived with since his birth.
Abune GebreMenfeskidusSt. Gebre Menfes Kidus lived on the mountain for 262 years after establishing his Monastery. It is said that the saint lived on the place right up to his death in the 15th century. After that the then king of Ethiopia called Endreyas [Hisbe Nagn], built five churches (for St. Michael, for Saint Gabriel, for Holy Mary, for Savior of the world and the last for Abune Gebre Menfes Kidus) on and around the mountain in honor of the saint. These churches continued giving function up to the time of ‘Ahmed the left handed’ who destroyed it in the 16th century. Then Zeqwala and the famous monastery became a ruin for more than 400 years. After that a saintly saint anchorite and monk reached the place in the grace of the Holy Spirit and asked the Showa king Sahile Selassie to build a church on top of the mountain. The king sent soldiers who fought against the lions and bores which populated the place and cleared enough space to build a church. The place was made an important traditional worship site of the Oromo late in the 19th century during the founding of the Monastery once again by a saintly monk by the name Aba Gebre Hiwot. Even today a visitor might encounter these traditional worshipers on the mountain. St. Abo is said to have told a monk that such people will inherit the depth of hell for not believing in Christ seeing the wonders he has done and is doing on the monastery.
After the elapse of this time Emperor Minilik built the present church and dedicated his time and power to preserve the forest on and around the mountain. In that effort, he gave fifes to the monastery and a tax collecting right. Observing the forest fires on the area he is said to have given the monks and priests thirty slaves who serve the monastery. There whose sole duty was to stop forest fires, bury the dead monks and serve the monastery in manual labor. The present people of Zeqwala are descendants of these faithful individuals.
During the Italian invasion a great miracle has occurred on mount Zeqwala. The Catholic Italians accusing that the monastery as a fort of patriots sent a jet to bombard the church. The pilot reaching the area tried to bomb the church but saw a being standing on the mountain and reaching the jet and pushing the bombs away from the Church and scared pilot then beat a hasty retreat. A monk also saw the event and was able to recognize Abune Gebre Menfes Kidus.

The well preserved and intact nature of the mountain natural forest, Crater Lake, wild life be it mammals or birds is still remembered by the elders up to the beginning of the second half of the 20th century. The reverse began to happen with the land proclamation of 1966 E.C. This policy has its own effect at the local level by creating a power vacuum in the area.  As a result with the reigning of chaos the forest on whole area was destroyed. To make matters worse Lutheran Mission was established on the area in 1989 E.C. and converted most of the farming society into Protestants with a deep hostility to the monastery. The so called ‘aid and development’ it planned to do was limited only with a modern headquarters and a huge seedlings of Eucalyptus yearly given to the peasant for free. Thus, the crippled, dependant and perverted peasants (those living at the surrounding lands away from Wanber kebele in most cases) still lead a life of poverty and apathy burning the forest now and then evil for themselves and others with no hope for a better tomorrow.

Today, the extremely dedicated monks in the likeliness of their father Abune Gebre Menfes kidus protect the forest from the surrounding people on and around Zeqwala thirsting for water during the summer months and shivering for warmth in the winter. Therefore, the Children of the EOTC must pay for pipe system to bring water to the place from the town at the base, build a modern hall for the priests and assist them to start apiculture. Helping them to build an all weather gravel road from Dire to the mountain is another area open for the kind laity seeking the blessing of Abune Gere Menfes Kidus. Therefore, all the laity and priests of the Ethiopian Orthodox Church are called to save this wonderful and national heritage from destruction. May the blessing of our God Christ rest on Yuhanis of Debre Wifat the writer of this hagiography in the 15th Century hearing it told from the holy Gebre Menfes Kidus himself and all of us who love the saint.  

Glory to God and to His Holy Mother
Amen!

በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የደን ቃጠሎ በባሰ ሁኔታ ላይ ይገኛል!

መጋቢት 10/2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ


እሳት ወይስ መአት?


በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የደን ቃጠሎ በባሰ ሁኔታ ይገኛል፡፡ ቅዳሜ መጋቢት 8/2004 ዓ.ም. ከቀኑ 6፡00 በኋላ ልዩ ስሙ አዱላላ ከሚባለው አቅጣጫ የተቀሰቀሰው ቃጠሎ በመነኮሳትና በአካባቢው ምእመናን ለማጥፋት ከፍተኛ ጥረት  እያደረጉ እንደሚገኙና ከደብረ ዘይት የአየር ኀይል አባላት ትላንት ምሽት መጥተው እገዛ ለማድረግ ጥረት ማድረጋቸውን የገዳሙ ጸሐፊ አባ ወ/ሩፋኤል ቢገልጹም መፍትሔ እንዳልተገኘ ታውቋል፡፡

 

የቃጠሎው መንስኤ ለማወቅ ያልተቻለ ሲሆን “የቅዱሳን ከተማ” የተሰኘው የአባቶች የጸሎት ሥፍራ በከፍተኛ ሁኔታ በመቃጠል ላይ እንደሚገኝና በሥፍራው ውኃ የሌለ በመሆኑ ቃጠሎውን ለማጥፋት አፈሩን በመቆፈርና በመበተን እንጨቶችን በመቁረጥና በቅጠል በማጥፋት ርብርቡ የቀጠለ ቢሆንም ቃጠሎውን መግታት እንዳልተቻለ አባ ወልደ ሩፋኤል ጨምረው ገልጸዋል፡፡ ወደ ጸበሉ ቦታ እንዳይደርስ ጥረት እየተደረገ ሲሆን ምእመናን ከተለያዩ አካባቢዎች ወደ ገዳሙ በመሔድ ቃጠሎውን ለማጥፋት እየተረባረቡ ይገኛሉ፡፡ የገዳሙ ጸሐፊ አባ ወልደ ሩፋኤል ቃጠሎው ያደረሰው ጉዳት ከፍተኛ በመሆኑ መጠኑን ለመግለጽ መቸገራቸውንና ለመንግሥት አካላትና ለምእመናን የድረሱልን ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ ተመሳሳይ ቃጠሎ በተለያዩ ቤተ ክርስቲያናት ላይ እየደረሰ በመሆኑ “እሳት ወይስ መአት?! በማለት በጭንቀትና በስጋት ምእመናን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡

 

በ2000 ዓ.ም. በዚሁ ገዳም ቃጠሎ ተከስቶ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን በቅርቡም በጎንደር የሰለስቱ ምእት መጻሕፍተ መነኮሳት ጉባኤ ቤት፣ እንዲሁም የጥንታዊው የሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የቅኔ ትምህርት ቤት ቃጠሎ የደረሰባቸው ሲሆን በምዕራብ ሐረርጌ የሚገኘው የአሰቦት ገዳም ደን ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱም ይታወቃል፡፡

 

የዝቋላ የሰኞ መጋቢት 10 ቀን 2004 ዓ.ም. ውሎ

ቃጠሎው እጅግ አሳሳቢ  ሆኗል፡፡


ከጧት ጀምሮ ምእመናን ከደብረ ዘይት፣ ከአዲስ አበባ ከተለያዩ መሥሪያ ቤቶች የተውጣጡ የቤተ ክርስቲያን ልጆች፣ በማኅበረ ቅዱሳን የሚመራው የዩኒቨርሲቲዎች የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች፣ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አባላት ቃጠሎውን ለማጥፋት ቦታው ድረስ ተንቀሳቅሰዋል፡፡ ከገዳሙ በደረሰን መረጃ መሠረት እስከ ቀኑ 12፡00 ሰዓት ድረስ ቃጠሎው በፀሐይና በንፋስ በመታገዝ ከፍተኛ ውድመት እያደረሰ ይገኛል፡፡ መነኮሳቱ ለኦሮሚያ ፖሊስ፣ ለፌደራል ፖሊስና ለአየር ኀይል እንዲሁም ለምእመናን የድረሱልን ጥሪ በማሰማት ላይ ይገኛሉ፡፡ በተለይም ቦታው እጅግ አስቸጋሪ በመሆኑ ውኃ ማግኘት ባለመቻሉ የደኑን ውድመት እያባባሰው ስለሚገኝ ውኃ የሚያመላልሱ ቦቴ መኪናዎች ያሏቸው ምእመናን ውኃ በማመላለስ እንዲደርሱላቸው በመማጸን ላይ ናቸው፡፡

 

ከተለያዩ አካባቢዎች የተንቀሳቀሱት ምእመናን ከአስቸጋሪ ጉዞ በኋላ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ላይ ቦታው የደረሰ ሲሆን ለማጥፋት ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህንን ዜና እስካጠናቀርንበት 12፡00 ሰዓት ድረስ ቃጠሎው እንዳልጠፋና ከሌላ አቅጣጫ ሌላ አዲስ ቃጠሎ መቀስቀሱን በቦታው ከሚገኙ ምእመናን ለመረዳት ችለናል፡፡ ቃጠሎው በዚሁ ከቀጠለ ከፍተኛ የደን ሀብት ያለበት ቦታ መያዙ እንደማይቀር ስጋታቸውን በመግለጽ ላይ ናቸው፡፡

 

በቃጠሎ ጉዳት የደረሰባቸው ምእመናን እንደሚገኙ ከቦታው የደረሰን መረጃ የሚያመለክት ሲሆን በከፍተኛ ጥምና ረሃብ ላይ ለሚገኙ ምእመናን ውኃና ምግብ እንደሚያስፈልጋቸው ጭምር ገልጸዋል፡፡

የዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ደን እየተቃጠለ ነው፤ የምእመናንን እገዛ ይሻል፡፡

መጋቢት 10/2004 ዓ.ም.


በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ


ቅዳሜ መጋቢት 8 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 በኋላ የጀመረው የገዳሙ ቃጠሎ እየተባባሰ እንደሆነ የገለጹልን ያነጋገርናቸው የገዳሙ መነኮሳት እሳቱን ለማጥፋት የምእመናንን እርዳታ እንደሚሻ አሳስበዋል፡፡

 

አያይዘውም ለእርዳታ የሚመጡ ምእመናን ስንቅ እንዲይዙና በውኃ ጥም እንዳይቸገሩ ከቻሉ ውኃ እንዲይዙ፤ ቦቴ መኪና ያላቸውም እንዲተባበሩ ጠይቀዋል፡፡

 

በአሁኑ ወቅት ምእመናን ከደብረ ዘይትና አዲስ አበባ ዙሪያ ወደ ገዳሙ ለእርዳታ እየተጓዙ እንደሆነ ያገኘናቸው መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

 

ዝርዝር ሁኔታውን በቀጣዩ እናቀርባለን፡፡

አምላከ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በምሕረቱ ይታረቀን፡፡